ሰኞ 12 ሜይ 2014

መኢአድ ሳዉላ

መኢአድ ሳዉላ የተቃዉሞ ሰልፍ

 መኢአድ ሳዉላ
የተቃዉሞ ሰልፍ
ከ30000 ህዝብ በላይ በተቃዉሞ ሰልፍ ተገኝቶል፡፡
ፖሊስ እና የወያኔ ደህንነት ከፍተኛ ግፍ ፈጥሞል፡፡
የመኢአድ አመራሮች ኪሳቸዉ ሳይቀር ተፈተሸ፡፡
ደቡብ ኦሞ የትጥቅ ትግል ተጠናክሮል፡፡
የነፍጠኛዉ ቤዝ ደቡብ ነዉ ተባለ፡፡
ሰልፉ ከፍተኛ መሰዋትነት ተከፍሎበት በድል ተጠናቆል፡፡
ወያኔ የሞት ሞቱን ተፍጨርጨር፡፡
ሰላማዊ እንቢተኝነት በተግባር ዋለ፡፡
ቪዲወ እንለቃለን
ኔትዎርክ ሙሉ በሙሉ በሳዉላ ከተማ አልነበረም፡፡
ከምሽቱ 4 ሰዓት የመኢአድ አመራሮች ወላይታ ሶዶ ገቡ፡፡

 

ቅዳሜ 3 ሜይ 2014

Ethiopia: John Kerry raised concerns over the detention of bloggers

Ethiopia growth strains expose political fault-lines

US Secretary of State John Kerry yesterday raised concerns with the Ethiopian government about the detention in the past week of several journalists and bloggers. A number of opposition Blue Party members were also arrested last week ahead of a planned demonstration. US and other donor influence on the question of media freedom and repression of opposition is fairly limited, despite Ethiopia’s dependence on foreign aid. Nevertheless, the recent clampdown — coming amid a wave of protests by students at universities in the Oromo regional state against the pace of the capital city Addis Ababa’s expansion — highlights tensions created or exacerbated by the aggressive growth policies of the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF).

Secretary Kerry Speaks During News Conference in Ethiopia

በሰፊው የኦሮሞ ህዝብ እና ልጆች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ በአጽንኦት እናወግዛለን!!! ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በኢትዮጵያ የመሬት ስሪት ላይ ግልፅ አቋም እና ፖሊሲ ያለው ፓርቲ መሆኑ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ በዚህም መሰረት መሬት በሦስት መሰረታዊ አውድ ላይ እንዲመሰረት ይህም ማለት በወል፣ በመንግስትና በግል ይዞታነት እንዲከበር አቋም ይዞ ይታገላል፡፡ ነገር ግን ከወልና ከመንግስት ውክልና ውጪ ያሉት ይዞታዎች በግል ይዞታነት እንዲከበሩ አቋም ይዞ ይታገላል፡፡ ኢህአዴግ የገጠሩ መሬት የግል ከሆነ አርሶ አደሩ መሬቱን እየሸጠ ወደ ከተማ ይፈልሳል ብሎ ያምናል፡፡ ከምንም የተነሳ ስጋት ነው ባይባልም አንኳ ኢትዮጵያውያን ከመሬት ጋር ያለንን ስነልቡናዊ፣ ማህበራዊና ሁለንተናዊ መስተጋብርን ያላገናዘበና የተጋነነ ስጋት ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ከመሬት ጋር የተለየ ቁርኚት እንዳላቸሰው ለማወቅ ሞታቸውን ሲያስቡ እንኳ “የሀገሬ አፈር ይብላኝ” ሲሉ መመኘታቸው በቂ ማስረጃ ነው፡፡UDJ/Andinet party logo
ኢህአዴጎቹም በቀድሞ ስርዓት ሲተገበር የታገሉትን የመጨቆኛ መሳሪያ ለራሳቸው ሲሆን ተጠቀሙበት፡፡ የሆኖ ሆኖ ይህ የኢህአዴግ ስጋት እውነት ነው እንኳ ቢባል ኢህአዴግ የከተማውን መሬትስ የግል ይዞታ ያላረገው ከተሜው ወዴት እንዳይሰደድ ነው? ዋናው የገዥው ፓርቲ ፍላጎት መሬትን በጁ በማድረግ የዜጎችን ነፃነት በዚያኑ ያክል ለመሸበብ ነው፡፡ አርሶ አደሩም ሆነ የከተማው ህዝብ መሬት የኔ ነው ብሎ ካመነ ለኢህአዴግ ጫና ስለማያጎበድድ መያዣ ለማድረግ ነው፡፡ የህዝቡ የመሬት ባለቤትነት ቢረጋገጥ በመንግስትና ለኢንቨስትመንት በሚፈለጉ መሬቶች ላይ የመደራደር አቅሙ እጅግ ከፍ ይላል፡፡ መሬቱን በመልቀቁ በሚሰጠው ካሳ (ዋጋም) በቂ የኑሮ ዘዬ ሽግግር የሚያገርግበት አጋጣሚ ይፈጥራል፡፡ ይህ ሊሆን አልቻለም፡፡ በ02/ 08/ 06 ዓ.ም ቡራዩ አካባቢ በተደረገ የመሬት የሊዝ ጨረታ ለተነሺው አርሶ አደር በካሬ 10 ብር የታሰበለት መሬት በጨረታ በካሬ 17 ሺህ ብር መሸጡን ፓርቲያችን ያሰባሰበው ማስረጃ ያሳያል፡፡ በ10 ብር የታሰበለት አርሶ አደር የሚሰደደው በዚህ መልኩ መንግስት ሲቀማው እንጂ የመሬቱ ባለቤት ሆኖና ተደራድሮ በሚሸጥበት ወቅት አልነበረም፡፡
መሬት የምርጫ ድምፅ መያዣ፣ ለኢህአዴግ ገንዘብ ማሰባሰቢያ እና የድጋፍ ምንጭ ሆኗል፡፡ በቅርቡ በጉጂ ዞን ኦዶ ጉዶ አካባቢ ለ2007 ዓ.ም ምርጫ ሞዴል የተባሉ አርሶ አደሮች በቁጥር ከፍ እንዲሉ እንደሹመት ተሰጥቷቸው ሲያበቃ 500 ብር እንዲያዋጡ የመሬት ይዞታቸው ለማስፈራሪያነት መዋሉ እንደማሳያ ሊወሰድ ይችላል፡፡
በሌላ በኩል ምንም አይነት ህዝባዊ ውይይት ሳይደረግበት ከሰማይ ዱብ ያለው የአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የልማት መሪ ፕላን ያስቆጣቸው የኦሮሞ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሰልፍ በማድረጋቸው የደረሰባቸውን ህገ ወጥ ድብደባና እስራት አንድነት በእጅጉ ይቃወማል፡፡ ለእውነተኛ ልማት ነው እንኳ ተብሎ ቢታሰብ ኢህአዴግ ካለበት የተአማኒነት ችግር የተነሳ ተማሪዎቹ ለተቃውሞ አደባባይ ቢወጡ ተፈጥሯዊ እና ህገ መንግስታዊ መብታቸው ሊከበር በተገባ ነበር፡፡ ነገር ግን ሁሉን ነገር ካልጋትኳችሁ የሚለውና ለዴሞክራሲያዊ ሽንፈት የማይገዛው ኢህአዴግ በተማሪዎቹ ላይ ያደረሰውን እንቃወማለን፡፡ የታሰሩ ተማሪዎችም በአስቸኳይ እንዲፈቱም እንጠይቃለን፡፡ የኦሮሞ ተማሪዎችን በገፍ ከዩኒቨርሲቲ የትምህር ገበታቸው በማባረር የሚታወቀው የኢህአዴግ መንግስት ከዚህ ተደጋጋሚ ተግባሩ ታቅቦ ልጆቹን በአስቸኳይ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመልስ እንጠይቃለን፡፡
በአጠቃላይ መሬት የዜጎች መያዣ መሆኑ እንዲቀር እንታገላለን፡፡ ዜጎች በመሬታቸው የመደራደር እውነተኛ መብት ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ተቃውሞ የሚያነሱ ዜጎችም ድምፅ እንዲሰማ እናሳስባለን፡፡
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ
ሚያዚያ 22 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ

ወያኔ የሚፈራው ምርጫ ወይስ ሕዝባዊ እምቢተኝነት (አመጽ)


በዚች አለም በሕዝቦቻቸው ላይ የሚፈነጩ አምባገነኖችን ለማስወገድ የሚደረጉ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ የወያኔ ዘረኛችን ለምን ሲያስደነብራቸውና በፍርሃት ሲያሸማቅቃቸው እንደሚኖር የሁሉም ሰው ጥያቄ ነው፡፡ የህውሃት ዘረኛ ቡድን በሕዝብና በሃገር ላይ የሚያደርሰው መጠነ ሰፊ ጥቃት ወይም ውድመት በተለያየ መንገድ ሕዝቡ ቅሬታውን ቢያሰማም እራሱ ለፈጠረው ዘርፈ ብዙ ችግር መፍትሄ ከመሻት ይልቅ የሕዝቡን ብሶት ለማዳፈን ሀላፊነት የጎደለው ተግባራትን እየፈፀመ ሃገርን የመበተን ስራውን ቀጥሎበታል፡፡The long youth march to freedom and dignity has begun in Ethiopia. It is beautiful.
በአዋጅ የተደነገጉ የሕዝብን አሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመደራጀትና የመሰብሰብ እንዲሁም ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብትን እየሸረሸሩና አዋጅን በተራ መመሪያ እየሻሩ የስቃይ ቀንበሩን ያከብዱበታል ፡፡በየትኛውም ሁኔታ ማለትም የሰብአዊ መብቱ የተረገጠውን፣ የሃገሬ ጉዳይ ያገባኛል ስላለ እንደ ሁለተኛ ዜጋ እየታየ የሚሰቃየውን የነፃነት ታጋይ፣ በስርዓቱ ብልሹና የተዝረከረከ አሰራር በኑሮ ውድነት እየማቀቀ ያለው የህብረተሰብ ክፍል ለጥያቄው ተገቢውን መልስ ወይ መፈትሄ ከመስጠት ይልቅ በተራ ካድሬያዊ ዲስኩር ከላይ ለዘረኛው ስርዓት ቃል አቀባይ ከሆነው ጠ/ሚ ተብዬው እስከ ልማታዊ ጋዜጠኛ ነን እስከሚሉት ድረስ በርሃብ ለጠወለገው ምስኪን ሕዝብ ጥጋብን፣ በገዛ ሃገሩ ፍትህ አጥቶ ለሚሰቃየው ፍትሃዊነትን እንዲሁም ሰብአዊ መብቱ ተገፎ ነፃነቱን ለተነጠቀው ሕዝብ ዴሞክራሲን ነጋ ጠባ ይሰብኩታል፡፡
ይህው የወያኔ ዘረኛ ቡድን ስለፈጠረው ሃገራዊ ቀውስ ብዙ ብዙ ቢባልም የዚህን መርዘኛ ስርዓት ሰንኮፍ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነቅሎ ለመጣል ከምርጫ ይልቅ ሕዝባዊ እምቢተኝነት(አመጽ) ስለመሆኑ ስርዓቱ በሚያሳየውና ከሚሰጋባቸው ነገሮች ለመረዳት ይቻላል፡፡
እንደሚታወቀው በተደጋጋሚ የተካሄዱት ምርጫዎች ከምርጫ 97 ውጪ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለወያኔ መሳሪያ ከመሆን ወጪ የስርዓቱ የአፈና መዋቅር ተቃዋሚዎችን የሚያወላዳ አልነበረም፡፡ ይህ ማለት ይካሄዱ የነበሩ ምርጫዎች በህውሃት ዘረኛ ቡድን በተጠና የአፈና እንዲሁም በዋነኝነት ምርጫን ምርጫ ሊያሰኙ የሚችሉ ገለልተኛ ተቋማት በጠቅላላ በስርዓቱ መዋቅር የተዋጡና የተተበተቡ በመሆናቸው ለመገናኛ በዙሃን ሸፋንና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ መደለያ ካልሆነ በስተቀር ምርጫው ሳይጀመር ውጤቱ የታወቅ እንደ ነበር ከማንም የተሰወረ አደለም፡፡ ስለሆነም የህውሃት ቡድን አምስት አመት ጠብቆ የሚመጣ ምርጫ ከላይ እንደተጠቀሰው ለአንዳንድ ግብአት ይጠቀምበት እንደሆን እንጂ ምርጫ ስለተቃረበ እንቅልፍ የሚያጣ አይመስልም ምክንያቱም የምርጫ አስፈጻሚ አካላት እስከ ፍትህ ስርዓቱ በእጁ ናቸውና፡፡
የልቁንም ለዚህ እኩይ ስርዓት የራስ ምታት የሚሆንበትና ሰላም የሚነሳው ሕዝባዊ እምቢተኝነት(አመጽ) ነው፡፡ በቃ የሚል ትውልድ ግፍና በደል ያንገሸገሸው ሕዝብ ለመሆኑ ማሳያ ይሆኑ ዘንድ አንዳንድ ነጥቦች እናንሳ፡፡
ከአመታት በፊት ቱኒዚያዊው ሙሃመድ ቡዋዚዝ የቢን አሊን አንባገነን መንግስት በሃገሩ በቱኒዚያና በሕዝቧ ላይ የሚያሳደረውን ዘርፈ ብዙ ችግር በመቃወም እራሱ ላይ ነዳጅ አርከፍክፎ ካቃጠለ በሗላ ቱኒዝያን ጨምሮ ሊቢያ፣ ግብጽ፣ የመን፣ እስካሁንም በነወጥ ውስጥ ያለች ሶሪያ የደረሰውን ሕዝባዊ እምቢተኝንትና በየሃገሩ የተለኮሰው አመጽ የወያኔን ዘረኛ ቡድን ያስፈራውና ያሸማቀቀውን ያህል አምስት አመት ጠበቆ የሚካሄደው የየስሙላ ምርጫ አላሸበረውም፡፡
ይህንንም ለመገንዘብ በዛን ወቅት ሟቹ መለስ ዜናዊ የወሰዳቸውን እርምጃዎች ማየት የበቃል፡፡ በመጀመሪያ የአረብን አለም አብዮት የሚዘገቡ አለም አቀፍ የመገናኛ ቡዙሃንን ማፈር ቀዳሚ ተግባሩ ነበር ሆኖም መረጃው በተለያየ መንገድ ሕዝብ ጋር መድረሱን የተረዳው ሟቹ ጠ/ሚንስትር የሕዝብን መንፈስ ለመሳብና ቤሔራዊ ስሜትን ሰቅጦ ይይዝልኛል ያለውን መላ ምቱ ዘየደ ባይሳካም ኤርትራን ለመውረር መዘጋጀቱን ማወጅ ነበር፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው አብዮቱ የኢትዮጲያንም በር እንዳያንኳኳ ካለው ከልክ ያለፍ ፍርሃት ነበር፡፡ ሆኖም ሕዝብ ኖሮውን እንጂ የወረራ ዲስኩር ችላ እንዳልው ሲረዳ በኤኮኖሚም በፖለቲካ እንዲሁም ሃገራችን ያላትን መልካም የውጪ ገንኙነት የላገናዘበ በተጨማሪም በባለሞያዎች በቃ ጥናትና ምርምር ያልተደረገበትን እስካሁንም ዘርፈ ብዙ ችግር አዝሎ የሕዝብ ኪስ የራቆተውን የአባይ ግድብን እንካችሁ ብሎ ሻማ አለን፡፡ የሟቹን አላማ ይህኛው በተወሰነ መጠን አሳካለት ሆኖም አብዮት የፈራው ወይም ሕዝባዊ እምቢተኝነትን የፈራው የህውሃት ዘረኛ ቡድን የማይገፋ እዳ ለሃገርን ለሕዝብ ትቶ ችግሩን ፍርሃቱ ፈታበት፡፡
በተጨማሪ ይህው ዘርኛ ቡድን በአለም ዙሪያ የተደረጉ የተሳካላቸው ምርጫዎችን እያነሳ የሰጋበት ግዜ አይታወስም፡፡ በአንጻሩ ምርጫ ያጭበረበሩ አምባገነኖችን ሕዝብ ሲቃወምና ድምጹን ለማስመለስ የሚያደርገውን የነፃነት ትግል አሉታዊ መልክ ሰጥቶ ባዘጋጃቸው የፖለቲካ ተንታኝ ተብዬዎች ውግዝ ከማርዮሰ ሲያስብላቸው ይውላል፡፡ በየትኛውም መልኩ የሚካሄዱ ሕዝባዊ እቢተኝነት(አመጽ) ከማውገዝ ወደ ሗላ ብሎ የማያቀው ይህ ስርዓት ሰሞኑን ዘጋቢ ፊልም መስራት በማይሰለቻቸው ልማታዊ ጋዜጠኞቹ ይቀርብ የነበረው የዚሁ የፍርሀትና እራሱን እየከፈነ ያለው ያበቃለት የህውሃት ዘረኛ ቡድን ቅዠት ነው፡፡
ቅዠቱ የቀለም አብዮት ይልና ከብርቱካናማው የዩክሬን አብዮት ጀምሮ ቬንዙዌላ የድርሳል አጠቃላይ ምልከታው አብዮት ወይም ሕዝባዊ እምቢተኝነት የሚከናወነው ሕዝብ ፈልጎት ሳይሆን ከምዕራባዊያን እዲሁም በምዕራባዊያን ሃገራት ከሚኖሩ ዜጎች ፈላጊነት የሚመነጭ ነው ይለናል ኸረ እንደውም እነዚሁ ምዕባዊያን የማይፈልጓቸውን መንግስታት የሚያሶግዱበት አንዱ መሳሪያ ሕዝባዊ አመፅ ነው በማለት ይቀጥላል፡፡ ሌላው የሚገርመው የ 97 ምርጫን ተከትሎ ሕዝብ የተቀማ ድምጹን ለማሰመለስ ያደረገውን እንቅስቃሴና ንጹሃን ወገኖቻችንን በዚሁ ዘረኛ ቡድን የተነጠቅንበት ትእይንትም እንደ ዘጋቢ ፊልሙ አገላለጽ በሌሎች ሃገራት እንደተደረገው ሁሉ በምህራባዊያንና በነዚሁ ሃገራት በሚኖሩ ዜጎች የተቀነባበረ እንደሆነ ያትታል፡፡ የሚገርመው ታዲያ ወያኔን ይህንን ያህል ዘመን በሕዝብ ጫንቃ ላይ ያስቀመጡት እነሱ ምዕራባዊያን ሆነው ሳለ ስጋቱን ምን እንዳመጣው ነው፡፡
ሕዝብ ለሚያቀርበው የመልካም አስተዳደር ጥያቄ፣ የፍትህ ጥያቄ እንዲሁም የዴሞክራሲና የነፃነት ጥያቄ ጀርባ ሰጥቶ በትምክህት መኮፈስ በቃኝ ለሚል ለውጥ ፍላጊ ትውልድ እሳት ላይ ነዳጅ እንደማርከፍከፍ ነው፡፡ የህውሃት ዘረኛ ቡድን አሁን የተያያዘው መንገድ ይህው ነው፡፡
ምን ያለበት ምን አይችልም እንደሚባለው የትም ይሁን የት መሰል የአመባገነኖችን ዙፋን የሚያነቃንቅ ሕዝባዊ አመጽ የሕውሃት ቡድን እራስ ምታት ነው፡፡ ሕዝብንም በመከፋፈልና በመለያየት የተጋው ፍርሃቱን ለማብረድ ነው፡፡ በተረፈ አምስት አመት ቆጥሮ የሚመጣን ምርጫ ያውም 99.6% ሊሰርቅበት የሚችል ለእርሱ በእርሱ የተከፈተ የምርጫ ስርዓት ያሰጋዋል ተብሎ አይገመትም፡፡ ከላይ እንደተገለጸው በፍርህት የሚያርደውም የሚያሶግደውም ሕዝባዊ እምቡተኝነት(ሕዝባዊ አመጽ) ነው፡፡ በተለይ አሁን ስርዓቱ በስብሶ እራሱን በገነዘበት ሰዓት ሊቀብረው የሚችል በኢትዮጲያዊነት ጥላ ስር በአንድነት የተደራጀ በቃ በሎ ነፃነቱ የሚያውጅ ተውልድ ነው!!!
ድል ለኢትዮጲያ ሕዝብ!!!

ክብርነቶ በተናገሩበት ሳመንት?

ሰኞ መያዚያ 13 2006 ባሌ ውስጥ የሁለት ንፁሀን ዜጎችን መገደል በመስማት ሳምንቱን ጀመርነው። አገዳደላቸው ወንጀላችሁን ከባድ ያደርገዋል። የመጀመርያው ልጅ በቁጥጥራችሁ ስር ነበር። በህግ አግባብ መጠየቅ ስትችሉ ነው በነጻ እርምጃ የገደላችሁት። አፉ ውስጥ ሽገጥ አስገብታችሁ ተኩሳችሁ። በሚቀጥለው ቀን ይህን ግፍ ዜጎች ስለተቃወሙ ሌላ ዜጋ ደግሞ በቀን ብረሀን ገደላችሗል።
ማክሰኞ መያዝያ 14 2006 አፋር ውስጥ አስር ንፁሀን ተገለዋል። ከቦታው ያንድ እህት ምስክርነት።” እኔ አራሴ የቆምኩት ስምንት እሬሳ ላይ ነው። ይህ የመጀመርያ አይደለም። በየቀኑ አምስት ልጅ፤ ስድስት ልጅ፤ ሰባት ልጅ፤ ስምንት ልጆች እየቀበርን ነው። ገዳዬች ፌደራል ፖሊሶች ናቸው። እጅግ ለጆሮ በሚከብድና በሚያሳዝን ሁኔታ ልጆ መገደሉ ሳያንስ ነብሰ ጡር እህትም በጽኑ ተጎድታለች። ይህቺ እህታችን ሳትሞትም አልቀረችም’”። በዚሁ ቀን ጋንቤላ ዲማ ላይ መከላከያ ሰራዊት አባለት አስገድደን ፍቶወት ካልፈጸምን ብለው ባስነሱት አንባጓሮ ከመከላከያ ሶስት ከፌደራል አንድ ሞተዋል። “ጋዜጠኛ መሳይ ዝሆኖች ሲጣሉ” ብሎ እንደገለጸው ይህ ገጠመኝ ቁጥሩ ከራት በላይ የሆኑ ንፁሀን ዜጎች ሂወት ያለአግባብ እንዲጠፋ አድርጓል ። ህጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚታገሉት ድርጅቶች ውስጥ ሰማያዊ ፓርቲ አስራ ስምንት አባላቱ ምንም ወንጀል ሳይሰሩ በዚሁ እለት ታስረውበታል። የአገሪቷ ህግ ተቃውሞ ለማድረግ ፍቃድ የማያሻ መሆኑን ቢደነግግም በዚሁ እለት አንድነት ፍቃድ ከለከልንህ ብላችሁታል።
እሮብ መያዝያ 15 ካመት በፊት ዴሬደዋ ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ በተያያዘ የታሰረ ዳንኤል ጎሳ የሚባል ዜጋ አሰቃይታችሁ ገድላችሗል። ይህ ወገን ደብደባ ሲፈፀምበት ነበር። ለእሬሳ ምርመራ ፖሊስ ከቤተሰቡ ጋር ወደ አዲስ አበባ ተልኳል። የተላከው ፖሊስ ገዳዩ እራሱ አለመሆኑ የታወቀ ነገር የለም። የሬሳ ምርመራው አምስት ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ተጠናቋል። ሐኪምቤቱ የሬሳ ምርመራ ውጤት ቅጂውን እንኳ ለቤተሰቡ አልሰጥም ነው ያለው። ባንፃሩ አባት አበበ ጎሳ ልጄን ገድሏል ብለው ከጠረጠሩት አካል ነው የምርመራውን ውጤት ያገኛሉ የተባሉት። አቶ አበበ ያላቸው አንድ ልጅ ብቻ ነው። እሱኑ ነው የገደላችሁባቸው። ልጅ የሙት ልጅ ነው። አባት በወንድ አቅማቸው ብቻቸውን ሆነውና መከራ አይተው ያሳደጉት መሆኑን ተናግረዋል። እናንተ እንዳላችሁት እራሱንም ያጥፋ ወይ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ይገደል በናንተ እጅ እያለ ስለሞተ መንግስቶት ተጠያቂነት አለበት።
ሐሙስ መያዚያ 16 ጎንደር ጪንጋ ላይ ዜጎች ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ የመብት ጥያቄ ማንሳት ከጀመሩ ቀናቶች ተቆጥረዋል። ይህን ምክንያት አድርጋችሁ አራት ዜጎችን ገድላችሗል። እንዲሁ አንድ ፖሊስ ሞታል ሌላ ቆስሏል። ነዋሪው ተቃውሞ ሲያሰማ የነበረው መሳርያ ሳይዝ ስለነበር ህዝብ ፖሊሶቹ እርስ በእራሳቸው ተጋዳድለዋል እያለ ነው። እነዚህ ፖሊሶች የሞቱትም ሆነ የቆሰሉት በየትኛውም መንገድ ይሁን ወናው ጉዳይ እናንተ በተሸነፋችሁ ጊዜ ወይ ከዛም በሗላ አልቻልንም ብላችሁ ስልጣን ስላለቃቅችሁና ሁሌም ችግሮችን ሁሉ በምትፈቱበት የሀይልና ግጭት ያለበት መንገደ ምክንያት ስለሆነ አሁንም ለነዚህም ዜጎች ሞትም በቀጥታ ተጠያቂ ናችሁ። በዚሁ እለት የቆሰሉት ዜጎች ብዙ መሆናቸውና ባህር ዳር ሆስቢታል ልህክምና መግባታቸውን ሰምተናል። አስራ ስድስት ተጨማሪ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ማታሰራቸውንም በዚህ ቀን ነው የሰማነው።
አርብ መያዚያ 17 የሰላማዊ ፓርቲ ሰላሳሶት አባላት ሊቀመንበሩን ጨምሮ መታሰራቸውን ሰምተናል። እነዚህ ዜጎች ያለምንም ጥፋት የታሰሩት ለሰላማዊ ሰልፍ ህዘብን ሲቀሰቀሱ በነበረበት ጊዜ ነው። የጋዜጠኛ የሱፍ ጌታቸው ዘግናኝና ልታፍሩበት የሚገባ ግብራችሁን የሰማንበትም ቀን ነው። የዞን ዘጠኝ ስድስት አባላትም መታሰራቸውን የሰማነው በዚሁ ሳምንት ነው። መብራት አገልግሎት ለረጅም ጊዜ እያገኘን አይደለም ያሉ የሽሮ ሜዳ አካባቢ ነዋሪዎችን አፍሳችሁ አስራችሗል።
ቅዳሜና እሁድ ዜና ሰለሌ ነው እንጂ ግድያው፤ እስሩ፤ ማንገላታቱ ይኖራል። ግፋችሁን በማጋለጥ እንኳ እኩል ልንራመድ አልቻልንም። ጨርሼ ሳለቀው ሌላኛው ሰኞ መጥቶ ይህም ሳምንት እንዲሁ በመገደል በማሰር በማሸበር መጀመሩን እየሰማው ነው። በቀጣይ ያንድነት ሰላማዊ ተቃውሞ አለ። የስልምና እምንት ተከታይ ወንድሞቻችን ጥያቄያቸውን ለማስመለስ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ አለ። አስተዳድራችሁ አድሏዊ ሆኖ እያለ አዲስ አበባን እናስፋፋለን በሚል ደሀ ዜጎችን ከመሬታቸው ለማፈናቀልና ለማኝ ለማድርግ የዘየዳችሁት እቅድ መረረ ተቃውሞ ከዜጎች እየስነሳ ነው። ጎንደር፤ ጋንቤላ ባጠቃላይ በመላ አገሪቱ የለውጥ ፍላጎት እየተንቀለቀለ ነው። ሰንቱን ገድላችሁ፤ ስንቱን አስራችሁና አሰቃይታችሁ እንደምትወጡት የምናየው ይሆናል።
ይህን እንዳስብ ያደረገኝ ሰባቱንም ቀን በየቀኑ በግፍ ስለተገደሉ እንሰማባቸው የነበሩ ሳምንታት እጅግ ብዙ መሆናቸውን ስለታዘብኩ ነው። በሳምንት አምስቴ፤ ሶስቴ ወይ አንዴ መስማት የተለመደ ነው። የታሰረውን፤ ግፍና ስቃይ የተፈፀመበትን ወይ ያሰደዳችሁትን ዜጋ ጨምረን እንይ ካልን ይህን አይነቱ ወንጀል ሳይፈፀምና እኛም ሳንሰማ ያሳለፍነው ቀን ማግኘት አይቻልም። ይህ እንግዲህ የመገናኛ ሽፋን ለማግኘት የቻለው ብቻ ተወስዶ ነው።
በእርግጥ ንፁሀን ዜጎችን መግደል ማሰር ማሰቃየት ማሰደድ ትግል ላይ እያሉም ያለቆቾ ዋና ሞያቸው እንደነበረ ብዙዎች መስከረዋል። ሚኒልክ ቤተ መንግስት ከገባችሁ ሀያ ሶስትኛ አመታችሁ ላይ ናችሁ። ታዲያ ከሀያ ሶስት አመት በሗላ ዛሬስ ነጻ እርምጃን ማቆም ቻላችሁ ወይ ነው ጥያቄው?። የለመግባባቶችን፤ ልዩነትን ሳትገድሉን ዜጋውን ሳታሸብሩ መፍታት ትችላላችሁ ወይ ነው ጥያቄው?። ከላይ እንዳዩትና ልትክዱት የማያችላችሁ ይህ ችግር ከአመት አመት የሚጨምር እንጂ የሚቀንስ በጭራሽ አልሆነም። ስለዚህ መልሱ ባጭሩ አልቻላችሁም ነው። በእርግጥም ይህን የሀያሁለት አመት እብደት ላየ መግደልና ግፍ መፈፀም እንዳትችሉ እስክናደርጋችሁ ወንጀላችሁ አይቆምም ብሎ ድምዳሜ ዜጋው ላይ ባይደርስ ሲፈጥረው ጅላንፎ ሆኖ ነው ማለት ይቻላል። እርሶ እራሶ ዘላለማዊ ከብርና ሞገስ ብለው ማሀላ ፈፅመው ስልጣን ከያዙ በሗላ እንኳ ብዙ ንፅሀን ዜጎች በነጻ እርምጃ ተገለዋል። ያለጥፋታቸው ዜጎች በገፍ እየታሰሩና ስቃይ እየተፈፀመባቸው ነው። የታዘለች ህፃንም አልቀረላትም። ይህን አይነት መንግስታዊ ሽብር በሚፈፀምበት አገር ለአፍ ካልሆነ ፖለቲካ ማህደሩ ስፍቷልም ጠቧልም ብሎ መከራከር ልብ ድክም ማድረግ ነው።
በጠቅላላው የስልጣን ዘመናችሁ የፈፀማችሁት ፍጅት ቢወዳደር ከደርጉ የሚብስ ይመስለኛል። ምክንያቱም በዚህ ደረጃና በማያባራ ሁኔታ በየቀኑ በግፍ ስለሚገደሉ ስለሚታሰሩ ሰቆቃ ስለሚፈፀምባቸው ንፁሀን ዜጎች በኔ እድሜ ያኔ አይሰማም ነበር። በርግጠኛነት ግን እስቲ ቦንብ አፈንድተን ሀያ ሰላሳ ሰው እንግደልና የዜጋውን ስሜት እናጥና ወይ ፖለቲካ እንስራበት ብለው ፍጅት የሚፈፅሙ መሪዎች አልነበሩም።” ጦርነት ሰርተን” የምትባለው አለቆቾ የሚወዷት የጫወታ አይነትን ማለቴ ነው።
ደርጉም አንባገነን ስርአት ስለነበር ሰፈራ የመሳሰሉ ግብታዊና ጎጂ እቅዶችን ተግባራዊ አድርጓል። ዜጎች ያልተስማሙባቸውና አምርረው የተቃወሟቸው ቢሆንም እንደናንተ ያጉረመረመውን ሁሉ በገፍ መግደል ወና የቅዱ ማስፈፀሚያ ግን አልነበረም። ሰበብ አይሁን ለማለት ነው። ህንፃ ለመግንባት፤ መንገድ ለመስራት፤ አበባ ለመትከል የንፁሀን ሂወት እስርና ስቃይ የግንባታዎቹ ሁሉ መሰረቱ እኮ ነው የሆነው። ይህ የባህሪያችሁ ከመሆኑም በተጨማሪ ሁላችሁም ጋር ከፍተኛ የማስተዳደር እውቀት አለ ማለት ብቻ ነው የሚቻልው።
ክብር የሆነው ለሰው ልጅ ሂወት የሚሰጠው ዋጋ ከፍተኛ በነበረበት ዘመን ዜጎች ግዛው ለምን ለምን ሞተ? ማርታ ለምን ለምን ሞተች ብለው ጉሮሮ ሊይዙ ይደርሱ እንደነበር ያውቃሉ። ዛሬ ከአንድ እስከ አስር ዝም ብሎ ዜናችን ነው። ለምን ተብሎ መጠየቅ አይደለም ገደሏቸው እኮ ተብሎም በቀጣይ አናወራበትም። ሀምሳ፤ መቶና ሶስት መቶ አዲስ ቁጥር አየደለም። ከዚህ በፊት አድርጋችሁታላ። ያዋጣል ካላችሁ ግን ለወደፊቱም በርቱ። ይህን በሚመስል እውነታ ውስጥ ጊዜና ሁኔታ ይመቻቻል። ያኔ ገደላችሁ አይደለም ገላመጣቸሁ የስልጣናችሁን ፍፃሜ እንደሚያደርገው እነግሮታለው። ማወቅ ያለቦት የተለወጠ ነገር የለም ያው ኢትዬጵያዊ ነው።
በግሌ ስልጣኑ የያዙ ለት ያደረጉትን ንግግሮትን ካዳመጥኩበት ጊዜ ጀምሮ ሁሌም ሳዮትም ሆነ ስሰማዎት አብሮአደጌን ሞዘዘኝን ነው የሚያስታወሱኝ። በዛኑ ሰሞን በፃፍኩት ፅሁፍ ስለዚሁ ጉዳይ ልነግሮት ነበር። ሰው ናቸው የሚሉ ሲበዙ አልቸኩል ሊሆኑ ይችላሉ ብዬ ተውኩት። ይህን ክፍል ጎርጄ በሌላ ገፅ ላይ አኖርኩት። ዛሬ ኮፒ ፔስት ነው ያደረኳት። በርግጥ ሰበአዊነት ያለበትና ልጆቼ ተቆጡኝ። ፀለይኩኝም የምትለዋ ቃለ መጠይቆት አጭበርብራኝለች።
ልጆች ሆነን ከልጅነቱ ጀምሮ የመጨረሻ ገንገበት የነበረ ልጅ ነበር። ለዚህ ልጅ የሆነ ጊዜ ላይ ይህን ባህሪውን ያየ ሌላኛው አብሮ አደጌ ሞዘዘኝ ብሎ የቅጥል ስም አወጣለት። ገንገበቶች ገገማ ስለሆኑ እንደተጠመቀበት ወይ እንደሰለጠኑበት ጉዳይ ነው ለመሀበረሰቡ ጠቃሚም ጎጂም የሚሆኑት። አክራሪ የእምነት ሰው፤ ወይ ገገማ ቀልደኛ፤ ጨካኝ መርማሪ ወይ ለእውነት የሚሞት ዳኛ ወይ የሚያናድድ ሊስትሮ ጠራጊ ሊሆኑ ይችላሉ። ሞዘዘኝ ከፍ ሲል የሰፈር የጠብ ቡድን አገኘው። ከዛ አንዷን ጡቷ ላይ በጩቤ ወጋት፤ እትዬ እንትናን በድንጋይ ፈነከታቸው። የዛን ሰፈር ልጅ በብረት ሰንሰለት ቀጠቀጠው። ብቻ ስሙ ባንዴ ዝነኛማ ተፈሪም ሆነ። የጠብ ቡድን ውስጥ ደግሞ ድርሻቸው ማካበድና ማሟቅ የሆነ አሉ። ሀይ ሀይ ስለበዛበት ሞዘዘኝ እስታ ሊል አልቻለም። ቆያይቶ ተገደለ።
እርሶን ሳይ ትግሬ ተጋዳላዮች ምርጥ መጠቀሚያ ነው ከመንጋው መዘው ያወጡት እላለው። ገንገበቶችን እንዲሞቃቸው በማድረግ ብቻ እንደፈለጉ ሊነዷቸው መቻላቸውን አውቀዋል። የዚህ አይነት ሰዎችን ምንም አይነት ወንጀል ማሰራት ቀላል ነው። የሚፈልገው ጎሽ አበጀህ፤ አቤት ድፍረት፤ ለርሶ ሲሆን ባለእራዩም እንዲህ ሊያሳምረው አይችልም ነበር። እስከዛሬም ተሳስተናል አይነት ሙገሳን መጨመር ነው። በርግጠኛነት ከበቀደሙ የፓርላማ ውሎዎ መልስ ብዙዎች ይህን አይነት አስተያየት ሰጥተዎታል። ከዋኖዎቹ ለዚሁ ጉዳይ ተደውሎሎታል። ሙገሳ ያለበት ተመሳሳይ ነገርን ብለዎታል። ለሁሉም መልክቴን ጠቅላይ ሚንስትሩ ሞዝዘውኛል። ብዬ አቆማለው።

በጎንደር ተኩሱ ቀጥሏል፣ በግጭቱ 6 ሰው ሞቷል

May 1, 2014

Update:

ፖሊስ በነዋሪዎቹ ላይ የወሰደው እርምጃ ያስቆጣው የጎንደር ህዝብ በቁጣ የአጸፋ እርምጃ እየወሰደ እንደሆነ ከጎንደር የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በፖሊስ እርምጃ የተቆጡ ወጣቶች የፖሊስ መኪና በመሰባበር ላይ ናቸው ተብሏል፡፡ ህዝቡ በነቂስ እየወጣ ግጭቱ እየተባባሰ መሆኑንም ምንጫችን ጠቅሷል (ነገር-ኢትዮጵያ)

——————————
ነገረ-ኢትዮጵያ – ጎንደር ከተማ ውስጥ ቀበሌ 18 ልዩ ቦታ አርምጭሆ ሰፈር፣ ገንፎ ቁጭና ህዳሴ የተባሉ ሰፈሮች የከተማው አስተዳደር ‹‹ህገ ወጥ ሰፈራ ነው፡፡›› በሚል ቤቶችን ለማፍረስ መዘጋጀቱን ተከትሎ አፍራሾቹ ከህዝብ ጋር በፈጠሩት ግጭት ከ6 በላይ ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸውንና መታሰራቸውን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ግጭቱ ከሶስት ሰዓት እስከ አራት ሰዓት ተኩል ድረስ ቀጥሎ የነበር ሲሆን ምንጫችን ደውሎ በሚነግረን ወቅት (ከቀኑ 6፡ 43) ተኩስ እንደነበር ለመረዳት ችለናል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎቹ ሚያዝያ 7/2006 ዓ.ም ቤታቸውን እንዲያፈርሱ ትዕዛዝ በተላለፈበት ወቅት ህገ ወጥ አለመሆናቸውን፣ ካልሆነም መንግስት ቅያሬ ቦታና ጊዜ መስጠት እንዳለበት በመግለጽ አንለቅም ብለው እንደነበር ይታወቃል፡፡ በዛሬው ቀን ግጭቱ የተነሳውም አፍራሾቹ እንዲፈርሱ የተወሰነባቸውን ቤቶች ቀለም በመቀባታቸውና ህዝቡም እንዳይቀቡ በመከልከሉ መሆኑ ታውቋል፡፡
በግጭቱ ፖሊስ፣ ፌደራልና ልዩ ኃይል የተሳተፈበት ሲሆን ከተገደሉትና ከቆሰሉት በተጨማሪ የአካባቢው ወጣቶች ላይ ድብደባና እስራት እየፈጸሙባቸው እንደሆነ ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ‹‹ወጣቶችን እንደ እንሰሳ በአንድ ገመድ አስረው እየደበደቧቸው ነው፡፡ ህዝብ በጅምላ እየታሰረ ይገኛል፡፡ ግጭቱ ቢያቆምም በአሁኑ ወቅት በሶስቱም ሰፈሮች ጥይት እየተተኮሰ ነው›› ያሉት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች የተወሰደው እርምጃ የጎንደርን ህዝብ በማስቆጣቱ ከዚህ የባሰ ግጭት እንዳይፈጠር ያሰጋል ሲሉም ገልጸውልናል፡፡ በግጭቱ ወቅት የመጀመሪያዋ የሞት ሰለባ የሆነችው ልዩ ኃይል ቤቷ እንዲፈርስ ቀለም ሲቀባ የተቃወመች የልጆች እናት እንደሆነችም ታውቋ፡፡

አንድነት ፓርቲ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ “የእሪታ ቀን” በሚል ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ይቀላቀሉ! (ግዛቸው ሽፈራው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር)

ጤና ይስጥልኝ
ግዛቸው ሽፈራው እባላለሁ። የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀመንበር ነኝ። አንድነት በኢትዮጵያ ሕጋዊ ፍቃድ አግኘቶ፣ በአገሪቷ ባሉ ክልሎች ሁሉ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀሰ ድርጅት ነው። አንድነት ከማንም ኢትዮጵያዊና ድርጅት ጋር ፀብ የለዉም። የአንድነት ፖለቲካ የኢትዮጵያዊነት፣ የፍቅርና የመቻቻል ፖለቲካ ነው። አላማችን ፣ የበለፀገች፣ ልጆቿ፣ በዘር ፣ በሃይማኖት፣ በጾታ ልዩነት ሳይደርገባቸው እኩል የሆኑባት፣ አንድነቷና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን መመስረት ነው።
አሁን በስልጣን ላይ ያለው የኢሕአዴግ መራሹ መንግስት፣ ግልጽነት የጎድለው፣ ተጠያቂነት የሌለው፣ በሙስና የተዘፈቀና የመልካም አስተዳደር ችግር ያለበት እንደመሆኑ፣ በሕዝብ ላይ ትልቅ በደል እያደረሰ ይገኛል። የሚከተለው የተሳሳተና ጎጂ የመሬት ፖሊሲ፣ ዜጎች፣ በልማት ስም፣ በቂ ካሳ ሳይከፈላቸው፣ ከቤታቸው እና ከእርሻ ቦታቸው በኃይል እንዲፈናቀሉ እያደረገ ነው። የሰብአዊ መብት ረገጣው፣ ተማሪዎች፣ ጋዜጠኞች የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ….. በግፍ መታሰራቸው፣ የኑሮ ዉድነቱ ሕዝቡ ከሚሸከመው በላይ እየሆነበት ነው።
ሕዝባችን ከዚህ የተሻለ ይገባዋል። ኢትዮጵያዉያን አሁን ያለውን አሳዛኝ ሁኔታ አንቀበለም በማለት፣ ለዉጥ መጠየቅ፣ ባለስልጣናትን ተጠያቂ ማድረግ ይኖርብናል።
ሕዝቡ ድምጹን ማሰማት የሚችልበት መድረክ ያገኝ ዘንድ፣ አንድነት፣ በሚመለከታቸው የመንግስት አካላት እውቅና ያገኘበት፣ ሁለት ታላላቅ ሰላማዊ ሰልፎች ፣ እሑድ ሚያዚያ 26 ቀን፣ በአዲስ አበባ እና በደቡክ ክልል በምትገኝ የድራሼ/ጊዶሌ አዘጋጅቷል። የአዲስ አበባ እና የጊዶሌ ነዋሪዎች፣ በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን እንዲያሰሙ በአክብሮት ጥሪ አቀርባለሁ። ነጻነት ነጻ አይደለም። ነጻነትን ከሌሎች አናገኝም። ነጻነትን እኛዉ እራሳችን ነን ለራሳችን ማወጅ የምንችለው። እራሳችንን በግል ካያነው፣ ምንም ማድረግ የማንችል፣ አንድ ተራ ሰው አድርገን ልንቆጠር እንችላለን። ነገር ግን ተራ ሰዎች፣ በሚሊዮን ሲቆጠሩ፣ እነርሱን ማነቃነቅ የሚችል ምንም ኃይል አይኖርም። እንነሳ። ሰልፍ እንዉጣ። ድምጻችንን እናሰማ። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን ! እራሳችንን ነጻ በማወጣት አገራችንን ነጻ እናውጣ!
እንግዚአብሄር አገራችን ኢትይጵያን ይባርካት
ግዛቸው ሽፈራዉ

UDJ Addis Ababa demonstration on May 4

“የፈሪ ዱላው አስር” ኢህአዲግ ፈርቷል። ለመሆኑ ኢህአዲግ ያሰራቸው ምንም አይነት ድብቅ አላማ የሌላቸው የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች እነማን ናቸው?

ጉዳያችን ብሎግ ፍርሃት የማያሰራው ነገር የለም።ኢህአዲግ በከፍተኛ የፍርሃት ማጥ ውስጥ ነው።ሁሉንም ይፈራል።አይዞህ አትፍራ ቢሉትም የሚችል አይመስልም።በሕዝብ ላይ የሰራቸው ሕዝብ የሚያውቃቸው እና የማያውቃቸው ብዙ ድብቅ ስራዎች ስላሉት የመፍራት ደረጃው ከዕለት ወደ ዕለት እየባሰበት እንጂ እየተሻለው አልሄደም። የሚደግፉትም ልያፅናኑት አልቻሉም።ከሚገባው በላይ ፍርሃት ሲያንቀጠቅጠው ሲመለከቱ እነርሱም ይብሱን ፈሩ።ብዙ የስርዓቱ ደጋፊዎች እና በሀብት የደለደሉቱ ሀገር ጥለው እየወጡ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።ይህ ደግሞ ሌላው የፍርሃት ገፅታ ነው።Get all the best tweets and latest buzz about freezone9bloggers
የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሌሎች ሰሞኑን የተያዙት ጋዜጠኞች ምንም የተደበቀ አጀንዳ የሌላቸው ግን ህገ መንግስቱ ላይ የሰፈረው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ይከበር ያሉ በእዚህም መስረት የሕገ መንግስቱን አንቀፅ እየጠቀሱ የሃሳብ የመግለፅ መብታቸውን የተጠቀሙ፣የሚሰሩት በመንግስት መስርያቤቶች የሆነ፣የሚፅፉት አይደለም ምን በልተው ከማን ጋር ውለው እንዳደሩ መንግስት ብቻ ሳይሆን ሕዝብ የሚያውቃቸው ኢትዮጵያውያን ናቸው።ከእዚህ በፊት በሃሳብ የሞገቱትን ሁሉ ”ህገ መንግስቱን እና ስርዓቱን ለመናድ የተንቀሳቀሱ” እያለ ሲያስራቸው የነበረው መንግስት ዛሬ እራሱ ህገ መንግስቱን አክብረው ሕግ እየጠቀሱ የፃፉትን በ20 ዎቹ እድሜዎች ውስጥ የሚገኙ ወጣቶችን ”ሃገርን በውጭ ከሚኖር ድርጅት ጋር ተመሳጥረው ሊያሸብሩ” እያለ ፌዝ አይሉት ቀልድ መሰል ክስ አቅርቦ ማዕከላዊ እስር ቤት አስገባቸው።ምንም አይነት ወንጀል እንደሌለባቸው እራሱ ኢህአዲግ ያውቀዋል።ግፍ መስራት የማይሰለቸው እና በፍርሃት የተዋጠ መሆኑ ግን የእዚህ አይነቱን ተግባር እንዲቀጥልበት አድርጎታል።
”የፈሪ ዱላው አስር” እንዲሉ የኢህአዲግ አባላት ማታ ኢቲቪ ዜና ላይ የግብፅ፣የየመንን በቅርቡ ደግሞ የዩክረንን የህዝብ ንቅናቄ እያዩ በሰላም መተኛት አልቻሉም።ያ ቀፎው እንደተነካ ንብ የሚተመው ሕዝብ አንድ ቀን እኛም ላይ ይነሳል የሚል ስጋት አድሮባቸዋል።ለእዚህም ማስረጃው ኢቲቪ ባለፈው ሰሞን ያሳየው የዩክሬንን አመፅ የተመለከተ ፊልም መጥቀሱ ይበቃል።ፍርሃታቸውን ደግሞ እነ ሚሚ ስብሃቱ ቀዝቃዛ ውሃ ውስጥ ገብቶ እንደሚንዘፈዘፍ ሰው እየተንቀጠቀጡ ሲናገሩ ሕዝብ ታዝቦ ”ወይ ፍርሃት” ብሏል።ግንቦት 20 ስመጣ ጀግና እንደነበሩ ከሃያ ዓመት በፊት የነበሩ አሮጌ ታንኮች ያሳየናል።መለስ ብለው ደግሞ በፈስ ቡክ እና በጡመራ ፈራን ይላሉ።አጀብ ነው።
ኢህአዲግ ፈራሁ ብሎ ያሰራቸው ንፁሃን ጦማርያን እና ጋዜጠኞች እነማን ናቸው? የወጣቶቹን የስራ መስክ ግልፅነት እና ሙያ ተመልክታችሁ ፍረዱ።ለፈሪዎችም እዘኑላቸው።
1/ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ
ለተባበሩት መንግሥታት ዜና አገልግሎት ኢሪን ለረጅም ጊዜ የሰራ የእንግሊዝኛው ‘ፎርቹን’ ጋዜጣ አምደኛ እና ዘጋቢ
2/ ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ
አዲስ ጉዳይ መፅሄት ከፍተኛ ኤዲተር
3/ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ
በአካባቢ ጥበቃ የሰለጠነች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ እና በቀድሞው ‘እንቢልታ’ ጋዜጣ ዘጋቢ
4/ በፍቃዱ ኃይሉ
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ፣ብሎገር እና ቅድስት ማርያም ዩንቨርስቲ በሙያው የሚሰራ
5/ አቤል ዋበላ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ የአየር መንገዱ ‘ግራውንድ ቴክኒሻን’
6/ ማህሌት ፋንታሁን
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ምሩቅ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሰራተኛ
7/ አጥናፍ ብርሃኔ
የ25 ዓመት ወጣት በፌስ ቡክ ሃሳቡን የሚገልፅ በብሎጉ ላይ ሃሳቡን የገለፀ
8/ ናትናኤል
የ 26 ዓመት ወጣት የኢኮኖሚ ባለሙያ፣’የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር’ አባል
9/ ዘላለም ክብረት
የሕግ ባለሙያ፣ማስተርሱን ከሰራ ገና ሳምንታት የሆነው በአምቦ ዩንቨርስቲ የሕግ ትምህርት መምህር ናቸው።
ምንጭ – ከጦማርያኑ ውስጥ በውጭ ሀገር የሚገኙት እንዳልካቸው እና ሶልያና ለቪኦኤ የአማርኛው አገልግሎት ሚያዝያ 20/2006 ዓም ከሰጡት መግለጫ የተገኘ።
ጉዳያችን
ሚያዝያ 21/2006 ዓም