ማክሰኞ 9 ጁላይ 2013

አቶ ድሪባ ኩማ የአዲስ አበባ ከንቲባ ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲሱ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ዛሬ በይፋ ተመስርቶ ስራውን ጀምሯል።

ምክር ቤቱ ዶክተር ታቦር ገብረመድህንን በአፈ ጉባኤነትና አቶ ወልደገብርኤል አብረሃን ደግሞ በምክትል ከንቲባነት መርጧል ።

ምክር ቤቱ በከንቲባነትም አቶ ድሪባ ኩማን ሾሟል።

አዲሱ ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ለምክር ቤቱ የካቢኒ አባላቶቻቸውን በማቅረብ አስፀድቀዋል ።

በዚህም መሰረት

አቶ አባተ ስጦታው ምክትል ከንቲባ

አቶ ሀይሌ ፍሰሃ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ አስኪያጅ

አቶ ይስሃቅ ግርማይ የአቅም ግንባታ ቢሮ ሀላፊ

አቶ ጌታቸው ሀይለማርያም የኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ቢሮ ሀላፊ

አቶ ጥላሁ ወርቁ የጥቃቅንና አነስተኛ ቢሮ ሀላፊ

አቶ ገብረ ፃዲቅ ሀጎስ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ

ወይዘሮ ብዙነሽ መሰረት የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ

አቶ ኤፍሬም ግዛው የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ

አቶ ሺሰማ ገብረስላሴ የንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ

አቶ ፎርኢኖ ፎላ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ሀላፊ

አቶ ሰለሞን ሀይሌ የመሬት ማኔጅመንትና ልማት ቢሮ ሀላፊ

አቶ ዲላሞ ኦቶሬ የትምህርት ቢሮ ሀላፊ

አቶ ፀጋዬ ሀይለማርያም የፍትህ ቢሮ ሀላፊ

ወይዘሮ ፍሬህይወት አያሌው የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ በመሆን ተሹመዋል ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ