ረቡዕ 3 ፌብሩዋሪ 2016

በኦሮሚያ ክልል አዲስ የጸጥታና የደህንነት/ስለላ መዋቅር ሊዘረጋ ነው::በጋምቤላ የሕወሓት ባለስልጣናትና ቤተሰቦቻቸው ንብረት በታጠቁ የደቡብ ሱዳን ቅጥረኞች እና በአግአዚ ወታደሮች መጠበቅ ተጀምሯል::


ልዩነት ውበት ነው…ግን አልፈጠረብንም::መቻቻል ያልተጋባቸው ያልበሰሉ ጭፍኖች በ2 ጽንፍ ማሕበራዊ ድህረገጾችን ወረዋል:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Oromoprotests‬ ‪#‎Gambella‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬
በኦሮሚያ ክልል አዲስ የጸጥታና የደህንነት/ስለላ መዋቅር ሊዘረጋ ነው::በጋምቤላ የሕወሓት ባለስልጣናትና ቤተሰቦቻቸው ንብረት በታጠቁ የደቡብ ሱዳን ቅጥረኞች እና በአግአዚ ወታደሮች መጠበቅ ተጀምሯል::
===========================================================
Minilik Salsawi – በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አከባቢዎች አሁንም ውጥረት የነገሰ መሆኑን የደህንነት ቢሮ የሚደርሱ ሪፖርቶች እንደሚጠቁሙ ለጉዳዩ ቅርበት ያላችው ወገኖች መረጃ ሰጥተዋል::በኦሮሚያ ክልል በጥሩ ክፍያ በፎቶግራፍ እና በቭድዮ ቀረጻ ላይ ተሰማርተው የነበሩ የኦሕደእድ ካድሬዎች እየተለቀሙ መሆኑ ታውቋል::የወያኔው ጁንታ አገዛዝ አስፈላጊውን ግድያና የጅምላ እስር ከፈጸመ በኋላ ለይስሙላ የመለሳለስ ባሕሪያ በማሳየት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን አቆምኩት እንዲሁም የሕዝቡ ጥያቄ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ነው በሚል የሰራውን እኩይ ተግባር ለመሸፋፈን ቢዳክርም የሕዝቡ ተቃውሞ እያገረሸ ብሎም እንዳተኮሰ ይገኛል::መሰሪ እና ውሸታም የሆነው የወያኔ አስተዳደር ላይ ላዩን በመለሳለስ ውስጥ ውስጡን አዲስ የጸጥታ እና የደህንነት/ ስለላ መዋቅር ሊዘረጋ ሲሆን ሕዝቡ ግን አሁንም ለአንድ ለአምስት የአፈና መዋቅር ያልተበገረ ለአዲሱም የስለላ መዋቅር እንደሚያስቸውግር ስጋት መኖሩት የወያነ የደህንነት መረጃዎች ጠቁመዋል:: የመዋቅሩ አዘረጋግ በተመለከተ አስፈላጊው ስራ እየተሰራ ሲሆን ይህ መረጃ የደረሳችሁ ማንኛውም የሕዝብ አካላት የወያኔን መዋቅር በማፈራረስ ዳግም ለህዝባዊ እምቢተኝነት እንድትዘጋጁ ምንጮቹ አሳስበዋል::
በጋምቤላ ክልል አኙዋክ ብሄሮች ላይ ከቀያቸው አፈናቅሎ በሕወሓቶች ለመተካት በደቡብ ሱዳን ቅጥረኛ ኑዌሮች የተጀመረው ግድያ እና ማሳደድ የቀጠለ ሲሆን የሕወሓት ባለስልጣናትና ቤተሰቦቻቸው ንብረት በታጠቁ የደቡብ ሱዳን ቅጥረኞች እና በአግአዚ ወታደሮች መጠበቅ ተጀምሯል::በአኙዋክ ሕዝብ ላይ እጅግ አደገኛ የሚባልለት ይህ የዘር ማጽዳት ከዚህ ቀደም የተካሄደ ሲሆን ለም መሬቶችን ለመቀራመት ባሰፈሰፉ የሕወሓት ስዎች እና ጋሻጃግሬዎቻቸው የደቡብ ሱዳን ኑዌር ስደተኞችን በማስታጠቅ አከባቢው በደም እንዲጨቀይ አድርገዋል::በአለም አቀፉ እና በሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጫና ግጭቱ ራሱ በከፈተው መንገድ ራሱ ያቀዘቀዘው ሕወሓት አሁንም በበቂ ሁኔታ ለመስፋፋት እና አዳዲስ ለም መሬቶችን ለመያዝ እንዳቀደ በስፋት እየተነገረ ይገኛል::በሃገሪቱ ከባድ እና አደገኛ ውጥረት በመጫር ዘእጎች በሞት እንዲያልኡ እያደረገ የሚገኘውን የሕወሓት አገዛዝ ከስሩ ነቅሎ ለመጣል ትግላችንን አጠናክረን መቀጠል እንዳለብን አሳስባለሁ::
Minilik Salsawi's photo.

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ