አንድነትና መኢአድ ብአዴንና አመራሮቹን በመቃወም እሁድ የካቲት 16 በባህር ዳር ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ መጥራታቸው ያሳሰበው ገዢው ፓርቲ አቶ አለምነው መኮንን ትላንት ማስተባበያ እንዲሰጡ ማስደረጉ የባህርዳር ነዋሪዎች እንደ አዲስ ሰውውን የጥላቻ ንግግር በስፋት እንዲደመጥ ምክንት መሆኑንን የፍኖተ ነፃነት ዘጋቢ ያነጋገራቸው ከተማዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢያችን በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች እየተዘዋወረ እንደታዘበውም የአቶ አለምነው ንግግር በባህር ዳር እንደ አዲስ የመወያያ አጀንዳ መሆኑን ታዝቧል፡፡ በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎችም በብአዴን ላይ ቁጣቸውን ለመግለፅ እሁድን እየጠበቁ ነው፡፡ ብአዴን ከአቶ አለምነው ማስተባበያ ውስጥ የተቀነጨበ መልእክት የያዘ በራሪ ወረቀት ከትላንት አመሻሽ ጀምሮ በባህር ዳር እንዲሰራጭ በማድረግ ላይ መሆኑ ታወቃል፡፡
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ