እሑድ 17 ሜይ 2015

የማሙሸት አማረ ክስ


የማሙሸት አማረ ክስ
ሚያዝያ 14/2007 ዓም በisis የታረዱ ወገኖቻችን ላይ የተደረገውን አሰቃቂ ግድያ ለማውገዝ የተጠራውን የተቁውሞ ሠልፍ አመጽ እንዲነሳ አቀነባብረሀል ፣ድንጋይ በመወርወር ሌሎች እንዲወረውሩ አነሳስተሀል፣ ምርጫው ሠላማዊ እንዳይሆን ሁከት ለማስነሳት በመኖሪያ ቤትህ ወጣቶችን በመሠብሰብ አደራጅተሀል ፣ ወዘተ የሚል ነው ግንቦት 05/2007 ዓም ከቤት ወደ ት / ቤት በመጓዝ ላይ እያለ ቦሌ ሚካኤል አካባቢ ታፍኖ የተወሰደው ቦሌ ፓሊስ መምሪያ ከተወሰደ በኋላ ከጥቂት ሰአት በኋላ ሲኤም ሲ አካባቢ ፍርድ ቤት አቅርበው ከተያዘ በኋላ የመያዣ እና ቤት የመበርበሪያ ትዕዛዝ አውጥተው በርብረዋል ።
በማግስቱ በ06/2007 ዓም ሲኤምሲ ፍርድ ቤት 4:30 አካባቢ አቅርበውታል ፍርድ ቤት ያቀረበው ፓሊስ የሱ መርማሪ ያልሆነ ነበር በእለቱ ማሙሸትን የመረመረ መርማሪ ምርመራውን እንዳጠናቀቀና 4 ሠውም እንደመሠከረበት ነግሮት ነበር ፍርድ ቤት ያቀረበው ፓሊስ ግን ምርመራውን እንዳልጨረሰና ምስክሮችም አስመስክሮ እንዳልጨረሰ ገልጾ በተጨማሪም ግብረአበሮቹ ገና እንዳልተያዙ በማስረዳት የ14 ቀን ቀጠሮ ጠይቆበት ነበር ዳኛው እሱ በእራሱ ወንጀል ይጠየቃል ሌሎቹም በስራቸው ይጠየቃሉ የጠየቃችሁት የ14 ቀን ጊዜ ብዙ ነው 4 ቀን በቂ ነው በማለት ወሰነ ።
የማሙሸት አቤቱታ
ማሙሸት መርማሪየ ምርመራ ጨርሰሀል ምስክር ተመስክሮብሀል ብሎኛል ይህ ፓሊስ መርማሪየ አይደለም በተያዝኩበት እለት የተወሰዱብኝ ንብረቶች ሞባይልና ላፕቶፕ አልተመዘገበልኝም በማለት ለችሎት አቅርቦ እንዲመዘገብለት ዳኛው አዟል በቀጠሮው መሠረት ከቀረበ ነገ በ10/2007 ዓም 4:30 ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል

ረቡዕ 13 ሜይ 2015

Ethiopia: Opposition groups claim harassment, detentions ahead of elections

Ethiopia: Opposition groups claim harassment, detentions ahead of elections

Associated Press+ More
By ELIAS MESERET, Associated Press
ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Ethiopian opposition groups are accusing the government of harassing their members and carrying out illegal detentions ahead of the May 24 elections.
Yonathan Tesfaye, spokesman for the Blue Party, told The Associated Press this week that some party members are being beaten, especially in the southern region. He said his party may boycott the elections.
"If the current level of harassment and detention along with the problem in registering our observers continues, we might be forced to consider exiting from the election process," he said.
Chane Kebede, leader of the Ethiopian Democratic Party, also complained of a climate of fear.
"We have now come to the understanding that the ruling party wants a 100 percent control of the government after the upcoming election," he said.
Only one opposition lawmaker won a seat in the country's parliament in the 2010 general elections, which watchdog groups said were marred by intimidation and harassment of opposition activists.
But a spokesman for the ruling party, Desta Tesfaw, dismissed the allegations and accused opposition parties groups of trying to discredit the elections.
"They don't have their own policies and agendas, and that's clear to the Ethiopian people," Tesfaw said, referring to the political opposition. He noted, however, that the ruling party had "taken some measures against our members who were found violating the election code." He did not say what the violations were.
In 2010, the ruling Ethiopian People's Revolutionary Democratic Front, or EPRDF, won 99.6 percent of all parliamentary seats — a victory that Human Rights Watch said was "the culmination of the government's five-year strategy of systematically closing down space for political dissent and independent criticism."
Copyright 2015 The Associated Press. All rights reserved. This material may not be published, broadcast, rewritten or redistributed.

ቅዳሜ 9 ሜይ 2015

የብሄራዊ ደህንነት መረጃ ሃላፊዎች ጥብቅ ፍተሻ እንዲካሄድ አዘዙ

የብሄራዊ ደህንነት መረጃ ሃላፊዎች ጥብቅ ፍተሻ እንዲካሄድ አዘዙ

ሰሞኑን በአዲስ አበባ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አባላት ነን ያሉ ሲቪል የለበሱ ግለሰቦች፣ ከደህንነት መስሪያ ቤት ነው የመጣነው በማለት በየክፍለከተማዎችና ወረዳዎች እየዞሩ፣ ለመንግስት መስሪያ ቤቶችም ሆነ ለግል ተቋማት ሃላፊዎች፣ ” ማንም ሰው ፣ የመንግስት ባለስልጣናም ሆነ መለዮ ለባሽ ወታደር፣ ፖሊስ ወይም ተስተናጋጅ ባለጉዳይ” ሽጉጥን ጨምሮ የትኛውንም አይነት የጦር መሳሪያ ይዘው እንዳይገቡ፣ የመስሪያ ቤት ጠባቂዎች ጥብቅ ፍተሻና ቁጥጥር እንዲያደርጉ” ትእዛዝ አስተላልፈዋል።
እንዲህ አይነት ትእዛዝ ተላልፎ እንደማያውቅ የሚናገሩት ምንጮች፣ ትእዛዙ መጪውን ምርጫ ተከትሎ ረብሻ ሊፈጠር ይችላል ከሚል ስጋት ሳይሆን እንደማይቀር ምንጮች አስተያየታቸውን ቢሰጡም፣ ትእዛዙ በኢህአዴግ ባለስልጣኖች ላይ ሳይቀር መተላለፉ ውሳኔው ከመጪው ምርጫ ጋር ብቻ ያልተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ያመለክታል።
የደህንነት ሰራተኞች ለመስሪያ ቤት ሃላፊዎች ብቻ ሳይሆን ትእዛዙን ለጥበቃ ሃላፊዎችም እየሰበሰቡ በመናገር ላይ ናቸው።