ዓርብ 18 ዲሴምበር 2015

‘አማራ ነን‘ የወልቃይት ሕዝብ ያልተመለሰ ጥያቄ – የወልቃይት ሕዝብ አቤቱታ እንደሚከተለው ቀርቧል።


የወልቃይት ማህበረሰብ ከአዲስአበባ በ977 ኪሎሜትር ላይ በትግራይ ክልል ስር በሁመራ ዞን አድረመጭ ወረዳ የሚገኝ ነው።
በ11ሺ 149 ስኩዌር ኪሎሜትር ላይ ሰፈረውና 413ሺ564 ሕዝብ እንዳለው የሚነገርለት የወልቃይት ማህበረሰብ ባለፉት 24 ዓመታት የአማራ ብሄር ነን በሚል በአማራ ክልል ለመካለል ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ሲቀርብ ቢቆይም ጥያቄው በትግራይ ክልል በአዎንታ መልኩ ባለመታየቱ ለእስር፣ ለሞትና ለስደት መዳረጉን ከሕዝቡ የተወከሉ የኮምቴ አባላት ያስረዳሉ። ባለፉት 24 ኣመታት አማራ ነን የሚል የብሄርተኝነት ጥያቄ በማቅረባቸው ብቻ 116 ያህል ሰዎች ታስረው የገቡበት እንዳልታወቀ የኮምቴ አባላቱ በስም ዝርዝር አሳውቀዋል። በተጨማሪም ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ንብረታቸው በጠራራ ጸሀይ የተነጠቁ ሰዎችንም ዝርዝር እንዲሁ በማስፈር አቤቱታቸውን ለፌዴሬሽን ም/ቤት እና ለሰብዓዊ መብት ኮምሽን ሰሞኑን በጹሑፍ አሳውቀዋል።
የወልቃይት ሕዝብ አቤቱታ እንደሚከተለው ቀርቧል።
……………

የወልቃይት የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄ መነሻ፣

በመሰረቱ የወልቃይት የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄ አሁን የተነሳ ጥያቄ ሳይሆን ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ የተነሳና በሕገ-መንግስቱ የሰፈሩትን ሃሳቦች ታይተው ምላሽ ያልተሰጠው በየጊዜው እየተንከባለለ  የመጣ ነው። ጥያቄው እንደ ጥያቄ ማንሳት በሕግ እንደሚያስቀጣ ሕገመንግስታዊ መብት ነው ብሎ እንደመብት ተደርጎ ባለመወሰዱ የተነሳ ሲንከባለል የቆየ ጥያቄ እንጂ አዲስ ጥያቄ አይደለም።

የወልቃይት የአማራ ብሔተኝነት ጥያቄ እንደ ጥያቄ ሲነሳ ዋናው መነሻው ሕገ-መንግስቱን መሠረት ያደረገ ነው። በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 39 ተራ ቁጥር 2 ተራ ቁጥር 5 እንደሚከተለው ያስቀምጠዋል።

ተራ ቁጥር 2 “ማንኛውም የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰብ ህዝብ በቋንቋው የመናገር የመፃፍ ቋንቋውን የማሳደግ እና ባህሉን የመግለፅ የማዳበር የማስፋፋት እንዲሁም ታሪኩን የመንከባከብ መብት አለው” ይላል። ከዚህ በተጨማሪም በተራ ቁጥር 5 በዚህ ሕገ-,መንግስት ውስጥ “ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች ማለት ከዚህ ቀጥሎ የተገለፀውን ባህሪይ የሚያሳይ ማህበረሰብ ነው። ሰፋ ያለ የጋራ ጠባይ የሚንፀባርቅ ባህል ወይንም ተመሳሳይ ልምድ ያላቸው ሊግባቡ የሚችሉበት የጋራ ቋንቋ ያላቸው የጋራ ወይም የተዛመድ ህልውና አለን ብለው የሚያምኑ የሥነ-ልቦና አንድነት ያላቸውና በአብዛኛው በተያያዘ በመልክዓምድር የሚኖሩ ናቸው።

በሕገመንግስቱ አንቀፅ 39 ተራ ቁጥር 2 እና 5 በተቀመጠው መሰረት እኛ የወልቃይት ሕዝቦች የራሳችን አማራዊ ባህል ያለን ሲሆን ይህ ባህል ከትውልድ ትውልድ በቅብብሎሽ የተረከብነው እና ከዘመን ዘመን እያደገ የመጣ የነበረ ነው። ሆኖም ግን በዚህ 24 ዓመታት ውስጥ ይቅር የራሳችን ባህል ማሳደግ፣ ማስፋፋት፣ መከባከብ ይቅርና እነሆ የማንነታችን መገለጫ የሆነው ባህላችን እየጠፋ በሌላ ባህል እየተተካ የእኛ ባህል እየከሰመ በምትኩ የሌላ ባህል የሚያድግበት የሚስፋፋበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ከላይ ለመግለፅ እንደተሞከረው ህገመንግስቱ ያስቀመጠው መብቶቻችን ተረግጦ በምትኩ አዲሱ ትውልድ የሌላ ብሔር ባህል እንዲቀበል በመደረጉ የአንድ ብሔር ባህል ጠፍቶ በሌላ ባህል መተካት ሕገመንግስታው ጥሰት መሆኑ እየታወቀ በእኛ ላይ ይህ መሰል ሕገ-መንግስታዊ የመብት ጥሰት የተካሄደብን ስለሆነ ይህን ሕገ መንግስታዊ ጥሰት ቆሞ ታሪካችን ወጋችን ባህላችን በአጠቃላይ ማንነታችን ወደሚከበርበት አማራ እንድንከለል የተነሳ ጥያቄ ነው።

በሌላ በኩል ከደርግ ውድቀት በፊት ሃገራችን በተማከለ አስተዳደራዊ ስርዓት ስትመራ በነበረበት ወቅት እኛ የወልቃይት ህዝቦች በጎንደር ክ/ሃገር በወገራ አውራጃ ውስጥ ስንተዳደር የነበርን ከአማራ ህዝብ ጋር ተፋቅረን ተመሳሳይ ሳይሆን አንድ አይነት ባህል ወግ ታሪክ ያለን የስነ ልቦና ትስስር ያለን በተያያዘ መልክአምድር ጋር የምንኖር ህዝቦች ሁነን እያለን ህገ መንግስቱ ባስቀመጠው አቅጣጫ እነዚህ እላይ የተገለፁትን የብሔር ብሔረሰብ መገለጫ ተጠቃሚ ሳንሆን ቀርተናል። ያለ ህዝቡ ፍላጎትና ምርጫ ተከለልን እንጂ በራሳችን ፍቃድና ሕገ-መንግስቱ ባረጋገጠልን መስፈርት ተመስርቶ ባለመካለላችን ማንነታችን እንዲጠፋ አድርጓል።

ስለሆነም ዛሬ በዓለማችን ሆነ በሃገራችን ዴሞክራሲ በማደግ ላይ ነው። ምንጊዜም ቢሆን ዴሞክራሲ የሚያድገው በሂደት ስለሆነ ትላንትና እንደነውር ወይንም እንደወንጀል የሚታዩ የነበሩ፣ ነገር ግን የዴሞክራሲ መብቶች የሆኑ ጊዜአቸው ሲደርስ መብት ሁነው ሲገኙ በዴሞክራሲ ስርዓት መልስ ያገኛሉ። ስለዚህ በሀገራችን ሁሉን ያካተተ ህገመንግስት አለን። ስለዚህ ሕገመንግስት ሲባል ክብረ መስዋትነት ተከፍሎበታል። በመሆኑም በሕገ መንግስቱ አማካኝነት የሚመለስ ጥያቄ እስከአለን ድረስና ይህን ጥያቄ የሚመልስ ሥርዓት እስካለን ድረስ የወልቃይት የአማራ ብሔርተኝነት ጥያቄ ማነሳታችን ወንጀል ሳይሆን ሕገመንግስታዊ መብታችን መሆኑ አሁንም ሊታወቅልን ይገባል።

በወልቃይት ሕዝብ የደረሱ የፖለቲካ ተፅዕኖዎች

  •    ልጆቻችን በቋንቋቸው እንዳይማሩ በግድ ትግርኛ እንዲማሩ ተደርገዋል፣
  •    በየትኛው መ/ቤት የስራ ቋንቋ በግድ በትግርኛ እንድንናገር ተገደናል፤
  •    የአማርኛ ባህል ቀይራችሁ የትግርኛ ባህል በግድ ተቀበሉ እየተባልን ነው
  •    የአካባቢያችን ጥንታዊ ያሀገር፣ የወል እና የጋራ ስሞች ማትም የወረዳ፣ ከተማ መንደር፣ ወንዝ ጋራ ሸንተረር ምንጭ በትግራይ ስም ተሰይመዋል።
  •    በትግራይ ባሉ መስሪያ ቤቶች የወልቃይት ተወላጆች 5 በመቶ የትግራይ ተወላጅ 95 በመቶ ሲሆን፤ ያሉትም እኩል መብትና ስልጣን የላቸውም፤
  •   ትግራይ ክልል መሆን አንፈልግም ብለው የተቃወሙትን ከ300 በላይ የሚሆኑ የወልቃይት ተወላጆች ከየቤታቸው በጨለማ ታፍነው ተወስደው ያለፍርድ ጠፍተዋል። ለዚህ አባሪውን መመልከት ይቻላል። የእነዚህ ወገኖች በአመለካታቸው መጥፋት ዋናው ምክንያት የማንነት ጥያቄ በማንሳታቸው በመሆኑ የወገኖቻችን መጥፋት ሕገ-መንግስታዊ ጥሰት ስለሆነ ይህን የፈፀመው የትግራይ መንግስት መሆኑ፤
  •    ወልቃይት በመወለዳችን በማንነታችን እንድናፍር ሁነናል፤
የወልቃይት ህዝብ በኢኮኖሚ የደረሰበት በደል፣
  •    ትግራይ አይደለንም ያሉትን በቀጥታ ንብረታቸውን ሀብታችን ተወርሰዋል። ሃብትና ንብረታቸው የተወሰደባቸው ዝርዝር ከአባሪው ጋር ተያይዟል፤
  •    መሬታቸው ተነጥቆ ለትግራይ ተወላጅ በመስጠት የወልቃይት ተወላጆች ወደ ድህነት እንዲወርድ ተደርገዋል።
  •    በግልባጩም የትግራይ ተወላጅ አለአግባብ ሃብታም እንዲሆኑ ተደርጓል
ለዘመናት የወልቃይት ህዝብ ገበሬ ሲያርሰው የነበረ መሬት ተነጥቆ ለትግራይ የእርሻ ድርጅት ተሰጥቷል። እኛ የት እንውደቅ ተብሎ አቤቱታ እንኳን ቢያቀርብ ህዝቡን የትግራይ ክልል በየአመቱ ለምዕራባዊ ዞባ እያለ አዳዲስ የመሬት አዋጅ በማውጣት ለትግራይ ተወላጅ በወልቃይት መሬት ባላባት ሆነው እንዲያስተዳድሩት ሲደግፍ የወልቃይት ህዝብ ግን ከመሬቱ እንዲነሳና እንዲሰደድ የተለያዩ እርምጃዎች ወስዷል። የዚህ ሰለባ የሆኑት ሰዎች የወልቃይት ተወላጆች ለአብነት በአማራ ክል በሶረቃ፣ በአብራሃጅራ፣ በአብደራሬ፣ በመተማ፣ በቋራ በሽህዲ፣ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል እና በጋምቤላ ክልል ተሰደው ይገኛሉ። የትግራይ ተወላጆች ግን በሰፈራ የመጡ አሁን ከሁለት ሄክታር አሳልፈው የአምሳ እና የመቶ ሄክታር ከዛም በላይ ባለቤቶች ሆነው ይታያሉ። በአጠቃላይ በአካባቢያችን አልምተን እንዳንጠቀም እድሉ ተፈፅሞብናል።

በወልቃይት ሕዝብ በማህበራዊ ኑሮ ላይ የደረሰው ጉዳት፣
  •   ከመንገድ አንጻር የትግራይ አካባቢ ከወረዳው ቀበሌ የሚያገናኝ ጥርጊያ አብዛኛው ተሰርቷል። የወልቃይት አካባቢ ግን ከወረዳ ቀበሌ ይቅርና ከወረዳ ወደ ወረዳ የሚያገናኝ አንኳን በቅጡ ተሰርቶ አይታይም። ዛሬም የወልቃይት እናት መኪና አጥታ በወሊድ የምትሞት ናት።
  •   ውሃ ዛሬ በብዙ የትግራይ አካባቢ ንፁህ ውሃ ሲጠጣ የወልቃይት ህዝቦች ግን እንስሳ እና ሰው በአንድ የሚጠቀሙበት በብዙ ቦታ ይታያል።
  •   ትላንትና የመጣ የትግራይ ሰፋሪ ህዝብ ቧንቧ ውሃ ሲዘረጋለት ጥንታዊ የወልቃይት ህዝብ ግን ምንም ውሃ እና የጉድጓድ ውሃ ሲጠቀም ይታያል የህክምና ተቋማትም ተመሳሳይ ለትግራይ ተወላጆ በሚጠቅም መልኩ የተሰራ ነው።
  •   የትምህርት ተቋማትም አንድም ኮሌጅና ዩኒቨርስቲ የለም
የወልቃይት ህዝብ ልጆቹን አስተምሮ በተወለዱበት አገር ስራ ቅድሚያ መስጠት እና ማግኘት ሲገባቸው ቅድሚያ ለትግራይ ተወላጆ የስራ ቦታ እና እድል ይሰጣል ሊሰጥ ከሆነ ደግሞ በናቱ ወይም በአባቱ የትግራይ ዘር መወለድ ቅድሚያ በሚሰጥ ይጠናል። አጠቃላይ የወልቀቃይት ህዝብ ማህበራዊ ኑሮውን ከትግራ ተወላጆች ተጠግቶ እንዲጠቀም የተፈረደበት ይመስላል። ከላይ በዝርዝር ለመግለፅ እንደተሞከረው አሁን ሀገራችን በዴሞክራሲና በልማት ጎዳና ባለችበት ወቅት ምንም እንኳ አንዴት እነዚህ ችግሮች ሊከሰቱ ይችላሉ ብሎ የሚጠይቅ አካል ስለማይጠፋ የተዘረዘሩትን ችግሮች ለመፈፀማቸውና እየተፈፀሙ እንዳሉ ዋናው ምስክር ህዝባችን ስለሆነ ህዝባችን የፌዴሬሽን ምክር ቤት እንዲያነጋገርልን።

የፌዴሬሽን ም/ቤት ባለው ስልጣንና ኃላፊነት በሰላማዊ መንገድ ያነሳነው የዴሞክራሲ ጥያቄያችን ተመልክቶ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጠን፣ እኛ የህዝባችን ተወካዮች ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ህዝባችን የደረሰበት ሕገመንግስታዊ ጥሰትና እየደረሰበት ያለ በዴሞክራሲ መንገድ እንዲፈታ ከህዝባችን ጋር ለመወያየት እንዲፈቀድልን፣ የህግ ከለላ እንዲሰጠን። በሌላ በኩል ወደእዚህ የመጣን የህዝባችን ወኪሎች ስንመለስ በራሳችን፣ በቤተሰቦቻችንና በሀብታችን ላይ ጉዳት እንዳይደርስብን የሕግ ከለላ እንዲደረግልን በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን።

ልጆች በጥይት አይቀጡም፣ የትኛው መንግስት ዛሬ ተማሪዎችን በጥይት ይደበድባል?

ልጆች በጥይት አይቀጡም፣ የትኛው መንግስት ዛሬ ተማሪዎችን በጥይት ይደበድባል?

ዛሬ የዓለም መሪዎች በፓሪ ፈረንሳይ ስለ ዓለማችን ያየር ንብረት ችግሮች እየመከሩ ነው።ችግሩ ደግሞ ቀድሞ ሰለባ ያደረገው ደሃ አገሮችን መሆኑ ግልጽ ነው።ኢትዮጵያም አንድዋ ናት።ከኢትዮጵያ ህዝብ አስራ አምስት ሚሊዮን ለራብ መጋለጡ መደበቅ የማይቻል እውነት ነው።ወያኔ ሃላፊነት ያለው መንግስት ቢሆን እዲህ ጊዜ የማይሰጥ ችግር ላይ ያተኩር ነበር።የአስራ አምስት ሚሊዮን ህዝብ ለራብ መጋለጡን የአውሮፓ ህብረት ጉዳዬ ብሎ ሲመክርበት ህወሃት ይህን ችግር ከፖለቲካ ተቃውሞ መለየት ተስኖት ከውይይቱ እንኳን ለመሳተፍ አልመረጠም።ካአየር ንብረት ችግሩ እጅግ የከፋው የአስተዳደር ጉድለቱ የሚፈጸመው ግፍ ነው በኢትዮጵያችን።ኢትዮጵያ መንግስትዋ ሽብርተኛ ያየር ንብረት ችግሯ በጣም ፈታኝ የሆነበት ዘመን ዛሬ ነው።ያየር ንብረት ችግር ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ልጆችዋን እየገበረች ነው።ልጆች በጥይት ይቀጣሉ።የህወሃት ግፍ ይህ ነው።TPLF killing Oromo students
ህወሃት የዛሬውን አይበለውና የትግራይ ህዝብን አታግልለታለሁ ሲል “ሃረሽታይ ሸቃላይ” ወይም አርሶአደር ላብአደር ይል ነበር። ለህዝብ እንደቆመ ሁሉ።ዛሬ “መሬት ላራሹ”ን ተረተረት አድርጎ የኢትዮጵያን አርሶ አደር መሬት ንብረቱን ቀምቶ እያራቆተው ይገኛል። ከአርሶ አደሩ አብራክ የወጡትን ልጆቹን ለአርሶ አደሩ በደል ቢነሱ በጥይት ይደበድባቸዋል። የዓለም ዜና ይህን ባያተኩርበትም ዛሬ የኢትዮጵያ ሁኔታ በከፋ መጠን እየተናጋ መሆኑን ማንም ሊክድው አይችልም።በዓለም ተበትነን ያለነው ዜጎች በየሰዓቱ የምንከታተለው ይህንኑ ነው።
ማንም ህብረተሰብ ቀጣዮን ትውልድ ያስተምራል።ፈደል ተቆጥሮ፤ሂሳብ ተምሮ፤ ቋንቋ ሰዋስው አጥንቶ፤ሳይንስን ተቃምሶ የህብረተሰብ ጥናት ታሪክንም ለካክፎ ወደከፍተኛ ትምህርት ማምራት አለ።ከፍተኛ ትምህርት አንድ ህብረተሰብ ለወጣት ዜጋው የሚያቀርበው ትልቁ የውቀት ገበታ ነው።አላፊነት የሚሰማው አገሩን የሚወድ ትውልድ የሚዘጋጅበት፤ራስንም ዓለምን ለማወቅ የሚሞከርበት የድሜ ዘመን የሚልፍበት ነው ማለት ስተት አይሆንም።በከፍተኛ ትምህርት ቅጥር ውስጥ እማይጠየቅ የለም።እማይፈተን የለም። ሁሉም በነጻነት ይፈተሻል።ይሞከራል።ጉልበት፤ ስልጣን አለው ተብሎ የሚፈራ የለም።በከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሁሉም ይተቻል።ይጠናል።ይተነተናል።የበደለም ይኮነናል።ለውነት ለፍትህም ቆምን ይባላል።ዛሬ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለተቃውሞ ቢወጡ ለአገር ለወገን ብለው ነው።ተቃወሞ ወግ ነው።ልጆች ስለተቃወሙ በጥይት አይቀጡም።የትኛው መንግስት ዛሬ ተማሪዎችን በጥይት ይደበድባል ? ፈሪው ህወሃት ብቻ!ጨካኙ ህወሃት ብቻ!ከፖለቲካ ድርጅትነት ዘቅጦ የእጽ ሻጭ ካርቴል የነብሰገዳይ ጥርቅም ዓይነት የሆነው ህወሃት ብቻ!
ህወሃት መሩ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ቅጥር ግቢን የሞት አውድማ ያደረገው ገና ድሮ ነው። የመለስ ዜናዊም “ሌጋሲ” “ትሩፋት” አንዱ ይህ ነው። ሰሞኑን በሀረር ሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የሆነው ዘግናኝ ነው። በሌሎቹም ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁ። የህወሃት አገዛዝ ከጅምር አካሄዱ ይሄው ጥፋት ነበር።በዘውዱ ስርዓት ፖሊስ ዩንቨርሲቲ ቅጥር ሲገባ እጅግ ይኮነን ነበር።ወታደራዊ ደርግም ወጣቱን በቀይ ሽብር ቢጨፈጭፍም እዲህ እንደ ህወያት መሩ መንግሰት ዩንቨርሲቲውን የጦር ቀጠና አላደረገውም ነበር።ህወያት መሩ መንግሰት ቁንጮ ላይ ያሉት ጥራዝ ነጠቅ የዛሬ ተራ ቀማኞች “መሬት ላራሹ” ካለው ትውድ እንደመር ይሉ ይሆን ?ያትውልድ ህወያት የሚባል ጉድ ትቶ አለፏል።ግን የኢትዮጵያ ተማሪዎችን አኩሪ የትግል ታሪክን ህወሃት አይሽረውም።እዚህ ቀጣይ የሞት ሂደት ውስጥ የከተተው የቀማኛ ቡድንን አስወግዶ የዜግነት ክብር የነገሰባትን፤እኩልነት የሰፈነባትን ነጻ ኢትዮጵያ ከህዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሀይሎች ጋር በመሆን ይመሰርታል።እልሙ ኢትዮጵያ! ናት።ድል የሚገኘው በህብረት ትግል እንደሆነ ይገነዘባል።
የኢትዮጵያ ተማሪዎች ቀድሞ ሲነሱ ኢትዮጵያ! ነው ያሉት።”መሬት ላራሹ” የተባለው ለትግራዩ፤ለኦሮሞው፤አማራው፡ለአፋሩ፤ለሱማሌው ለደቡቡ ለሁሉም ነው፤የህወሃት የአዲሱ አገዛዝ አናት ላይ መሆን እንጂ ”መሬት ላራሹ” ዛሬም ፍቺ ያላገኘ የዴሞክራሲ ጥያቄ ነው።የምናየውን እልቂትን የሚገፋው ምክንያት ይሄው ነው።”አዲስ ንጉስ እንጂ ለውጥ መቼ መጣ?” ቴዲ አፍሮ ጨርሶታል። እኩይ ንጉስ ነው የመጣ!
በኦሮሚያ ክልሎች የሆነው ከላይ ያልኩት ነው። የከፍተኛ የትምህርት ገበታን የሞት አውድማ ማድረግ ነው ።ተማሪዎች ልክ ድሮ የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንደታገሉት ሁሉ “መሬት ላራሹ” ብለው ዛሬም እየታገሉ ነው።የወገንን መሬት “ኢንጉርጉረምቱ!” አይሸጥም ! ነው ያሉት።ጥያቄው የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ሁሉ ጥያቄ ነው።በተለይ የኦሮሚያ ክልል ብቻ ብሎ የሚፈረጅ አይደለም።የአፋሩ፤የጋምቤላው በደል ከአማራውና ከኦሮሞው የሚለይ አይደለም።
የገጠመንን ችግር የከልል ማድረግ የኢትዮጵያን ሁኔታ ጠንቅቆ አለመረዳት ነው።የልጆቻችን ተስፋም እመረቃለሁ፤ ለማዕረግ እበቃለሁ እንጂ እሞታለሁ መሆን አይገባውም። የልጆቻችን ሞት የኢትዮጵያዊ ወገናችንም ሁሉ ሞት ሊያገሸግሸን ይገባል።ኢትዮጵያ ተበደለች። ልጆችዋን ገበረች።ተምሬ ወግ ማእረግ አይባታለሁ የምትባለዋን ኢትዮጵያን የምናይበት ጊዜው እሩቅ አይሆንም።የሚጠይቀው ህብረታችንን ብቻ ነው። ህወሃት መሩን መንግስት ተባብረን እንሸኝ።ከዚህ ወዲያ ድርድር የለም።
የኦሮሚያ ክልልን መዝረፍና ማስዘረፍ የአማራውን ክልል የሞት፤የቃጠሎ የእስራት ቀዬ ማድረግ በሁለቱም የኢትዮጵያ አካሎች ላይ የዘር ማጥፋት ወጀልን ወደ መፈጸም የሚቀርብ ክፋት ነው።የጎንደር ህዝብ በደል የኢትዮጵያ በደል ነው።በተለይ አጠገቡ ለሆኑት የትግራይና የወሎ ህዝቦች በደል ነው።ጎንደርን መሸንሸን እንደምን ይሆናል ? የኢትዮጵያ አንድነት ምንጭ መሰረቱን ?! የወልቃት አልበቃ ብሎ ቅማንትን! ከወንድም እቶቹ ማጋጨት ?ወሰን ድንበር ለባዕድ ለመለገስ ሸር ጉድ? አዲሳባን እናስፋ በማለት ዝርፊያ አሁን ይቁም! ራብም እየፈጀን ልጆቻችንም እየሞቱ እየተቃጠልን እየደማን እስከ መቼ? ወገኖቼ።ዘረፋው እስከመቼ? ምን እንጠብቃለን።
ለደሃው የኢትዮጵያ አርሶ አደር አለኝቶቹ ዛሬ በዳያስፖራ የምንገኝ ነን!
በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የህወሃት ገዳዮች የሚፈጽሙትን በህብረት እናውግዝ!
ኢትዮጵያን ከክፉ መከራ አላህ የሰውራት! ሁላችንም እየጸለይን እንታገል!

ለወያኔ ድርጊት፣ ምን ስም እናውጣለት (ይገረም ዓለሙ)

ለወያኔ ድርጊት፣ ምን ስም እናውጣለት (ይገረም ዓለሙ)

ይገረም ዓለሙ
ወገንን ጨፍጫፊ ቆዳው የነጣ ነው
በአበሻ የሚጨክን ፈረንጅ ብቻ ነው፤
እያለ የሚያስብ የዋህ ፍጡር ማነው
ጨፈጫፊ ከሆነ አበሻም ጣሊያን ነው
እንቶኔም በተግባር ሲኞር እንቶኔ ነው፤
Police brutality in Ethiopia
በየግዜው እየከፋ የሄደውን የወያኔ አረመኔነትና የሀገራችንን ጉዞ ወዴትነት ሳስብ ትውስ ያለችኝን ይህችን ስንኝ ወደ ማስታወሻየ ገልብጬ ያኖርኳት በ1980ዎቹ መጨረሻ ግድም ለንባብ ይበቁ ከነበሩት መጽሄቶች ከአንዱ ነው፡፡ ወያኔ ዴሞክራት መስሎ ለመታየት በሞከረበትና ትክክለኛ ማንነቱ ገሀድ ወጥቶ ብዕርን ከጠመንጃ አስበልጦ መፍራት ባልጀመረበት በዛ ወቅት እንዲህ የጻፉት ሰው ዛሬ በህይወት ካሉ ምን ሊሉ እንደሚችሉ መገመት ይቸግራል፡፡
ወያኔዎች ደርግን በጨፍጫፊነት በማውገዝ ዛሬም ድረስ ፈሺስት ናዚ ወዘተ በማለት ይገልጹታል፡፡ በዘመነ ደርግ የተፈጸመውን ቀይ ሽብርም ለአንድ ሰሞን የፖለቲካ ፍጆታ ሊጠቀሙበት ሞክረዋል፡፡ ግን ካወገዙት ተግባር ተምረው ከተጸየፉት ድርጊት ርቀው ሊገኙ አልቻሉም፡፡ በርግጥም ከጅምሩ ስለ ቀይ ሽብር የነበራቸው አያያዝ ሊማሩበት ሳይሆን ሊያደናግሩበት፤ ለተበዳዮች ፍትህ ሊያስገኙበት ሳይሆን ጥላቻን ሊያነግሱበት እንደነበረ መለስ ብሎ በማስታወስ ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ከቀይ ሽብር ቢማሩ ኖሮ ራሳቸው ያቋቋሙት የቀይ ሽብር ኮሚቴ ይዞት የነበረውን “ያለመቻቻል ፖለቲካ ሰማዕታት፣መቼም እንዳይደገም” የሚለውን መርህ ተግባራዊ ባደረጉና እንዲህ የለየላቸው ጨፍጫፊ ባልሆኑ ነበር፡፡
የቀይ ሽብር ነገር ለወያኔ የፖለቲካ ካርድ በነረበት ወቅት የቀይ ሽብር ኮሚቴ ባዘጋጀው አንድ የውይይት መድረክ ላይ የጥናት ወረቀት ያቀረቡት ፕ/ር ባህሩ ዘውዴ “…የፖለቲካ ልዩነቶችንም በተመለከተ አንዱ ወገን ምንግዜም ቢሆን ፍጹማዊ እውነትን ሊታደል እንደማይችል ተገንዝቦ የሌላውን ወገን ሀሳብ እህ ብሎ ማዳመጥ መቻል ይኖርበታል፡፡ የተቀዋሚ ወገን አየለ ብሎ ቃታ ለመሳብ መጣደፍ ዞሮ ዞሮ ሀገርን በብርቱ የሚጎዳ መሆኑን ከ « ቀይ» ሽብር ያተረፍነው ትልቁ ትምህርት ነው” ብለው ነበር፡፡ ነገር ግን ወያኔዎች ቀይ ሽብርን ያራገቡት ፖለቲካ ሊቆምሩበት እንጂ ሊማሩበት ያለመሆኑን ውለው ሳያድሩ በጀመሩት የሁሉም ነገር መፍትሄ ከጠመንጃ ይመነጫል አይነት ተግባራቸው አሳይተውናል፡፡
ሌላው ተናጋሪ የነበሩት ዶ/ር የራስ ወርቅ አድማሴ ባቀረቡት ጽሁፍ ደግሞ “ከኛ ትውልድ ስህተት በመማር የልጆቻችንን ትውልድ ከፖለቲካ ግድያ፣ከዘር ማጥፋት ፍጅትና ከስጋትም ጭምር ነጻ በሆነችና ፍትህ በነገሰባት ኢትዮጵያ እንዲኖሩ እንመኛለን፡፡ ይህን ምኞታችንን እውን ካደረግን ደግሞ እሱ ጊዜ የማይሽረውና የማያደበዝዘው ዕውነተኛው የሰማዕታት መታሰቢያ ይሆንልናል፡፡”» በማለት ዋናው ቁም ነገር የድንጋይ ሀውልት ማቆሙ ሳይሆን ካለፈው ተምሮ መሰል ጥፋት እንዳይደገም ማድረጉ እንደሆነ ነበር የገለጹት ፡፡ግና አንደ አለመታደልም ሆነና ወያኔን ሀይ የሚለውም ጠፋና ይሄው ዛሬ ድረስ ስጋቱም ፍጅቱም እንዳለ አለ፡፡
ባለፉት ሀያ አራት ዓመታት ወያኔ ከምንይልህ ቤተ መንግሥት ሆኖ የፈጸማቸው ኢ- ሰብአዊ ተግባሮቹን ለታሪክና ለትውልድ ፍርድ ትተን ዛሬም በእብሪትና በማን አለብኝነት የሚፈጽማቸውን ተግባራት ስናስተውል ጨፍጫፊ ከሆነ ሀበሻም ጣሊያን ነው የሚያሰኙ ናቸው፡፡ታዲያ እኒህን ከእለት እለት እየባሱ የመጡ አረመኔያዊ ድርጊቶቹን ምን ስም አንስጣቸው፡፡ ይመጥ አይመጥነው ባይታወቅም አንድ ሰሞን አንዳንድ ሰዎች ጥቁር ሽብር ማለት ጀምረው ነበር፡፡
ከወራት በፊት አቶ ኤፍሬም ማዴቦ “አይኔ እያየስ እዚህ ውስጥ አልገባም, መሠረት ሙሴ” በሚል ርዕስ ባስነበቡን ጽሁፍ ስሙ የተጠቀሰው ወጣት ከሌሎች ሁለት ወጣቶች ጋር ጎነደር መተማ ላይ ተያዘ፡፡ ሁመራ ተወስደው ጫካ ውስጥ ሊረሸኑ ጉድጓድ አፍ ላይ ቆመው ገዳዮቹ አንደኛውን ወጣት በጥይት መትተው ወደ ጉድጓድ ሲከቱት አይኔ እያየስ እዚህ ውስጥ አልገባም ያለው መሰረት እግሬ አውጪኝ ብሎ ሮጦ አካሉ በጥይት ቢነዳደልም አምልጦ በሻዕቢያ ወታደሮች እጅ መውደቁንና ታክሞ ድኖ ግንቦት ሰባትን መቀላቀሉን ነግረውናል፡፡( ይህን አንብበን ዝም ማለታችን ራሱ አስገራሚ ነው)
ወጣቱ በፈጣሪ ቸርነት በማምለጡና አቶ ኤፍሬምንም በማግኘቱ የአይን ምስክርነቱን ሊሰጥ ቻለ፡፡ ባይሆን ኖሮ ይኑሩ ይሙቱ ሳይታወቅ ቤተሰብም እርሙን ሳያወጣ ጫካ እንደተጣሉ ይቀሩ ነበር፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በየደረጃው ባሉ ዘመንኞች እየተረሸኑ በጅምላ የተቀበሩና በየጫካው የተጣሉ ዜጎችን ቤት ይቁጠራቸው ማለት ይቻላል፡፡ አንድ ቀን ግን መጋለጡ አይቀርም፡፡
እዛው ጎንደር ውስጥ የወንድሞቹ በረሀ መግባት በሰላም ለሚኖረው ክብሩ አሰፋ ወንጀል ሆኖ 18 ዓመታት አስፈርዶበት በጎንደር ወህኒ ቤት ስድስት ኣመታትን ካሳለፈ በኋላ ከእስር ቤት ተወስዶ መረሸኑን ከአርበኞች ግንቦት ሰባት መግለጫ አንብበናል፡፡ይህም ወያኔዎች ጠላታችን የሚሉትን ሰው አስረው እንኳን እንቅልፍ የማይወስዳቸውና ካልገደሉ የማይረኩ መሆናቸውን የሳየ ነው፡፡ በዚህ መልክ የተረሸኑ ወገኖቻችንስ ምን ያህል ይሆኑ?
ከሁለት ዓመት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ ከስድስት ኪሎ ወደ ፈረንሳይ የሚሄደው መንገድ ሲሰራ ሶስተኛ ሻለቃ በመባል ይታወቅ የነበረውና ወያኔ ስሙን እየቀያየረ የሚጠቀምበት የጦር ሰፈር ጫፉ ላይ አጥሩ ፈርሶ ሲቆፈር የቅርብ ግዜ አስክሬን ከነተጠቀለለበት ብርድ ልብስ መገኘቱ ይታወሳል፡፡ በማህበራዊ ድረ ገጽም ምስሉ ተለቆ ለአንድ ሳምንት መነጋገሪያም ሆኖ ነበር፡፡ (ንዴት ቁጣችን፣ ተቃውሞ ፉከራችን ከአንድ ሳምንት አይዘል አይደል!) ሳይታሰብ በመንገድ ስራ ቁፋሮ ምክንያት ለእይታ የበቃው ያ የወገን አጽም የወያኔ የጦር ካምፖች ለወታደራዊ ተግባር ብቻ ሳይሆን ታፍነው ለሚሰወሩ ዜጎች ማሰቃያ መግደያና መቀበሪያነትም የሚያገለግሉ መሆናቸውን ያጋለጠ ነው፡፡ በዚህ መልክስ ስንት ወገኖቻችን በአረመኔዎች እየተገደሉ በየቦታው ተቀብረው ይሆን; ጠያቂ ጠፍቶ ጯሂ አልተገኝቶ ሆኖ እንጂ ቁፈራው ሰፋ ተደርጎ ቢቀጥል ብዙ ጉድ በተጋለጠ ነበር፡፡
የፖለቲካ ትርፍ አገኛለሁ ብሎ በደርግ እየተገደሉ በየቦታው የተቀበሩ ወገኖቻችንን አጽም እያወጣና በቴሌቭዥን እያሳየ ሲያስለቅሰንና ሲያላቅሰን የነበረው ወያኔ እሱ በተራው ሀያ አራት ዓመት ሙሉ አስሮ አሳቃይቶና ገድሎ ሊረካ አልቻለም፡፡ መታሰር መሰቃየትና መገደል በቃን ብለን ካላመረርንና ካልተባበርን አለበለዚያም ለወያኔ ሰጥ ለጥ ብለን ካላደርን በስተቀር ወያኔ ከዚህ አድራጎቱ መቼም የሚገታ አይመስልም፡፡ ግና ዘላለማዊ ምድራዊ ኃይል የለምና አንድ ቀን የጨለመው ሲበራ ህሊናቸው ፋታ ነስቶአቸው ወይንም ህግ አስገድዷቸው ወያኔ በዘመነ ሥልጣኑ እየገደለ በየቦታው ስለቀበራቸው ኢትዮጵያውያን የአይን እማኝነታቸውን የሚሰጡ ሰዎች መኖራቸው አይቀርም፡፡
ይሄው ሰሞኑን ደግሞ በየመድረኩ ስለፍትህ ስለ መልካም አስተዳደር ተቃውሞን በሰላማዊ መንገድ መግለጽ ስለመቻል ወዘተ እየደሰኮሩ በተግባር ግን በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ባቀረቡና ተቃውሞ ባሰሙ ወጣቶች ላይ ነብሰ ገዳይ ወታደሮቻቸውን አሰማርተው እያስደበደቡ እያሳሰሩና እያስገደሉ ነው፡፡ ለሀያ አራት አመታት በስልጣን ለመቆየት የቻሉት በማናቸውም ወገን የሚነሳን ማናቸውንም ጥያቄና ተቃውሞ በእስር በድብደባና በግድያ ጸጥ በማሰኘት በመሆኑ ሌላ ለጥያቄ መልስ መስጫ ዘዴም ሆነ ተቃውሞን ማስተናገጃ መንገድ አያውቁም፡፡
የአረመኔነታቸው ክፋት ጎንደር እስር ቤት ተቃጥሎ እስረኞች ህይወታቸውን ለማትረፍ ሲሮጡ እየተኮሱ ገድለዋል፡፡ ያለህበት ቤት ሲቃጠል አይንህ እያየ ዝም ብለህ ተቃጠል የሚሉ ነው የሚመስለው፡፡ እንደው እነዚህ ከእሳት የሚያመልጥን ዜጋ ተኩሰው የሚገድሉ ነብሰ በላዎች ከምን አይነት ማህጸን የተፈጠሩ ይሆኑ! ወይስ ወያኔዎች ሲያሰለጥኑዋቸው ከምግብ ወይንም ከሚጠጣ ነገር ጋር ቀላቅለው የሚሰጡዋቸው ከሰውነት ወደ አንስሳነት የሚቀይር፣ ሰዋዊ አስተሳሰብን አደድቦ ህሊና ቢስ የሚያደርግ ነገር ይኖር ይሆን፡፡
ወያኔዎች የአረመኔነታው ክፋትና የንቀታቸው ብዛት አንድም ገደሉ መቶ ለአፋቸው ይህል እንኳን በተፈጠረው ነገር እናዝናለን አይሉም፡፡ እነርሱ የሚያውቁት በሟች ቁጥር ላይ መሟገት ነው፡፡ ሰሞኑን የምንሰማውም ይህንኑ ነው፡፡
በሰላም ተቃውሞ በሚያሰሙ ( ቢቢስ ድንጋይ ይወረውሩ ይሆናል) ወጣቶች ላይ እንዲህ በየግዜው ግድያ የሚፈጽሙት ወያኔዎች ደርጎች ላይ እንደሆነው በአዲስ አበባ ከተማ በትላልቆቹ ባለሥልጣኖች ላይ ቢተኮስባቸው፣ ከመካከላቸው ቢቆስልና ቢሞትባቸው ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ መገመት አይከብድም፡፡ አብርሀ ደቦጭና ሞገስ አስግዶም የጣሊያኑን ጀነራል በቦምብ ካቆሰሉ በኋላ ጣሊያኖች በአዲስ አበባ የፈጸሙት ጅምላ ፍጅት መቼም የሚረሳ አይደለም፡፡ ወያኔዎች ከእስከዛሬ ተግባራቸው እንዳወቅናቸው ከመካከላቸው አንድ ሰው ቢገደል ወይንም ቢቆስል ተመሳሳይ ተግባር ከመፈጸም ወደ ኋላ እንደማይሉ ፡፡ ታዲያ ይህን በቀይ ሽብር ለተጨፈጨፉ ወገኖች ሀውልት አቁሞ ጭፍጨፋ የሚፈጽም አረመኔ ቡድን ለእሱም ሆነ ለድርጊቱ ምን ስም እናውጣለት፡፡

የኦሮሞ ህዝብ ብሶት፥ ወደ የጋራ ነጻነት

የኦሮሞ ህዝብ ብሶት፥ ወደ የጋራ ነጻነት


“ከአዲስ አበባዉ የእርሻ መሬት እስከ አሜሪካዊ ቤተ መንግስት፥መብትን የማስከበር ጣምራ ሒደት!”
በአሜሪካዉ ቤተ መንግስት እና በዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የኢትዮጵያ መንግስት በሰላማዊ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ የሚያደርገዉን ግድያ፣ድብደባ፣ እስር፣ወከባና ማፈናቀልን በመቃወም በተደረገዉ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በመገኘት ሳዲቅ አህመድ ያዘጋጀዉ ልዩ ፕሮግራም።

Washington DC protest against the killing of Oromo students