
በተመሳሳይ የደ/ጎ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ሰብሳቢና የፎገራ ወረዳ የተወካዮች ም/ቤት እጩ ተወዳዳሪ አቶ አለማየሁ አደመ ላይ ከፍተኛ የሆነ ድብደባ እንደተፈፀመበት ተገልጾአል፡፡ ደህንነቶች አቶ አለማየሁ በሚኖርበት ደራ ወረዳ አርብ ገበያ ከተማ ሚያዝያ 20/2007 ዓ.ም ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ደብደባ ፈጽመውበታል፡፡ አቶ አለማየሁ ድብደባው በተፈፀመበት አርብ ገበያ ጤና ጣቢያ እየተረዳ የነበር ቢሆንም ጉዳቱ ከፍተኛ በመሆኑ ወደ ባህርዳር ሪፈራል ሆስፒታል መዛወሩ ታውቋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ የምዕራብ ጎጃም ዞን አስተባባሪ የሆነው አቶ አዲሱ ጌታነህ መንግስት አይ ኤስ በኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን ግድያ ለመቃወም ባህርዳር ከተማ ላይ በጠራው ሰልፍ ተገኝቶ ከተመለሰ በኋላ ምሽት ላይ ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመበት መዘገባችን ይታወሳል፡፡
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ