ማክሰኞ 5 ጃንዋሪ 2016

በወቅታዊ የአገራችን አሳሳቢ ጉዳዮች ላይ ለመምከር የተዘጋጀ የዉይይት መድረክ — በዋሽንግተን ዲሲ


ኢትዮጵያ እና የህዝቦቿ የወደፊት እጣ ፈንታ አሳስበዎታል? ያገርዎ፣ የባህልዎ፣ የእምነትዎ ወዘተ ጉዳይ ያገባኛል ይላሉ? እዉነተኛ ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር፣ የህግ የበላይነት፣  ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ስርዓት እንዲመጣ ይሻሉ? ለነዚህ እና ለመሳሰሉት አንገብጋቢ ጉዳዮች ገንቢ ሃሳብ ለመስማት እና የርስዎንም ለማካፈል እንዲሁም ባገር ዉስጥ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እቅድ እና እንቅስቃሴን ለመረዳት በዚህ ዝግጅት ላይ ተካፋይ ይሁኑ!
ተጋባዥ እንግዶች:
(ከአዲስ አበባ)
ዶ/ር መረራ ጉዲና
ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት
አቶ ነጋሲ በየነ
(ከዋሺንግቶን ዲሲ)
አቶ ሀይለገብርኤል አያሌው
አቶ ሄኖክ ጋቢሳ
አወያይ:
አቶ ጥበበ ሳሙኤል
ቀን:       እሁድ Jan 10, 2016    ሰአት:  2pm
ቦታ: 7701 16th St NW, Washington DC, 20012
አዘጋጅ:     የሰማያዊ አንድነት ድጋፍ በሰሜን አሜሪካ
ለተጨማሪ መረጃ: ስልክ፥ (202) 556-3078
ኢሜል፥ info@semayawiusa.org
ድህረ ገጽ፥ www.semayawiusa.org
ይህ ዉይይት የሚካሄደው በአዲስ አበባ እና በዋሺንግቶን ዲሲ በቪዲዮ ግንኙነት ስለሆነ በሁለቱ ከተሞች መካከል ያለዉን የሰአታት ልዩነት ታሳቢ በማድረግ ፕሮግራሙ በሰአቱ የሚጀመር መሆኑን አዘጋጆች ማሳሳብ እንሻለን። እርስዎም ከጥሪው ሰአት ቀደም ብለዉ በመገኝት እንዲተባበሩን በማክበር እንጠይቃለን።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ