ስለነ ዘመነ ምህረት አዲስ ነገር
ለገሰ ወ/ሃና
ዘመነ ምህረት ; መለሰ መንገሻ እና ሌሎች ጥር 10/2007 ዓም ከጎንደር ተይዘው አዲስ አበባ ማዕከላዊ ይገኛሉ ሰሞኑን በርካታ ወጣቶች ከሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተይዘው እየገቡ እንደሆነ መረጃ ደርሶኛል
ዘመነ ምህረት ከጥር 10/2007 ጀምሮ ላለፉት 75 ቀናት ማዕከላዊ ቁ 84/10 ጨለማ ቤት እንደሚገኝ ታውቋል ድሮ በዚህ ክፍል ውስጥ የመአሕድ መስራችና በኋላ የመኢአድ የአስተዳደርና ፋይናንስ ክፍል ሀላፊ የነበሩት አቶ ገብረፃዲቅ ሀይለማሪያም ታስረውበት የነበረ ነው ዛሬ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ም/ል ፕሬዝደንትና የሰሜን ቀጠና ሀላፊ ዘመነ ምህረት ታስሮበት ይገኛል 84/09 ኢንጂነር ሀይሉ ሻውል ታስረውበት የነበረ የዛሬውን ተራኛ አልታወቀም 84/08 ዛሬ ማን እንዳለበት አላውቅም በፊት ሻለቃ ጌታቸው መንግስቴ ታስረውበት የነበረ ነው ሌላው 84/07 አቶ ማሙሸት አማረ ታስረውበት የነበረ ነው የነዚህ ክፍሎች በር ሲዘጋና ሲከፈት የሚፈጠረው ድምጽ እኳን የተኛ የሞተም የሚቀሰቅስ ይመስለኛል ያሉኝ አሉ ሌላው በዚህ ክፍል ውስጥ የሚገኝ እስረኛ በካቴና ይታሰራል ቅዝቃዜው ውሃን ወደ በረዶነት የመቀየር አቅም ሳይኖረው አይቀርም ብለውኛል የቀመሱት በተመሳሳይ መንገድ መለሰ መንገሻም 84/06 ይገኛል ቀደም ሲል በዚሁ ክፍል ታስረውበት የነበሩ ሰዎች እንደነገሩኝ በነሱም (በአሳሪዎቹም) እንደሚታመነው አንድ ሰው በነዚህ ክፍልሎች ውስጥ ከ27 ቀን በላይ በዚህ ክፍል ውስጥ ከቆየ የአይን ብርሀኑ ሙሉ ጤናማ እንደማይሆን ይታመናል በነዚህ ክፍልሎች ምንም አይነት የተፈጥሮ ብርሃን አያገኙም እነዚህ ክፍልሎች ከ1984 ዓም ጀምሮ በርካታ የመአሕድና የመኢአድ አመራሮችና አባላት ታስረውበት የነበረ ነው እነዛ ክፍልሎች ታስረው የወጡ ታሳሪዎች እንዳጫወቱን ከክፍሉ ቅዝቃዜ የተነሳ ለከፋ የጤና ችግር ተዳርገው እንዳሉ በዚሁ ምክንያት ያጡትን ጤና ለመመለስ እውጭ ሀገር ድረስ ሄደው ቢታከሙም መዳን እንዳልቻሉ ገልፀውልኛል
እነ ዘመነ ምህረት ላለፉት 2 ወር ከ15 ቀን በነዚሁ ክፍሎች ውስጥ ሌሊትና ቀን እጅና እግራቸው በካቴና ታስሮ በመከራና በስቃይ እንዳሳለፉ ይገመታል ።
ሰው ሆኖ በሰው ልጅ ላይ ሊደርስ ይችላል ተብሎ የማይታመንና አለም በሙሉ በአስከፊነቱ ያስወገደውን ኢሰብአዊ ድርጊት በነዚህ ወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመባቸው ለመሆኑ የጉዳዩ ባለቤቶች ገልፀዋል ።
ለገሰ ወ/ሃና
ዘመነ ምህረት ; መለሰ መንገሻ እና ሌሎች ጥር 10/2007 ዓም ከጎንደር ተይዘው አዲስ አበባ ማዕከላዊ ይገኛሉ ሰሞኑን በርካታ ወጣቶች ከሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተይዘው እየገቡ እንደሆነ መረጃ ደርሶኛል
ዘመነ ምህረት ከጥር 10/2007 ጀምሮ ላለፉት 75 ቀናት ማዕከላዊ ቁ 84/10 ጨለማ ቤት እንደሚገኝ ታውቋል ድሮ በዚህ ክፍል ውስጥ የመአሕድ መስራችና በኋላ የመኢአድ የአስተዳደርና ፋይናንስ ክፍል ሀላፊ የነበሩት አቶ ገብረፃዲቅ ሀይለማሪያም ታስረውበት የነበረ ነው ዛሬ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ም/ል ፕሬዝደንትና የሰሜን ቀጠና ሀላፊ ዘመነ ምህረት ታስሮበት ይገኛል 84/09 ኢንጂነር ሀይሉ ሻውል ታስረውበት የነበረ የዛሬውን ተራኛ አልታወቀም 84/08 ዛሬ ማን እንዳለበት አላውቅም በፊት ሻለቃ ጌታቸው መንግስቴ ታስረውበት የነበረ ነው ሌላው 84/07 አቶ ማሙሸት አማረ ታስረውበት የነበረ ነው የነዚህ ክፍሎች በር ሲዘጋና ሲከፈት የሚፈጠረው ድምጽ እኳን የተኛ የሞተም የሚቀሰቅስ ይመስለኛል ያሉኝ አሉ ሌላው በዚህ ክፍል ውስጥ የሚገኝ እስረኛ በካቴና ይታሰራል ቅዝቃዜው ውሃን ወደ በረዶነት የመቀየር አቅም ሳይኖረው አይቀርም ብለውኛል የቀመሱት በተመሳሳይ መንገድ መለሰ መንገሻም 84/06 ይገኛል ቀደም ሲል በዚሁ ክፍል ታስረውበት የነበሩ ሰዎች እንደነገሩኝ በነሱም (በአሳሪዎቹም) እንደሚታመነው አንድ ሰው በነዚህ ክፍልሎች ውስጥ ከ27 ቀን በላይ በዚህ ክፍል ውስጥ ከቆየ የአይን ብርሀኑ ሙሉ ጤናማ እንደማይሆን ይታመናል በነዚህ ክፍልሎች ምንም አይነት የተፈጥሮ ብርሃን አያገኙም እነዚህ ክፍልሎች ከ1984 ዓም ጀምሮ በርካታ የመአሕድና የመኢአድ አመራሮችና አባላት ታስረውበት የነበረ ነው እነዛ ክፍልሎች ታስረው የወጡ ታሳሪዎች እንዳጫወቱን ከክፍሉ ቅዝቃዜ የተነሳ ለከፋ የጤና ችግር ተዳርገው እንዳሉ በዚሁ ምክንያት ያጡትን ጤና ለመመለስ እውጭ ሀገር ድረስ ሄደው ቢታከሙም መዳን እንዳልቻሉ ገልፀውልኛል
እነ ዘመነ ምህረት ላለፉት 2 ወር ከ15 ቀን በነዚሁ ክፍሎች ውስጥ ሌሊትና ቀን እጅና እግራቸው በካቴና ታስሮ በመከራና በስቃይ እንዳሳለፉ ይገመታል ።
ሰው ሆኖ በሰው ልጅ ላይ ሊደርስ ይችላል ተብሎ የማይታመንና አለም በሙሉ በአስከፊነቱ ያስወገደውን ኢሰብአዊ ድርጊት በነዚህ ወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመባቸው ለመሆኑ የጉዳዩ ባለቤቶች ገልፀዋል ።
ለሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች
ማዕከላውይ በሚባለውና በሌሎች ማሰቃያ ቦታዎች እጅግ በጣም ብዙ ቁጥር ያላቸው የመኢአድ አመራርና አባላት ያሉበት ሁኔታ በመኖርና ባለመኖር መካከል ያሉ ስለሆነ የነዚህን ወገኖቻችን ጉዳይ በመከታተል ባላችሁ ሀላፊነት መሠረት በናንተ ላይ ወድቋል የሚቻለውን ሁሉ ጥረት ታደርጉ ዘንድ ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችሁ ጥሪያችንን እያስተላለፍን ሀላፊነታችሁን ትወጡ ዘንድ እናሳስባለን ።
ማዕከላውይ በሚባለውና በሌሎች ማሰቃያ ቦታዎች እጅግ በጣም ብዙ ቁጥር ያላቸው የመኢአድ አመራርና አባላት ያሉበት ሁኔታ በመኖርና ባለመኖር መካከል ያሉ ስለሆነ የነዚህን ወገኖቻችን ጉዳይ በመከታተል ባላችሁ ሀላፊነት መሠረት በናንተ ላይ ወድቋል የሚቻለውን ሁሉ ጥረት ታደርጉ ዘንድ ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችሁ ጥሪያችንን እያስተላለፍን ሀላፊነታችሁን ትወጡ ዘንድ እናሳስባለን ።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ