ከ 70 እስከ 80 ሺህ ( የባህር ዳር ሕዝብ አንድ አራተኛ) ነዉ ለሰልፍ የወጣው !
በባህር ዳሩ ሰልፍ ከሰባ እስከ ሰማኒያ ሺህ ሕዝብ እንደነበረ አንድነት ገለጸ። ሰልፉ ገነ እንደተጀመረ ወደ 15 ሺ ሕዝብ አካባቢ የነበረ ሲሆን፣ ከሰልፉ መነሻ እስከ መዳረሻዉ በነበረዉ ጎዞ፣ ሕዝቡ እየተቀላቀለ፣ አስደናቂ የሕዝብ ማእበል ሊፈጠር ችሏል። ለሕዝብ ይፋ የሆኑ ታሪካዊ ፎቶግራፎች፣ ቪዲዮዎችም የሚያሳዩት ይሄንኑ ነዉ።
አንድነት ባወጣዉ መግለጫ በባህር ዳር የታየዉ አይነት በአገሪቷ በሙሉ እንደሚቀጣጠል ለዚህም በአገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ድጋፉን እንዲሰጥ ትግሉን እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርቧል።
በባህር ዳር የታየው ምንድን ነው ?
በዋናነት የአገዛዙን ካድሬዎችን አፍ ያዘጋዉ የሕዝቡ ሰላማዊነት ነው። የተወረወረ አንዲት ጠጠር የለም። የተሰበረ ወይንም የወደመ ንብረት የለም። የትጎደ ዜጋ የለም። ያ ሁሉ ሺህ ተሰብስቦ ፣ በሚያኮራ መልኩ ፣ ሕዝቡ በሰላም ወጥቶ ነው በሰላም የገባዉ። ይሄም የአንድነት ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች «ሽብርተኞች» እያሉ ለሚከሱ የአገዛዙ ካድሬዎችና መሪዎች፣ አንድነት ፓርቲ ምን እንደሆነ በድጋሚ ያስመሰከረ ነው።
በባህር ዳሩ ሰልፍ ከሰባ እስከ ሰማኒያ ሺህ ሕዝብ እንደነበረ አንድነት ገለጸ። ሰልፉ ገነ እንደተጀመረ ወደ 15 ሺ ሕዝብ አካባቢ የነበረ ሲሆን፣ ከሰልፉ መነሻ እስከ መዳረሻዉ በነበረዉ ጎዞ፣ ሕዝቡ እየተቀላቀለ፣ አስደናቂ የሕዝብ ማእበል ሊፈጠር ችሏል። ለሕዝብ ይፋ የሆኑ ታሪካዊ ፎቶግራፎች፣ ቪዲዮዎችም የሚያሳዩት ይሄንኑ ነዉ።
አንድነት ባወጣዉ መግለጫ በባህር ዳር የታየዉ አይነት በአገሪቷ በሙሉ እንደሚቀጣጠል ለዚህም በአገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ድጋፉን እንዲሰጥ ትግሉን እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርቧል።
በባህር ዳር የታየው ምንድን ነው ?
በዋናነት የአገዛዙን ካድሬዎችን አፍ ያዘጋዉ የሕዝቡ ሰላማዊነት ነው። የተወረወረ አንዲት ጠጠር የለም። የተሰበረ ወይንም የወደመ ንብረት የለም። የትጎደ ዜጋ የለም። ያ ሁሉ ሺህ ተሰብስቦ ፣ በሚያኮራ መልኩ ፣ ሕዝቡ በሰላም ወጥቶ ነው በሰላም የገባዉ። ይሄም የአንድነት ፓርቲ አባላት እና ደጋፊዎች «ሽብርተኞች» እያሉ ለሚከሱ የአገዛዙ ካድሬዎችና መሪዎች፣ አንድነት ፓርቲ ምን እንደሆነ በድጋሚ ያስመሰከረ ነው።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ