መጀመሪያም በፍትህ አዘጋጀች ከዛም በአዲስ ታይምስ መታተም ከጀመረች ጀምሮ በስርአቱ ሎሌዎች ፍትህን ለማዘጋት ያልፈነቀሉት ድንጋይ አልነበረም ከዚህም ውስጥ የአዲስ ዘመን ገፅ 3፣ አይጋ ፎረም፣ዋልታ ፣ እንዲሁም በተረጴዛዋ ሟርተኛ ሚሚ ስብሃቱ የሚመራው ዛሚ ፌፍ ኤም ከነዚህ ውስጥ ይገኛሉ፡፡የሚገርመው የአሁኑ ዘመቻ ከበፊቱ ለየት ያለ መሆኑን ፍንጭ የደረሳቸው የልዕልና አዘጋጀች በልዕልና ጋዜጣ ቅፅ 1 ቁጥር 4 አርብ መጋቢት 13 2005 ባወጡት ፅሁፍ እንዲህ ብለው ነበር‹‹ከዚህ ቀደም ከተለመደው የመፈረጅ ፣ የማስፈራራት ፣ የማጥላላት ፣የማንኳሰስ ዘመቻ ይህንን ለየት የሚያደርገው እንደዚህ ቀደሙ በአዲስ ዘመን፣ በአይጋ ፎረም፣እና ዛሚ ሬዲዮ ጣቢያ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን ፤ በአዲሱ ዘመቻ በ‹‹ግል(ነፃ)›› ስም የሚታተሙ መፅሔቶችንም በተባባሪነት መጠቀምን የሚጨምር እንደሆነ የልዕልና ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡›› እያለ ይቀጥልና በመጨረሻም
‹‹ ልዕልና ነፃ ፕሬሱን ለማፈን ለሚደረገው ኢህአዴግ መራሹ ዘመቻ ‹‹ ነፃ ፕሬስ ››ን እንደ ሽፍን በመጠቀም መፅሔታቸውን በማከራየት የሚተባበሩትንም ሆነ በአዲስ ዘመን እና በአይጋ ፎረም ላይ በብዕር ስም ይህንኑ የአፈና ተግባር የሚፈፅሙትን እየተከታተለች ለአንባቢን ታቀርባለች ፡፡››
የሚገርመው ይህ ፅሁፍ በወጣ በነጋታው ቅዳሜ ነው ሎሚ መፅሔት ‹‹ለተመስገን ደሳለኝ የኢህአዴግ ማስተንፈሻ ማን ነው? በሚል ርዕስ አዲሱን ዘመቻ የጀመሩት ከዚህ ቀደም ካነበብኳቸው የዘለፋ ፅሁፎች የዚኛው በጣም ስልታዊ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ፡፡ ይህም የልዕልናን አዘጋጆች ከገዢው ፓርቲ ጋር እያገናኘ የፃፈው ነው፡፡;ይህን ማንም ሊጠረጥረው የማይችለው እና የተረጋገጠ እውነት የሆው ነገር አምባገነኑ ስርአት የነዚህን አይነት ጋዜጦች መኖር ከናካቴው አይፈልግም የልጁ መከራከሪያ ምን ያህል ዜሮ እንደሆነ የሚያረጋግጠው ጋዜጣው ብርሃንና ሰላምን በመሰሉ ማተሚያ ቤቶች በአነስተኛ ዋጋ ማሳተም እንዳይችሉ አድጎ በተለየ ይዘት እና በውድ ዋጋ እንዲያሳትሙ አስገድዷቸዋል፣ እንዲሁም 30 ሺህ ኮፒ ከታተመ ቦኋላ እንዳይወጣ አድርጎ አቃጥሎታል ፡፡ ይህም የሚያረጋግጠው ስርአቱ እንደ ፍትህ አይነት ጋዜጣዎችን መመልከት አለመፈለጉን ያሳያል፡፡ምንልክሳልሳዊ ብሎግ
ሌላው ደሞ እነእስክንድር ነጋ ጋዜጣ እንዳያወጡ ታግደው ፣የአወራምባ ታይምስ አዘጋጆች አውራምባ ታይመስ ከተዘጋች ቦኋላ ተሰብስበው ሄደው ሌላ ጋዜጣ ለማተም ሳይፈቀድላቸው ለነፍትህ አዘጋጆች ግን በየ 6 ወር በአዲስ ጋዜጣ የሚመላለሱት እነሱ ማን ሆነው ነው አይነት ከስርአቱ ጋር የማያያዝ ነገር ያንፀባርቃል ፡፡ ይህንን ማንም የሚያወቀው ሃቅ ይመስለኛል፡፡ እስክንድር ነጋ የታገደው ዛሬ አይደለም እሱምኖ ሆነ ባለቤቱ የታገዱት ምርጫ 97 ቦኋላ ነው እንጂ ዛሬ አይደለም ልጁም እንዲህ ማለቱ ለተነሳለት የቅጥፈት ተግባር ማለትም ከ97 ቦኋላ የተከፈቱትን አዲስ ነገር ፣ አውራምባ ታይምስ ፣ ፍትህ ፣ አዲስ ታይምስ እንዲሁም አሁን በነብስ ያለችውን ልዕልናን ገዢው ፓርቲ በማስተንፈሻነት እንደሚጠቀምባቸው ለመግለፅ ፈልጎ ነው ይህም የሎሌ እና የአድርባዮች ተላላኪ መሆኑን በደንብ የሚያሳይ ነው፡፡ ከዚህም ውስጥ 4ቱ በህትመት የሉም ታድያ እንዴት ሆነው ነው በህትመት ሳይኖሩ ማስተንፈሻ የሆኑት ደሞም እነዚህ ጋዜጦች በህትመቱ ለመዝለቅ የቻሉት ስርአቱን በማስገደድ ነው እንጂ ስርአቱ ፈልጎ እንዳልሆነ ሰይጣንም ያውቀዋል፡፡
ሌላው ደሞ ሌሎች ተከልክለው ፍትህ በአዲስ ታይመስ አሁንም በልዕልና ይመላለሳሉ የሚል ነው ፡፡ ይህም ቢሆን ምንም እውነትነት የሌለው ነው፡፡ ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ የፍትህ አዘጋጆች ፍትህ የሚሰደዱ እግሮች የሏትም ብለው በቁርጠኝነት መነሳታቸው ለስርአቱ አንንበረከክም ማለታቸውን የሚያሳይ ነው ፤ ይህም አንዱ በር ቢዘጋ በአንዱ መምጣታቸው ነገር ለፕሬሱ የሚያስብ ሰው ቢሆን በመልካም ጎኑ ሊያየው በተገባ ግን ምን ዋጋ አለው አቶ ታዲዮስ ታንቱ እንዳሉት አድርባይ እንዴት ሀገር ሊጠቅም ይችላል? ሲሉ የጠየቁት መጣልኝ እውነትዎን ነው አቶ ታድዮስ በምንም መንገድ አድርባይ አገር ሊጠቅም አይችልም ፡፡ ብሮድካስትም ሆነ አንባገነኑ መንግስት ለነሱ አዲስ የጋዜጣ ፍቃድ እንደማይሰጣቸው እርግጠኛ ስለሆኑ ወደህትመት ለመመለስ ሌላ አማራጭ መውሰድ ግድ ስለሆነባቸው ነው ከህትመት የወጡትን ጋዜጦችና መፅሔቶች እየገዙ ለመመለስ የተዘጋጁት ይህም እንደሚመስለለኝ በንግድ ህጉ መሰረት ባለቤትነትን ማዘዋወር በመሆኑ ለአፈና ብዙም ያልተመቸ በመሆኑ እንጂ ስርአቱ የነሱን መኖር ስለሚፈልግ አይደለም፡፡
ተመስገንን እና የልዕልና አዘጋጆችን እራሳቸውን እንደ እውነተኛ ሌላውን እንደሎሌ ያያሉ የሚል ነው፡፡ ይህ እኮ እሙን የሆነ ነገር ነው ለምሳሌ ሪፖርተር እና አዲስ አድማስ ጋዜጦች ከ 97 ሱናሚ አምልጠው አስራምናምን አመት መቆየታቸው በምን ምክንያት እደሆነ ሳያውቅ ነው እንግዲህ የፍትህ 4 አመት የአዲስ ታይምስ 6 ወር መቆት ያንገበገበው ይህ ደሞ ግልፅ ነው በ2004 መጨረሻ ፍትህ የጠቅላዩን ሞት ይዛ ስለወጣች ስትታገድ አዲስ አድማስ እና ሪፖርተር አንድ ግዜ ጠቅላይ ሚንስትሩ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ አንድ ግዜ ከህመማቸው አገግመው በቤተመንግስት አመራር እየሰጡ ነው እያሉ ውሸት ሲዘባርቁ ነበር ይሄ በራሱ ተመስገንም ሆነ የልዕልና አዘጋጆች ያሉት እውነት መሆኑን ያሳያል፡፡ ይህ ሲባል ግን ከልእልና ውጪ ያሉ ጋዜጦችን እና መፅሔቶችን የስርዐቱ ሎሌዎች ናቸው ማለት አይደለም፡፡
እንግዲህ ለዚህ ሎሌ አዲስ ነገር ፣ አውራምባ ታይምስ ፣ ፍትህ ፣ አዲስ ታይምስ አይነት የዕውነት ነፃ ፕሬሶች የህብረሰቡን ንቃተህሊና በማጎልበት ሰርተው ያለፉትን እንዲሁም ልዕልና አሁን እየሰራችው ያለቸውን ስራ ለሱ ምንም አለመሆኑ እሙን ነው ለኛ ግን ብዙ ነገሮቻችን ናቸው ወደፊት በሁሉም መንገድ አድጋ በልፅጋ ማየት ለምንፈልጋት ኢትዮጵያ የነዚህ አይነት ጋዜጦች መኖራቸው ግድ ነው!!
ከ97 ሱናሚ ቦኋላ ተከፍተው አሁን በህትመት የሌሉ ጋዤጦች አዲስ ነገር፣አውራምባ ታይምስ፣ጉግል፣ ፍትህ፣ፍኖተ ነፃነት፣ ነጋድራስ፣አዲስ ታይምስ ፣አዲስ ወሬ፣መሰናዘሪያ፣ኢትዮ ምሕዳር ወ.ዘ.ተ ይህም የሚያሳየው ስርዐቱ ፕሬሱን ምን ያህል እንደ ጦር እንሚፈራው ነው፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ ፕሬሱ አሁን ሰለሚገኝበት ሁኔታ ለመገንዘብ በልዕልና ጋዜጣ ቁጥር 3 የ‹‹ፍትህ›› ወደ ‹‹አዲስ ታይምስ›› ከዚያም ወደ ‹‹ልዕልና ›› መቀየር ፤ የመንግስት ‹‹ትልቅነት›› ወይስ ‹‹ትንሽነት›› ማሳያ? በሚል ብርሀኑ ደቦጭ የፃፈውን ፅሁፍ ማንበብ በጣም ጠቃሚ ነው!!
ከ97 ሱናሚ ቦኋላ ተከፍተው አሁን በህትመት የሌሉ ጋዤጦች አዲስ ነገር፣አውራምባ ታይምስ፣ጉግል፣ ፍትህ፣ፍኖተ ነፃነት፣ ነጋድራስ፣አዲስ ታይምስ ፣አዲስ ወሬ፣መሰናዘሪያ፣ኢትዮ ምሕዳር ወ.ዘ.ተ ይህም የሚያሳየው ስርዐቱ ፕሬሱን ምን ያህል እንደ ጦር እንሚፈራው ነው፡፡
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ