ሐሙስ 30 ኤፕሪል 2015

በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ላይ የሚፈፀመው ድብደባ ቀጥሏል


ምርጫውን ተከትሎ በሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ላይ የሚፈፀመው ድብደባ ተጠናክሮ መቀጠሉን የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ትናንት ሚያዝያ 21/ 2007 ዓ.ም በምስራቅ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ፀኃፊ የሆነው አቶ ሳሙኤል አወቀ በደህንነቶች ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመበት ኃላፊው ገልጾአል፡፡ አቶ ሳሙኤል ከምሽቱ 2 ሰዓት ላይ ወደ ቤቱ እየገባ በነበረበት ወቅት ሁለት ደህንነቶች አፍነው በመውሰድ ከሌሎች አራት ደህንነቶች ጋር በመሆን ከፍተኛ ድብደባ ፈጽመውበታል፡፡ ደህንነቶች ‹‹እንፈልግሃለን!›› ብለው ከወሰዱት በኋላ ‹‹ለምን አርፈህ አትቀመጥም?›› እያሉ ድብደባ እንደፈፀሙበትም አቶ ሳሙኤል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
በተመሳሳይ የደ/ጎ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ሰብሳቢና የፎገራ ወረዳ የተወካዮች ም/ቤት እጩ ተወዳዳሪ አቶ አለማየሁ አደመ ላይ ከፍተኛ የሆነ ድብደባ እንደተፈፀመበት ተገልጾአል፡፡ ደህንነቶች አቶ አለማየሁ በሚኖርበት ደራ ወረዳ አርብ ገበያ ከተማ ሚያዝያ 20/2007 ዓ.ም ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ደብደባ ፈጽመውበታል፡፡ አቶ አለማየሁ ድብደባው በተፈፀመበት አርብ ገበያ ጤና ጣቢያ እየተረዳ የነበር ቢሆንም ጉዳቱ ከፍተኛ በመሆኑ ወደ ባህርዳር ሪፈራል ሆስፒታል መዛወሩ ታውቋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ የምዕራብ ጎጃም ዞን አስተባባሪ የሆነው አቶ አዲሱ ጌታነህ መንግስት አይ ኤስ በኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን ግድያ ለመቃወም ባህርዳር ከተማ ላይ በጠራው ሰልፍ ተገኝቶ ከተመለሰ በኋላ ምሽት ላይ ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመበት መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ቅዳሜ 25 ኤፕሪል 2015

እሥላማዊ መንግሥት ነኝ በሚለው ፅንፈኛ የሽብር ቡድን ሊብያ ውስጥ ለተገደሉ መታሰቢያ በዋይት ሃውስ ደጅ የተዘጋጀ ሻማ የማብራት ሥነ-ሥርዓት




Letter from an Ethiopian prison to John Kerry

Letter from an Ethiopian prison to John Kerry

April 24, 2015

Natnael Feleke has been imprisoned for a year without trial. In a letter smuggled out of jail, he asks the US secretary of state to stop supporting the Ethiopian regime

by Natnael Feleke from Kilinto prison | The Guardian
US secretary of state John Kerry with blogger Natnael Feleke
US secretary of state John Kerry with blogger Natnael Feleke in Addis Ababa, 2013. Photograph: Endalk Chala
Dear John Kerry,
I first came to know about you back in 2004, during the US presidential election, when you were running for office against George Bush. At just 17 years old I knew little about US politics – or politics in general – but I discussed the campaigns with my schoolmates.
A year later, the historic 2005 Ethiopian national election took place. This election differed from previous votes in that the lead up to it was mostly democratic. This left many Ethiopians hoping they would witness the first elected change of government in the country’s history. But it was not to be.
After the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front realised they couldn’t win the election without rigging the vote, the true face of the regime emerged.
After polling day, we saw civilian bloodshed, and the arrest of thousands – including journalists and opposition leaders.
I was only young then, but the election gave me my first real experience of politics. It also left me with a strong desire to follow the repressive situation that was unfolding in Ethiopia.
It was this interest and commitment that led my friends and I to form the bloggers’ and pro-democracy activist group we called Zone 9.
The birth of Zone 9
All nine members of the blogging group are young and passionate about encouraging Ethiopia’s democracy.
We aimed to create a platform for Ethiopian youth to discuss political, economic and social issues when we launched our blog, with the motto, “we blog because we care”.
Although our arrest came two years after launching, our site was blocked in Ethiopia early on, but we continued to share our views via social media.
Finally, the regime took drastic measures: in April 2014 they arrested six members of Zone9, and three other journalists too.
We are now facing between eight and 18 years imprisonment.
This hasn’t come as a surprise. Whenever Ethiopians exercise their constitutional rights to free expression, the regime resorts to its security apparatus to silence them.
My charges are tied up with our meeting back in 2013. We met in Addis Ababa University: the minister of foreign affairs Tedros Adhanom invited me and a couple of others for a discussion, in which I raised my concerns about the regime’s tactics to push young citizens away from participating in politics.
I highlighted the negative impact this was having on the political sphere. I told you that I was risking a lot merely by expressing my thoughts freely. At that time, my arrest was only an abstract possibility.
An Ethiopian court granted police 10 more days to investigate six bloggers and journalists
All members of Zone9 (left to right): Endalk Chala, Soliyana Shemeles, Natnael Feleke, Abel Wabela, Befeqadu Hailu, Mahlet Fantahun, Zelalem Kibret, Atnaf Birahane, Jomanex Kassaye. Photograph: Endalk Chala
The conditions
The regime continues to silence any form of dissent using the strict anti-terrorism proclamation.
Since the 2005 Ethiopian election the government have prosecuted more than 200 people – journalists, dissidents and activists – and has shut down many weekly magazines and newspapers, sending most journalists into exile.
In the last eight months alone 17 journalists have been forced to flee the country.
This has made it nearly impossible for citizens to exercise their constitutional rights.
It is quite common for the federal police and the national intelligence and security service (Niss) to use force to solicit confessions from suspects. My friends and I fell victim to this type of mistreatment at the police crime investigation sector, commonly known as Maekelawi.
The abuses they are reported to have committed there include beatings with electric wire, forcing heavy physical exercise, lengthy interrogations with no rest, and keeping people in solitary confinement until suspects agree to incriminate themselves, or others. The mistreatment is more extreme under Niss.
My fellow bloggers and I spent the first 85 days of our arrest at the police station. We were given a 20-minute toilet break twice a day. In case of emergency, we found an understanding officer, or a bucket.
The rooms were crowded, filled with suspects from all over the country. We slept and ate in the little space available.
The suffocation was sometimes unbearable.
Halt the millions
The investigation has so far been a farce.
I have been, for instance, repeatedly asked what kind of relationship I had with you, and why I was invited to ask a question on the BBC’s Hardtalk program, hosted by Zeinab Bedawi, when it was filmed in Addis Ababa in May 2013 to mark the 50th anniversary of the African Union.
But to be honest, the amount of time I will be spending in prison is not the most pressing issue on my mind right now. Rather, I am worried about what will happen unless the international community, and specifically your government, assumes a firm stance on Ethiopia, demands progress with democratisation, and halts the millions of dollars pouring the regime’s way.
Having said this, I want to assure you that I understand the question of liberty and democracy in Ethiopia should be primarily answered by Ethiopians ourselves.
Ultimately, it is the “willingness to suffer and sacrifice [for our cause]”, in the words of Nelson Mandela, that will determine our fate.
Your sincerely,
Natnael Feleke

ረቡዕ 22 ኤፕሪል 2015

people have rallied in Ethiopia's capital, Addis Ababa



Tens of thousands of people have rallied in Ethiopia's capital, Addis Ababa, against the killing of more than 20 of their nationals by Islamic State (IS) militants in Libya. "We want revenge for our sons' blood," the protesters chanted. The demonstrators also accused the government of failing to tackle poverty, saying the killed group was probably in Libya in the hope of reaching Europe.   BBC Africa


A young Ethiopian girl beaten unconscionable by the federal police is being taken to hospital. ራስዋን እስክትስት ድረስ በፌዴራል ፖሊስ የተቀጠቀጠችው አንዲት ወጣት ኢትዮጵያዊት ወደሆስፒታል ተወስዳለች። በአሰቃቂ ሁኔታ ተደብድባ ራስዋን የሳተችው ሌላዋ ኢትዮጵያዊት ደግሞ 14 ዓመት የማይሞላት ልጅ ነች። እነዚህ ለጋ ወጣቶች ከቤታቸው በጥዋት የወጡት በሊቢያ ለታረዱት ወገኖቻቸው ሀዘናቸውን በሰላም ለመግለጽ ነበር። የ"ኢትዮጵያ መንግስት" ነኝ የሚል አካል በዚህ ሁኔታ ይጨፈጭፈናል ብለው አላሰቡም ነበር።



ማክሰኞ 21 ኤፕሪል 2015

በአዲስ አበባ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው፣ ሰልፈኛው በሊቢያ የኢትዮጵያውያንን መገደልና መንግስት ያሳየውን ቸልተኛነት በመቃወም ላይ ነው

ሰበር ዜና፣ ሰልፈኛው የኢቲቪ/ ኢብኮ ጋዜጠኞችን ደበደበ ****

(ነገረ-ኢትዮጵያ) ከደቂቃዎች በፊት የኢቲቪ/ ኢብኮ ጋዜጠኞች በለቀስተኞች መደብደባቸው ተሰምቷል፡፡ የኢትቪ /ኢብኮ ጋዜጠኞች ለቅሶ ቤት ውስጥ ቀረጻ አድርገው ሲመለሱ ‹‹ሌቦች እናንተ ልታስተላልፉት አይደለም፡፡ ስለ እኛ ምን አገባችሁ?›› ተብለው እንደተደበደቡ ለማወቅ ተችሏል፡፡
—————————
በሊብያ አሸባሪዎች በኢትዮጵያውያን ላይ የፈጸሙትን አሰቃቂ ግድያ ለማውገዝና መንግስት ነኝ ባዩ ወያኔ ያሳየውን ቸልተኛነት ለመቃወም በአዲስ አበባ ህዝቡ ነቅሎ አደባባይ ወጥቷል።
ይሁንና ፖሊስ እንደተለመደው ሰልፉን ለመበተን ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፣ ነገረ-ኢትዮጵያ እንደዘገበው ከሆን ፖሊስ ሰልፈኛውን በዱላ መደብደብ ጀምሯል።
ሰልፉ ከፖሊሶቹ ቁጥጥር በላይ ሆኗል፣ በርካታ ህዝብ እየጮኸ እና እያለቀሰ ሰልፈኛውን መቀላቀሉን ቀጥሏል።
ሰልፈኞቹ ከሚያሰሙት መፈክሮች መካከል፣
‹ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስት የለም!››
‹‹መንግስት የሌለው ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው!››
‹‹የወንድሞቻችን ደም በከንቱ ፈሶ አይቀርም!››
‹‹የወንድሞቻችን ደም ውሃ አይደለም!››
ሰልፈኛው በተለይ ወጣቱ በቁጭት ለሟቾቹ ትኩረት ያልሰጠው መንግስት ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ እያሰማ ነው!
‹‹ሌባ! ሌባ!ሌባ! ሌባ!ሌባ! ሌባ!››
ሰልፉ ቀጥሏል፣ ፖሊስ ሰዎች ሰልፈኛውን እንዳይቀላቀሉ ጥረት እያደረገ ነው።

ለቀጥታ ዘገባ የፌስቡክ ገጻችንን ይከታተሉ

Addis Ababa protest against Ethiopian government
Porotest in Addis Ababa, against ISIS and Ethiopian government
protest in Addis Ababa

ሰኞ 20 ኤፕሪል 2015

ኢትዮጵያውያን የሀገራችንና የራሳችን ክብር እና ደህንነት ማስጠበቅ ካለብን መጀመሪያ ሀገራችን ላይ የሚገኘውን ስርዓት በፅኑ መታገል የግድ ይለናል”ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ገለጸ።

ሚያዝያ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፓርቲው ፦«ከራሳችን ውጪ ለችግራችን ደራሽ መንግስት የለንም!»በሚል ርእስ በየመንና በደቡብ አፍሪካ በሚገኚ ኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጥቃት አስመልክቶ ባወጣው ወቅታዊ መግለጫ ፣የኢትዮጵያውያን የውርደት ዘመን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ሰሞኑን ከተከሰተው እጅግ አስከፊ ሁኔታ ላይ አድርሶናል ብሏል።
“የመን ውስጥ በተከሰተው ጦርነት ተጎጂ የሆኑትን የውጭ ዜጎች መንግስታቶቻቸው ቀድመው ሲያስወጡ ለኢትዮጵያውያን ግን የሚደርስላቸው አልተገኘም”ያለው ሰማያዊ ፓርቲ፤ ይህንንውርደትም ወገኖቻችን «የመን ውስጥ የቀረነው እኛና ውሻ ብቻ ነን» ሲሉ እጅግ በሚያሳዝን መልኩ እንደገለጹት አውስቷል። “ ኢትዮጵያውያን ላይ የመድፍ፣ የሞርታርና የአውሮፕላን ድብደባ ሲዘንብባቸው በመከራ ላይ ያሉት ኢትዮጵያውያን ስልክ እንዲደውሉ በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ ከማላገጥ ውጭ ምንም ያላደረገው የህዝብን ስልጣን በሀይል የተቆጣጠረው ገዥው ፓርቲ ፤ ይባስ ብሎ ለራሱ ስልጣን ይጠቅሙኛል ያላቸውን የጦርነቱን ተሳታፊዎች ደግፎ መግለጫ መስጠቱ- የኢትዮጵያውያንን ስቃይ እጥፍ ድርብ አድርጎታል”ብሏል። በአጭሩ ኢህአዴግ ለራሱ ጥቅም ሲል ብቻ በማያገባውና በማይወጣው ዓለም አቀፍ ጦርነት ውስጥ ሀገራችንን ሲዘፍቅ ፤ ጦርነቱን ያወጀው፦ የሚደርስላቸው ባጡ ምስኪን ኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያ ላይ ነው ብሏል-ሰማያዊ ፓርቲ።
በየመን የተከሰተውን መርዶ ሰምተን ሳንውል ሳናድር ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ አስደንጋጭ አደጋና እና ሰቆቃ ልንሰማ ተገደናል የሚለው የፓርቲው መግለጫ፤ኢትዮጵያውያንሀብትና ንብረታቸው መዘረፉ ሳያንስ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው ሲያልፍ በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ተከታትለናል ብሏል።
የዚህ አሰቃቂ አደጋ ሰለባ የሆኑ የሌሎች ሀገራት ዜጎች በቶሎ ከደቡብ አፍሪካ ሲወጡ፣ እንዲሁም ሀገራቱ ዜጎቻቸውን መታደግ ያስችላል ያሉትን መፍትሄዎች ሲያስቀምጡ እና ሲያስጠነቅቁ ቢደመጥም፤ ኢህአዴግ ግን እንደተለመደው የኢትዮጵያውያንን ሰቆቃና ስቃይ ከምንም እንዳልቆጠረው በግልፅ እየታየ ነው ሲልም ሰማያዊ ፓርቲ ቁጣውን ገልጿል።
በእርግጥ ላለፉት 24 ዓመታት ኢህአዴግ ሀገር ውስጥ የሚኖሩትን ዜጎች ሲያሰቃይ፣ በውጭ የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያንም የሆነ ያልሆነ ስም እየለጠፈ በጠላትነት ሲፈርጃቸው እንደቆየ አይተናል ያለው ፓርቲው፤ ኢህ አደግ  ከኢትዮጵያውያን ይልቅ የራሱን የግል ጥቅም ሲያሳድድም መቆየቱን አውስቷል።
በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሱ ባሉት ተደጋጋሚ ግፎች ተሸፈነ እንጅ ሰሞኑን ሌላ ኢህአዴግ ለዜጎች እንደማይጨነቅ የታየበት ክስተት እየተፈፀመ ያወሳው ሰማያዊ ፓርቲ፤  ኢህአዴግ ለሱዳን መንግስት አሳልፎ በሰጠው ሰፊና ለም የሀገራችን ሉዓላዊ መሬት አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ሌላ አሳፋሪ እና አሰቃቂ ወንጀል እንደተፈፀመ ምመዘገቡን ጠቅሷል። “ኢትዮጵያውያን የሀገራችንና የራሳችን ክብር እና ደህንነት ማስጠበቅ ካለብን መጀመሪያ ሀገራችን ላይ የሚገኘውን ስርዓት በፅኑ መታገል የግድ ይለናል።”ያለው ሰማያዊ ፓርቲ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ምቹ አስተዳደር፣ ዴሞክራሲያዊና ለዜጎች የሚያስብ ስርዓት ቢኖር መጀመሪያውኑም ወገኖቻችን በገፍ ለአደጋ ወደሚጋለጡባቸው አካባቢዎች ባልተሰደዱ ነበር።”ብሏል።  በመሆኑም በቅድሚያ ክብራችንን ለማስመለስ የነፃነት ትግሉን አጠናክረን መቀጠል አልብን ብሏል-ፓርቲው። ሰማያዊ ፓርቲ አክሎም፦“ክብራችንን ልናስመልስ የምንችለው ሀገራችን ውስጥ እንዳንኖር ያደረገንን ስርዓት ቀይረን አንድም በገዛ አገራችን መኖር ስንችል፣ አንድም በአደጋ ወቅት ሊደርስልን የሚችል ተቆርቋሪና ለዜጎች የሚያስብ መንግስት መመስረት ስንችል ብቻ መሆኑን ልንገነዘበው ይገባል።”ብሏል።

ማክሰኞ 14 ኤፕሪል 2015

እነ ብርሃኑ ተክለያሬድ የርሃብ አድማ ጀመሩ


ሚያዝያ ፭(አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በማእከላዊ እስር ቤት ውስጥ ታስረው ከሚገኙት ፖለቲከኞችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች መካከል ወጣት ብርሃኑ ተክለያሬድና ፍቅረማርያም አስማማው የረሃብ አድማ ጀምረዋል። የረሃብ አድማው መንስኤ ወጣት
እየሩሳሌም ተስፋው በቤተሰቦቿ የመጎብኘት ፈቃድ በመከልከሏ፣ በማእከላዊ እስር ቤት ውስጥ ለብቻዋ ታስራ ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተፈጸመባት በመሆኑ፣ ድርጊቱን ለመቃወም ነው።
ወጣት ብርሃኑና ፍቅረማርያም በምርመራ ወቅት ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ምንጮች ገልጸዋል። በአሁኑ ጊዜ ቃላቸውን ሰጥተው ድብደባው የቆመላቸው ቢሆንም፣ በእየሩሳሌም ላይ የሚደርሰው ስቃይ ግን እንደጨመረ ነው።
በእየሩሳሌም ላይ የሚደርሰው ስቃይ እስካላበቃና ቤተሰቦቿ እንዲያዩዋት እስካልተፈቀደ ድረስ በረሀብ አድማው እንደሚገፉት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ገልጸዋል።
ብርሃኑ ተክለያሬድ ፣ እየሩሳሌም ተስፋውና ፍቅረማርያም አስማማው ከዚህ ቀደም በተለያዩ ሰላማዊ ሰልፎች ላይ በመሳተፋቸው ታስረው ተደብድበዋል።
ወጣቶቹ በምን ምክንያት እንደታሰሩ እስካሁን በይፋ መግለጫ የሰጠ አካል የለም። ይሁን እንጅ በቅርቡ ፍርድ ቤት በቀረበቡበት ወቅት፣ ሶስቱም ወጣቶች ከግንቦት7 ጋር በተያያዘ መከሰሳቸው ተገልጿል።

ቅዳሜ 4 ኤፕሪል 2015

የመኢአድ አመራሮች አዲስ አበባ ማዕከላዊ ይገኛሉ


ስለነ ዘመነ ምህረት አዲስ ነገር
ለገሰ ወ/ሃና
ዘመነ ምህረት ; መለሰ መንገሻ እና ሌሎች ጥር 10/2007 ዓም ከጎንደር ተይዘው አዲስ አበባ ማዕከላዊ ይገኛሉ ሰሞኑን በርካታ ወጣቶች ከሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተይዘው እየገቡ እንደሆነ መረጃ ደርሶኛል
ዘመነ ምህረት ከጥር 10/2007 ጀምሮ ላለፉት 75 ቀናት ማዕከላዊ ቁ 84/10 ጨለማ ቤት እንደሚገኝ ታውቋል ድሮ በዚህ ክፍል ውስጥ የመአሕድ መስራችና በኋላ የመኢአድ የአስተዳደርና ፋይናንስ ክፍል ሀላፊ የነበሩት አቶ ገብረፃዲቅ ሀይለማሪያም ታስረውበት የነበረ ነው ዛሬ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ም/ል ፕሬዝደንትና የሰሜን ቀጠና ሀላፊ ዘመነ ምህረት ታስሮበት ይገኛል 84/09 ኢንጂነር ሀይሉ ሻውል ታስረውበት የነበረ የዛሬውን ተራኛ አልታወቀም 84/08 ዛሬ ማን እንዳለበት አላውቅም በፊት ሻለቃ ጌታቸው መንግስቴ ታስረውበት የነበረ ነው ሌላው 84/07 አቶ ማሙሸት አማረ ታስረውበት የነበረ ነው የነዚህ ክፍሎች በር ሲዘጋና ሲከፈት የሚፈጠረው ድምጽ እኳን የተኛ የሞተም የሚቀሰቅስ ይመስለኛል ያሉኝ አሉ ሌላው በዚህ ክፍል ውስጥ የሚገኝ እስረኛ በካቴና ይታሰራል ቅዝቃዜው ውሃን ወደ በረዶነት የመቀየር አቅም ሳይኖረው አይቀርም ብለውኛል የቀመሱት በተመሳሳይ መንገድ መለሰ መንገሻም 84/06 ይገኛል ቀደም ሲል በዚሁ ክፍል ታስረውበት የነበሩ ሰዎች እንደነገሩኝ በነሱም (በአሳሪዎቹም) እንደሚታመነው አንድ ሰው በነዚህ ክፍልሎች ውስጥ ከ27 ቀን በላይ በዚህ ክፍል ውስጥ ከቆየ የአይን ብርሀኑ ሙሉ ጤናማ እንደማይሆን ይታመናል በነዚህ ክፍልሎች ምንም አይነት የተፈጥሮ ብርሃን አያገኙም እነዚህ ክፍልሎች ከ1984 ዓም ጀምሮ በርካታ የመአሕድና የመኢአድ አመራሮችና አባላት ታስረውበት የነበረ ነው እነዛ ክፍልሎች ታስረው የወጡ ታሳሪዎች እንዳጫወቱን ከክፍሉ ቅዝቃዜ የተነሳ ለከፋ የጤና ችግር ተዳርገው እንዳሉ በዚሁ ምክንያት ያጡትን ጤና ለመመለስ እውጭ ሀገር ድረስ ሄደው ቢታከሙም መዳን እንዳልቻሉ ገልፀውልኛል
እነ ዘመነ ምህረት ላለፉት 2 ወር ከ15 ቀን በነዚሁ ክፍሎች ውስጥ ሌሊትና ቀን እጅና እግራቸው በካቴና ታስሮ በመከራና በስቃይ እንዳሳለፉ ይገመታል ።
ሰው ሆኖ በሰው ልጅ ላይ ሊደርስ ይችላል ተብሎ የማይታመንና አለም በሙሉ በአስከፊነቱ ያስወገደውን ኢሰብአዊ ድርጊት በነዚህ ወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመባቸው ለመሆኑ የጉዳዩ ባለቤቶች ገልፀዋል ።
ለሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች
ማዕከላውይ በሚባለውና በሌሎች ማሰቃያ ቦታዎች እጅግ በጣም ብዙ ቁጥር ያላቸው የመኢአድ አመራርና አባላት ያሉበት ሁኔታ በመኖርና ባለመኖር መካከል ያሉ ስለሆነ የነዚህን ወገኖቻችን ጉዳይ በመከታተል ባላችሁ ሀላፊነት መሠረት በናንተ ላይ ወድቋል የሚቻለውን ሁሉ ጥረት ታደርጉ ዘንድ ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችሁ ጥሪያችንን እያስተላለፍን ሀላፊነታችሁን ትወጡ ዘንድ እናሳስባለን ።

ኢ/ር ይልቃል ከአገር አንዳይወጡ የተከለከሉበትን ምክንያት የሚነግራቸው ማጣታቸው ተዘገበ



መጋቢት ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሰማያዊ ፓርቲ ሊ/መንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ወደ አሜሪካ ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ በደህንነት ሰዎች እንዲሰረዝ ከተደረገ በሁዋላ፣ እስካሁን ድረስ ምክንያቱን የሚነግራቸው አካል መጥፋቱን ሊ/መንበሩ
ለነገረ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የኢሜግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ መስሪያ ቤት ‹‹ፓስፖርቱ እኛ ጋር አልደረሰም፡፡ ቆይተው ደውለው ይጠይቁ››  ብለው ስልክ እንደሰጧቸው የገለጹት ኢ/ር ይልቃል፣ ይህም ሆን ተብሎ ጉዞውን ለማጓተት የተደረገ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹ይህን ሁሉ የሚያደርጉት አገር የማስተዳደር
ብቃት ስለሌላቸው፣  የፖለቲከኛን እንቅስቃሴ በማጓተትና በማገድ የተፈጠረባቸውን ስጋት የሚቀርፉ ስለሚመስላቸው ነው፡፡  ከአቅመ ቢስነታቸው የመነጨ ነው›› ሲሉ ለጋዜጣው ተናግረዋል፡፡
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ሰማያዊ ፓርቲ በውጭ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ያለው ተቀባይነት ገዢውን ፓርቲ እንዳስፈራውም አክለዋል።