ዓርብ 29 ማርች 2013

ሰመጉ ለአዳራሽ ኪራይ ፈቃድ መጠየቁ ህገ-ወጥ ነው አለ


በመስከረም አያሌው
ሰንደቅ
ሆቴሎች እና ሌሎች የአዳራሽ አከራዮች አገልግሎት ለመስጠት ፈቃድ የሚጠይቁበት ሁኔታ ህገ-ወጥ መሆኑን የሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ) ገለፀ።
የተለያዩ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የሲቪክ ማህበራት በተደጋጋሚ እያቀረቡ ያሉት ቅሬታዎች በተለይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና የደጋፊዎች ስብሰባ ለማካሄድ የአዳራሽ ችግር እየተፈጠረባቸው መሆኑን ያመለክታል ያለው ጉባኤው፣ በአሁኑ ወቅት ሆቴሎች ወይም አዳራሽ አከራዮች በህግ ያልተጠየቀ መስፈርት ተሰብሳቢዎችን ሲጠይቁ የአዲስ አበባ አስተዳደር በበኩሉ ማረጋገጫ ለመስጠት የአዳራሽ ውል ይጠይቃል ብሏል። በዚህ ተያያዥ ምክንያት ስብሰባዎች እየተደናቀፉ መሆኑን የገለፀው ጉባኤው፣ እንዲህ አይነት ከሆቴሎችና አዳራሽ አከራዮች የሚቀርቡት ፈቃድ አምጡ ጥያቄዎች የሚታዩት ፖለቲካዊ ይዘት ባላቸው ስብሰባዎች ላይ ብቻ መሆኑን ተገንዝቤያለሁ ብሏል።
የተለያዩ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የመሰብሰብ እና ሰላማዊ ሰልፍ የመውጣት መብታቸው እየተጣሰ መሆኑን ለጉባኤው በተደጋጋሚ አቤቱታ እያቀረቡ መሆናቸውም ነው የተገለፀው። የባለራዕይ ወጣቶች ማህበር ታህሳስ 11/2005 ባቀረበው አቤቱታ ጠቅላላ ጉባኤውን ለማካሄድ ታህሳስ 5 ቀን 2005 ዓ.ም ለሰሜን ሆቴል ክፍያ የፈፀመ ቢሆንም፣ ሆቴሉ ከመንግስት የስብሰባ ፈቃድ ካለመጣችሁ ውሌን አቋርጫለሁ ሲል ደብዳቤ ፅፏል። ማህበሩም ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስብሰባውን ለማሳወቅ ጥያቄ ቢያቀርብም፣ ስብሰባውን ለማሳወቅ ቦታ እና ጊዜ መግለፅ ስላለባቸው አስተዳደሩ ጥያቄውን ሳያስተናግድ ቀርቷል።
ማህበሩ ስብሰባውን በ21/04/2005 ለማካሄድ በጠየቀው መሰረት የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ቦታ እንዳለ በመግለፅ ቅድሚያ ክፍያ እንዲፈፅመ ገልጾላቸው ነበር። ነገር ግን ክፍያ ሊፈፅሙ በሄዱበት ወቅት የምዝገባ ችግር በመዝገብ ሰራተኛቸው ምክንያት ተፈጥሮ እንደነበር እና ቦታ እንደሌላቸው ገልፀዋል። ሰመጉ ጉዳዩን ባጣራበት ወቅትም ተመሳሳይ ምላሽ ማግኘቱን ገልጿል። ጥያቄውን ያፀደቁት ዳይሬክተር በበኩላቸው ችግሩ የተፈጠረው በምዝገባ ሳይሆን የባለራይ የወጣቶች ማህበር ስብሰባ በሚካሄድበት እለት የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሰራተኞች ስብሰባ ለማድረግ በመፈለጉ ስምምነታቸው እንደተሰረዘ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ በበኩሉ የ2005 ዓ.ም የአካባቢ እና የከተሞች ምርጫ ቅድመ ዝግጅትን አስመልክቶ ከአባላቱ እና ደጋፊዎቹ ጋር ስብሰባ ለማካሄድ ለአዲስ አበባ ከንቲባ ጽ/ቤት የአዳራሽ ጥያቄ አቅርቦ በቃል ተስፋ ተሰጥቶት ነበር። በተገባላቸው ቃል መሰረት የአዳራሽ ኪራይ ጥያቄ ቢያቀርቡም ምክንያቱ ሳይገለፅ ጥያቄው ሳይስተናገድ መቅረቱን ፓርቲው ገልጿል። ሌሎች የስብሰባ አዳራሽ ማፈላለጋቸውን በመቀጠል ለሌሎች የአዳራሽ ባለቤቶች ጥያቄ ቢያቀርቡም፣ የስብሰባ ፈቃድ በፅሁፍ አስቀድማችሁ አምጡ ሲሏቸው የአዲስ አበባ ፈቃድ ሰጭ አካል በበኩሉ የስብሰባ አዳራሽ ፈቃድ ውል አምጡ በማለት በቅብብሎሽ ህገ-መንግስታዊ መብታችን ተጥሷል ሲል አቤቱታ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት (መድረክ) እና ሰማያዊ ፓርቲም ህገ-መንግስታዊ የመሰብሰብ መብታችንን ተነፍገናል ሲሉ በሰመጉ ጥያቄ ያቀረቡ ፓርቲዎች ናቸው። የስድስት ፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ ድርጅት የሆነው መድረክ በህዳር 18 ቀን 2004 ዓ.ም የወጣውን “የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ አዋጅ” አስመልክቶ ህዝባዊ ስብሰባ ለማካሄድ ከሙገር ሲሚንቶ ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና ኢንተርፕራይዝ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ጋር በአዳራሽ ኪራይ ስምምነት ፈፅሞ መጋቢት 15 ቀን 2004 ዓ.ም ክፍያ መፈፀሙ በማህበሩ የገንዘብ ደረሰኝ ቁጥር 22988 ተረጋግጧል። ስምምነቱን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላማዊ ሰልፍ እና ስብሰባ ማሳወቂያ ቢሮ በማቅረብ መጋቢት 19 ቀን 2004 ዓ.ም ከአስተዳደሩ የማሳወቂያ ማረጋገጫ ደብዳቤ ተሰጥቶታል። ሆኖም በስብሰባው እለት በሙገር ሲሚንቶ አዳራሽ ሲደርሱ ውሉ መሰረዙ ተነግሯቸዋል።
መድረክ በመቀጠል ያመራው ወደ ኮልፌ ቀራኒዮ ወጣቶች ማእከል ሲሆን፣ ግንቦት 1 ቀን 2004 ዓ.ም ለማእከሉ በደብዳቤ የአዳራሽ ጥያቄ አቅርቦ ማእከሉም ከመንግስት የስብሰባ ፈቃድ እንዲያመጣ ተነግሮታል። መድረክ ወደ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አምርቶ ጥያቄውን ሲያቀርብ የስብሰባ ቦታውን ማሳወቅ አለባችሁ መባሉን እና በዚህም ምክንያት ከማዕከሉ ጋር ስምምነት ሳይፈፅሙ መቅረታቸውን የመድረክ ጉዳይ አስፈፃሚ አቶ ወንደሰን ክንፈ ለሰመጉ ገልፀዋል።
ሰማያዊ ፓርቲ በበኩሉ የካቲት 30 ቀን 2005 ዓ.ም በዋቢሸበሌ ሆቴል የገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ምሽት ጠርቶ ከሆቴሉ ጋር ሁሉንም ስምምነት እና ክፍያ ቢፈፅምም፣ ዝግጅቱ ተጠናቆ ታዳሚው ወደ ሆቴሉ በመግባት ላይ እያለ የሆቴሉ አስተዳደር በድንገት ከአቅሜ በላይ በሆነ ምክንያት ዝግጅታችሁን ማድረግ አትችሉም በማለት ምክንያቱንም ለመናገር እንደማይችሉ በመግለፅ የተሰበሰበው ህዝብ ሊበተን መቻሉን ገልጿል።
እነዚህ ድርጊቶች በህገ-መንግስቱ የሰፈሩት መብቶች እና ሌሎች ሰብአዊ መብቶች ብቻም ሳይሆን መብቶቻቸውን በማጣታቸው የሚያደርጉት ተቃውሞም አብሮ የሚያፍን መሆኑን ያስረዳል ያለው ሰመጉ፤ እንዲህ አይነቶቹ ጫናዎች ከበስተኋላ የሚደረግ አሉታዊ ጫና እንዳለባቸው አመልካች ነው ብሏል።
ከፖለቲካ ፓርቲዎች የመሰብሰብ መብት በተጨማሪም ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት ጥሰትም እየተፈፀመ መሆኑን የገለፀው ሰመጉ፤ ለማሳያም ባለፈው መጋቢት 8 ቀን 2005 ዓ.ም የተከሰተውን ክስተት አንስቷል። የባለራዕይ ወጣቶች ማህበር፣ ሰማያዊ ፓርቲ እና ሌሎች አካላት በኢጣሊያ አፊል ከተማ ፊልድ ማርሻል ሩዶልፍ ግራዚያኒ ሙዚየም መገንባቱን እና በስሙም መናፈሻ መከፈቱን ተመልክቶ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰልፍና ህዝባዊ ስብሰባ ማሳወቂያ ቢሮ የካቲት 25 ቀን 2005 ዓ.ም ደብዳቤ አስገብተዋል። መጋቢት 7 ቀን 2005 የባለራእይ ወጣቶች ማህበር ስምንት አባላት በመኪና እየተንቀሳቀሱ ጥሪ ሲያደርጉ በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል። እነዚህ ወጣቶች በራስ ደስታ፣ ጃን ሜዳ እና አራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ታስረው ክስ ሳይመሰረትባቸው ከሁለት ቀናት በኋላ ተለቀዋል። ሰልፉ በሚካሄድበት መጋቢት 8 ቀን 2005 ዓ.ም ስድስት ኪሎ በተሰበሰቡበት አንድ ሲቪል የለበሰ የመንግስት የፀጥታ ሰራተኛ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ አትችሉም ማለቱን እና እነ ዶ/ር ያዕቆብ ሀይለማርያምን ጨምሮ ሌሎች በፖሊስ መኪና ወደ አራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ተወስደው ታስረው ከአንድ ቀን በኋላ በዋስ መፈታታቸውን ሰመጉ ገልጿል። በመሆኑም እነዚህን ዜጎች ለእስራት እና ለድብደባ የዳረጉት አካላት ተጣርተው አጥፊዎቹም ህግ ፊት እንዲቀርቡ ጠይቋል።

Global internet slows after 'biggest attack in history'


The internet around the world has been slowed down in what security experts are describing as the biggest cyber-attack of its kind in history.
A row between a spam-fighting group and hosting firm has sparked retaliation attacks affecting the wider internet.
It is having an impact on popular services like Netflix - and experts worry it could escalate to affect banking and email systems.
Five national cyber-police-forces are investigating the attacks.
Spamhaus, a group based in both London and Geneva, is a non-profit organisation that aims to help email providers filter out spam and other unwanted content.
To do this, the group maintains a number of blocklists - a database of servers known to be being used for malicious purposes.
Recently, Spamhaus blocked servers maintained by Cyberbunker, a Dutch web host that states it will host anything with the exception of child pornography or terrorism-related material.
Sven Olaf Kamphuis, who claims to be a spokesman for Cyberbunker, said, in a message, that Spamhaus was abusing its position, and should not be allowed to decide "what goes and does not go on the internet".
Spamhaus has alleged that Cyberbunker, in cooperation with "criminal gangs" from Eastern Europe and Russia, is behind the attack.

አቶ ሃይለማርያም ያላቸውን ሃይል ተጠቅመው የወሳኝነት ሚና እንዲጫወቱ ግፊት እየተደረገ ነው/ወያኔዎች ተደናግጠዋል!!



አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በተከፈተው በር ሰተት ብለው መግባት አለባቸው:: በወያኔ ውስጥ የተደረገውን የስልጣን ሽግሽግ ተከትሎ አዳዲስ ለውጦች እየታዩ ሲሆን የአቶ ሃይለማርያም የበላይነት ጎልቶ ለመውጣት እያቆበቆበ መሆኑን ከ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ አከባቢ የተገኙ መረጃዎች ሲጠቁሙ ከአከባቢው የህወሃት አክራሪዎች መወገድ እና የአቶ ደብረጺሆን የግለኝነት አትኩሮት ለአቶ ሃይለማርያም እድሉን ገርበብ አድርጎ የከፈተላቸው ሲሆን የአቶ ደብረጺሆን ግለኝነት በሙስና ስም ሊደፈቅ እንደሚችል ያከባቢው ገማቾች ሲናገሩ ወታደራዊው አካል ራሱን ለማዳን ሲል በተጠንቀቅ ከሃይለማሪያም አዲስ ካበበው ቡድን ጋር እንደሚሰለፍ አንዳንድ ፍንጮች ታይተዋል:: አቶ ሃይለማርያም በሙሉ መንፈስ ባይሆኑም ድፍረት እንዳገኙ ከደቡብ ጉባዬ በሁዋላ እየታየ ሲሆን የደቡብ ባለስልጣናት አንድነት ወያኔን አስደንግጦታል::
የሕወሓት የቀድሞ ታጋዮች የአሁን ባለስልጣናት በአቶ ሃይለማርያም ዙሪያ ጥያቄ በማንሳት ላይ ቢሆኑን በባህር ዳር በተደረገው ጉባዬ ላይ ያላቸውን የበላይነት እንዲያሳዩ ከፓርቲያቸው ግፊት እንደተደረገባቸው ምንጮች ጠቁመዋል::የደቡብ ባለስልጣናት አብዛኛዎቹ በግል አቶ ሃይለማርያምን በደቡቡ ጉባዬ ወቅን አግኝተው ያናገሯቸው ሲሆን በአንድነት ራሳቸውን ችለው እንዲወጡ እና ከሕወሓት የበላይነት እንዲላቀቁ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው መክረዋል::ለዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚረዳቸው ከወቅታዊ ጉዳዮች ጋር አስታከው ተወያይተውል::
በህወሓት ውስጥ ያለው ፍትጊያ በአባይ ወልዱ የበላይነት ያበቃ ነው ብለን መደምደም እንደማንችል እና መሃል ሰፋሪ ሆነው ወዳሸናፊው ለማዘንበል የግለኝነት ሚና እየተጫወቱ ያሉት ደብረጺሆን ደቡቦችን አመቻችቶ መያዝ አስፈላጊ እንደሆን ስለተረዱት በሃይለማርያም ድፍረት ጀርባ ሆነው ጨዋታውን ማጋጋል ተይይዘውታል::
ምንጮቹ በአከባቢያቸው ያለውን ሁኔታ በማየት እንዳሉት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በሃይለቃል ጭምር የሚደፋፈራቸው የደህንነት አማካሪው አለቃ ጸጋይ ከፓርቲው መነሳቱን ተከትሎ በደብረጺሆን ተዘዋዋሪ ቁጥጥር ስር መሆኑን ከጠ/ሚ ቢሮ የተገኙ መረጃዎች ሲጠቁሙ እንደት ከስልጣን እንደሚባረር ታቅዶለታል::
በስበሃት ነጋ የሚመራው ቡድን የቀድሞ ታጋይ የነበሩት እና በአሁን ሰአት በስልጣን ላይ ያሉ ሰዎች በማሰባሰብ በአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ላይ ጥያቄዎችን እንዲያነሱ እና ከሕወሓት ሰው ጠፍቶ ነው ወይ ከደቡብ ለትግሉ አስታውጾ ያላበረከቱ ሰዎች የሚመሩን ነገ ስጋት ሆኖብናል የሚሉ ታጋዮች ይህን ፕሮፓጋንዳ ይዘው በአቶ ስበሃት በኩል መሰለፋቸው በዚህ ሰሞን እንደገና ተረጋግቷል የተባለውን የወያኔ ክፍፍል እንደ አዲስ አግሎታል::

የሃይለማርያም ስልጣን መያዝ ያልጣማቸው አክራሪ ሕወሓቶች ከባህር ዳር መልስ አዲስ አበባ ውስጥ በስበሃት ነጋ ሰብሳቢነት  አርከበ እቁባይ ;ብርሃነ ገብረክርስቶስ ;አዲሳለም ባሌማ;አባዲ ዘሙ ;አለቃ ጸጋይ በርሄ; ቅዱሳን ነጋ; ሃይለኪሮስ እና ሌሎችም ተሰባሰበው በህወሃት ውስጥ ስለለው ሁኔታ እና ራሳችን በፈጠርናቸው ደቡቦች ልንዋጥ ነው የሚል እደምታ ያለው ውይይት አካሂደው ነበር:;
በአንድ ወገን ሆነው በአባይ ወልዱ መሪነት ብኣዴንን አስከትለው የስብሃትን ቡድን እየተዋጉ የሚገኙት አዜብ መስፍን እና ሌሎች..ሳሞራ የኑስን እንደመከታ አድርገው ቢተሙም ሳሞራ ሁኔታዎችን ከመከታተል ዉች ተሳትፎው የተልፈሰፈሰ መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል::
የደቡብ ባለስልጣናት ወይም በስበሃት አጠራር የከተማ ጮሌዎች ወደ ከፍተኛ የስልጣን እርከን መምጣታቸው እያንገበገባቸው ሲሆን መለስ ዜናዊ ላልሰለጠኑ አናሳ ብሄሮች ሸጠን በማለት በሟቹ ላይ ከንፈር ነክሰው እየሞገቱ ሲሆን ይህም አልበቃ ብሎ ከድርጅታችንን መመሪያ እና ደንብ ዉጭ በተለያየ ቦታ የመለስን ምስል ማየት ሰለቸን በሚል ምስሉ እንዲነሳ ግፊት ሲያደርጉ ቆይተዋል ምናልባት ሁኔታዎችን ያረግብ ይሆናል በሚል አቶ አዲሱ ምስሉ እንዲነሳ ቢናገሩም አቶ በረከት ጠላት እና ወዳጅን አጥርቶ ለመለየት በሚል እንዲቆይ አድርገዋል..
የስበሃት ቡድን ዉስጥ ውስጡን በትግራይ ለሚገኙ የሕወሓት የበታች አመራሮች እንዲሁም በሰራዊቱ ውስጥ ለሚገኙ የህወሓት መኮንኖች በሚያሰራጩት ፕሮፓጋንዳ በበረሃ ወንድም እና እህት ታጋዮችን ሰውተን ደማችንን አፍሠን የልጅነት ወዛችንን ጨርሰን ለዚህ የደረስነው ለደቡብ  ሰዎች እና ለከተማ ጮሌዎች ስልጣን ለመስጠት አይደለም አብረውን የታገሉ ኦሆዴዶች እንኳን ያላገኙትን ስልጣን ነው ያገኙት በማለት እና ለነገ የፖለቲካ ኪሳራ ያመጡብናል የሚያዘነብሉት ወደ ሌላው የኢትዮጵያ ክፍል ነው ለኛ አደጋ ስለሆኑ ከአሁኑ ልናሶግዳቸው ይገባል   በማለታቸው የወያኔ የውስጥ ቀውስ ግሎ ይገኛል::

በአሁን ሰኣት የደህንነት መዋቅሩን እና የጦር ሰራዊቱ ባለስልጣናት አጣብቂኝ ውስጥ ለማስገባት እየሰሩ የሚገኙት ደብረጺሆን አቶ ሃይለማርያም ያላቸውን ሃይል ተጠቅመው የወሳኝነት ሚና እንዲጫወቱ እያደፋፈሯቸው ሲሆን ከጎናቸው እንደሚሆኑ እና ምንም እንደማይመጣ እየመከሯቸው ሲሆን ለሁለት አመት ነው ያስቀመጥንህ የሚለውን የአለቃ ጸጋይ ዛቻ ከአሁን በኋላ ሰሚ የሌለው ጩሀት እንደሆነ መናገራቸውን ምንጮቹ አስቀምጠዋል::
የደቡብ ባለስልጣናት ማሰብ/ድፍረት መጀመር; የህወሃት ክፍፍል መጋል; የኦህዲድ አህያዊ ሞኝነት; የብኣዴን በዝምታ ነገሮችን መከታተል; የኢሕኣዴግ ባልተጠበቀ መልኩ ቀውስ ውስጥ መግባት እና ሌሎች ተደማምረው የወያኔን ውድቀት የሚያመላክቱ ሲሆን በሃገሪቷ ላይ የፖለቲካ ለውጥ እንዲኖር ለማየት የሚጓጓውን ህዝብ ስል ነቀል ለውጥ እንዲያደርግ መስራት ደሞ የእያንዳንዳችን ሃላፊነት ነው::

በኢትዮጵያዊያን ተወረናል መንግስትና የፀጥታው ክፍል ለምን ዝም ይላል!!!

በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሳውድ አረቢያ የሚገቡ ኢትዮጲያዊያን የሳዑዲን አንድነት ለማፈራረስ እና ፀጥታ ለመንሳት የመጡ ስለሆኑ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድባቸው በማለት የሃገሪቱ ጋዜጦች ግፊት እያደረጉ መሆኑ ተገለፀ፡፡


ባለፈው ማርች 5 እና 6 ብቻ እንኳን በ16 እለታዊ ጋዜጦች 24 ጊዜ ሽፋን የሰጠው በኢትዮጵያዊያን ተወረናል መንግስትና የፀጥታው ክፍል ለምን ዝም ይላል የሚል ጩኻት በየዕለቱ ከ120 እስከ 160 ሺህ ኮፒ ሽፋን እንደነበረው የገለፁት መረጃዎች ሣውዲ ዓረቢያን በቀይ ባህር በኩል ለመምታት የሃበሻን ስደተኞች አስታጥቆ እየላከ ነው የሚል ስጋት እንዳላቸው አስነብበዋል፡፡

የሣዑዲ ዐረቢያ የድንበር ጠባቂ ሃይል ባወጣው መረጃ በአንድ አመት ብቻ 330 ሺ ኢትጵያዊያን በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ሳውዲ የገቡ ሲሆን 5ሺ እነዚህን ግለሰቦች በኮንትሮባንድ የሚያንቀሳቅሱም ተይዘዋል ይላል፡፡
146 ሺ 546 ጥይት 1468 ክላሺንኮቭ ጠመንጃ 646 የውስኪ ጠርሙስ 3 ሚሊየን 964 ሺ 298 ኪ.ግ ሜትር እንዲሁም 15 ሺ ኪ.ግ ሃሺሽ ተገኝቷል የሚለው የድንበር ጠባቂ ሃይል መረጃ በተጨማሪም 2 ሚሊየን 652 ሺ የሳዑዲ ሪያል በካሽ እና 15ሺ 315 ኪ.ግ ሺሻ ተገኝቷል በማለት አስረድተዋል ፡፡

በታዋቂው የሳዑዲ አረቢያ አል መዲና ጋዜጣ ላይም ሀበሾች ሣዑዲ ሲመጡ ዝም ብለው ሳይሆን ዓላማና እቅድ አላቸው ብሎ መፃፍ ያስቆጣቸው የሳዑዲ ዜጎች የመንግስት አካላት በአንድ ጊዜ ተባብረው አንድ ወር ባላሞላ ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያዊያንን ጠራርገው እንዲያስወጡ አስተያየት እየሰጡ ነው፡፡