እሑድ 27 ማርች 2016

የሄነከን ቢራ ዘረፋ ምስጢር በኢትዮጵያ ሲጋለጥ – ክንፉ አሰፋ


የሄነከን ቢራ ዘረፋ ምስጢር በኢትዮጵያ ሲጋለጥ – ክንፉ አሰፋ



የሆላንድ ዜምብላ[1] ጋዜጠኞች የኦሮሞ ጸሃፊው የሆነውን ያሶ ካባባን ይዘው ወደ ጊንጪ ያመራሉ። እግረመንገድ ላይ የሚያገኟቸው ገበሬዎችም ሲጠይቋቸው በምስሉ ይታያል። እነዚያ በቀያቸው ማረፍያ እንኳን የሌላቸው ገበሬዎች የጋዜጠኞቹን መኪና ከብበው እንዲህ ሲሉ ይደመጣሉ። “መሬታችንን ቀምተው ለነጮች ሰጡብን። እኛንም በታተኑን…”
በገዛ ቀያቸው ስደተኛ የሆኑ እነዚህ ወገኖቻቸን ሰቆቃቸው የከፋ ነበር። በመጨረሻ ተሰባሰቡና መከሩ። ሰባት ሺህ የሚሆኑ የጊንጪ ተወላጆች ሆ! ብለው ወጥተው ይህንን የሁለት ሚሊዮን ዩሮ (ሃምሳ ሚልዮን ብር) ንብረት በሰኮንዶች ውስጥ አወደሙት። ምስላቸውን ለካሜራ ሳይደብቁ፣ ስሜታቸውን እና የወደፊት እቅዳቸውን ይናገራሉ። “ከአንባገነን መንግስት ጋር አብሮ ከመስራት ይልቅ የአካባቢው ነዋሪዎች ሊጠቀሙ በሚችሉበት መንገድ መስራት እንደሚችሉም።” ለፈረንጆቹ ይመክራሉ። “ይህ ካልሆነ ግን ማውደሙን እንቀጥልበታለን!” ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ይህ ማስጠንቀቅያ ግዙፉ አለም አቀፍ ኩባንያ የሆነው ሄነከን ቢራንም ይመለከታል።

ባለፈው ሳምንት በሆላንድ ብሄራዊ ቴለቭዥን የተላለፈው ዜምብላ ፕሮግራም የሚሊዮኖችን ቀልብ ስቧል። ለዚህም ምክንያቶች አሉት። አንደኛው ምክንያት፤ የዜምብላ ፕሮግራም በምርመራ ጋዜጠኞች የሚሰራ በመሆኑ እጅግ የሚፈራ እና በሃገሪቱ ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ማሳደሩ ሲሆን፣ በሁለተኛ ደረጃ በኢትዮጵያ እየወደመ ያለው ይህ ንብረት የተቋቋመው በሆላንድ መንግስት ድጎማ ሲሆን፣ ይህ ደግሞ የእያንዳንዱ ሆላንዳዊ ግብር ከፋይ ገንዘብ በመሆኑ ነው።

የሆላንድ የልማትና ትብብር ሚንስተር ለድሃ ሀገሮች እርዳታ ከመለገስ ይልቅ ወደ ንግድ ድጎማ ፊቱን ባዞረ ግዜ፣ 130 አትራፊ የንግድ ድርጅቶች ድጎማ እየተቀበሉ ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። ከነዚህ ውስጥ ትልቁን የድጎማ ድርሻ የወሰደው ሄነከን ቢራ ነው። ሄነከን ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ የሆላንድ መንግስት አንድ ቢሊየን ዩሮ ድጎማ አድርጓል። እንደ ሆላንድ መንግስት እሳቤ፣ ይህንን የልማት ትብብር ገንዘብ በእርዳታ መልክ ከመስጠት ይልቅ ይህንን አትራፊ ተቋም አበራትቶ ስራ በመፍጠር እና በንግድና በስራ ታክስ ሃገሪቱ ተጠቃሚ እንድትሆን ማድረግ ነበር። የሆነው ግን በተቃራኒ ነው።

የዜምብላ ቴሌቭዥን ዘገባ ያጋለጠው ጉዳይ በእጅጉ ያስደምማል። እንዲህ ነው የሆነው። እ.ኤ.አ. በ 2011 ሄነከን ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ የቢራ ስራ አዋጭ መሆኑን ስለተገነዘበ ስመ ጥሮቹን በደሌ እና ሃረር ቢራን ገዛቸው። ስራውንም በእጅጉ አስፋፋ። በአኢትዮጵያ የቢራ ተጠቃሚዎች ቁጥር በእጥፍ እንዳደገም ዘገባው አስምሮበታል። ትርፉም እንደዚያው አደገ።

በደሌ ቢራ ከመሸጡ በፊት አንድ ነጥብ አምስት ሚሊየን ዩሮ ግብር ይከፍል ነበር። ሄነከን ከገዛው በኋላ ግን የከፈለው ዘጠኝ መቶ ሺህ ዩሮ ብቻ ነው። አንድ ሚሊየን ዩሮ ግብር ይከፍል የነበረው ሃረር ቢራም አሁን ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ዩሮ ብቻ ነው ያስገባው። ትርፉ ከእጥፍ በላይ እያደገ፣ ግብሩ ከእጥፍ በላይ የመቀነሱ ምስጢር ምን ይሆን?

የግብር ማጭበርበር ጥቆማ የደረሳቸው እነዚህ ጋዜጠኞች ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ንግድ ሚንስትር ሄዱ። ምኒስትሩ በዚህ የማጣራት ጉዳይ ላይ ሊተባባራቸው ፈቃደኛ አልነበረም። ከዚያም ወደ ጉምሩክ እና ቀረጥ ቢሮ አመሩ። እዚያም ምንም መረጃ እንሰጥም ይሏቸዋል። ምስጢሩን ለማውጣት የጓጉት እነዚህ ጋዜጠኖች ተስፋ አልቆረጡም። በመጨረሻ ወደ ንግድ ምክር ቤት አመሩ። የዚያ ባለስልጣን የሰጧቸው ምላሽ የሚያስቅ ነው። “የንግድና ትርፍ ዘገባ አይደርሰንም።” አሉ። ታዲያ ንግድ ምክር ቤት ይህንን ካልመዘገበ ምን ይሆን የሚሰራው?

የንግድና የስራ ግብር መቀነሱ ብቻ አይደለም። ቀድሞ በሃረር እና በበደሌ ቢራ ቋሚ ሰራተኛ የነበሩ 699 (44%) ሰራተኞችም ከሄነከን ቢራ ተቀንሰዋል። የሆላንድ መንግስት ስራ ፍጠሩ ብሎ ድጎማ ሲያደርግ፣ ይልቁንም ነባሩን ሰራተኛ ከስራው አፈናቀሉት።


በኢትዮጵያ የሄነከን ተወካይ ሆላንዳዊ ነው። የዜምብላ ጋዜጠኖች የዚህን እንቆቅልሽ ለመፍታት እሱን ማፋጠጥ ይችላሉ። ስለዚህም ወደሱ አመሩ። የገቢና ወጪ ዘገባውን እንዲሰጣቸው ጠየቁት። እንቢ እንዳይል ቸገረው። ምክንያቱም በዚያ ዘገባ የሆላንድ መንግስት የድጎማ ገንዘብ ሰላለበት። እሺ ብሎ ይፋ እንዳያደርገው ደግሞ ምስጢሩ ለህዝብ ሊወጣ ነው። እሱም አለ። “የፋይናንስ ሪፖርቱን እሰጣችኋለሁ። እናንተ ግን ለህዝብ ይፋ እንደማታደርጉት ቃል ግቡልኝ።”

ዘገባውን በእጃቸው ያስገቡት እነዚህ ጋዜጠኖች፣ ዶክመንቱን አለም አቀፉ የገንዘብ ተቁዋም አማካሪዎች ጋ ይዘውት ሄዱ። የ አይ. ኤም. ኤፍ. ባለሙያው ወረቀቱን እንዳየ ምስጢሩን ለማወቅ ሰከንዶች አልፈጁበትም። የኢትዮጵያ ህዝብ በታክስ ተዘርፏል። ሰራተኛውም ወገን ከስራው እንዲፈናቀል ተደርጓል።

የመንግስት ባለስልጣን ሃገር ሲዘረፍ እና ወገን ከስራ ሲፈናቀል፣ ጉዳዩን ማፈን መርጠዋል። ምክንያት ቢኖራቸው እንጂ ይህን መረጃ መስጠት ሀገርን የሚጠቅም ነበር። በእርግጥ ይህ የግብር ማጭበርበር ተግባር እነሱ ሳያውቁት ሊሆን አይችልም። “የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ!” ነው ነገሩ። እንዲህ እየተዘረፈ ኢኮኖሚው እንዴት ነው በ 11 በመቶ የሚያድገው?


እንግዲህ ይህ በኢትዮጵያ ከዘመቱት 130 የሆላድ የንግድ ድርጅቶች አንዱ ታሪክ ነው። ገቢውና ወጭው በግልጽ የሚታይ፣ ግዙፍ እና አለም አቀፍ ድርጅት። ሄነከን ከገዥው ፓርቲ ባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ይህንን ያህል ከዘረፈ የሌሎቹ – የማይታወቁት ምን ያህ ይሆን?


የቀድሞው የሆላንድ ልማትና ትብብር ሚንስቴር የነበሩት ጃን ፕሮንክ፣ በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ከልማት እና እደገት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት ለሌላቸው የንግድ ድርጅቶች የገንዘብ ድጋፍ ማድረግን ክፉኛ ይወቅሳሉ። በተለይ መንግስታቸው በልማትና ትብብር ስም፣ በብሄራው ጥቅም ስም የስብአዊ መብት ረገጣን ችላ ማለቱን ያወግዛሉ።


በልማት ስም በሚሊዮኖች እየፈሰሰ ያለው የሆላንድ ግብር ከፋዮች ገንዘብ በኢትዮጵያ ስራ አልፈጠረም። እንደውም ሰራተኞችን አፈናቀለ። ሀገሪቱን በበለጠ የስራና የንግድ ግብር ተጠቃሚ ያደርጋል ይባል እንጂ ግብሩ በ 70 እጅ ያነሰ ሆኗል። ከሁሉም በላይ ደግሞ የገበሬው መሬት እየተነጠቀ ለነዚህ ዘራፊዎች መሰጠቱ የህዝብ ቁጣን አስነስቷል።


በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት እየተካሄደ ያለው ህዝባዊ አመጽ የገዥው ፓርቲ ችግር ብቻ ሳይሆን የሆላንድም ችግር መሆኑን በመግለጽ ዜምብላ ዘገባውን ይደመድማል።

ረቡዕ 16 ማርች 2016

Ethiopians hold demonstration in DC denouncing human rights violations in their country, demand US to take firm stand



Screenshot_2016-03-16-00-12-59 (2) (2)

Ethiopians living in the metropolitan Washington, DC area held a demonstration at the US State Department on Tuesday denouncing the human rights violations perpetrated by the tyrannical regime in their country against the people of Surma in South Ethiopia as well as the human rights abuses at various locations in the country.
The demonstrators also demanded the US government to show unwavering stance against the human rights abuses perpetrated by its ally in Ethiopia.
An international uproar ensued last week after a picture of Surma men in a chain gang, loaded on a police pickup, surfaced on the social media. They were apparently held by the regime’s forces for protesting the seizure of their land by the government for sugar plantations.
The Ethiopians demanded the regime in their country to immediately desist the wide range of human rights violations in Oromia, Wolkait in Amahra and Gambella regions and other corners of the country. The demonstrators hold the oppressive regime in Ethiopia responsible for the death of hundreds of people in the Oromia region of Ethiopia in the last four months protests.
The organizers of the demonstration have submitted to the US State Department a paper detailing the various human rights violations in Ethiopia.
Tuesday’s demonstration was organized by the Washington DC Joint Task Force, civic, political and religious organizations.

ሰኞ 14 ማርች 2016

በኮንሶ ግጭቱ አገረሸ ፤ ሰዎች ተገደሉ:: የካራት ከተማና አጎራባች ቀበሌዎች ትምህርት ቤቶች ተዘጉ::


– በኮንሶ ህዝብ የተነሳውን የአከላለል ጥያቄ ተከትሎ በሕወሓት አገዛዝ ታጣቂ ኃይሎችና በህዝቡ መካከል የተነሳው ግጭት ላለፉት ሁለት ቀናት ጋብ ብሎ የነበረ ቢሆንም እንደገና አገርሽቶ ሦስት ሰዎች ሲሞቱ ሁለት ደግሞ ቆስለዋል፡፡ የካራት ከተማ አጎራባች ከሆኑት ቀበሌዎች አንዱ በሆነው ደበና ቀበሌ ወጣት ፋንታዬ ጊዮርጊስ፣ ወጣት ሞሎ ቱሌ እና አንድ ስሙ ያልደረሰን 10ኛ ክፍል ያጠናቀቀ ሥራ አጥ ወጣት በሕወሓት አገዛዝ የጸጥታ ኃይሎች የተገደሉ ሲሆን በተጨማሪም ሁለት ወጣቶች ቆስለዋል ፡፡ በዚህ ግጭት ሳቢያ የካራት ከተማና አጎራባች ቀበሌዎች እስካሁን ትምህርት ቤቶች እንደተዘጉ ሲሆን ከተማዋና አካባቢው በመኪና ላይ በተጠመዱና የነፍስ ወከፍ መትረየስ ታጣቂዎች ተወሮ፣ ኮንሶ ልዩ ወረዳ ከዳር እስከ ዳር በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ናቸው፡፡
Minilik Salsawi's photo.
የኮንሶ ህዝብ የጀመረውን የአከላለል ጥያቄ ጋር በተያያዘ በህዝቡ ላይ በደቡብ ልዩ ኃይልና መከላከያ ሰራዊት እየደረሰ ያለው የአፈና ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በዚሁ መሰረት በከተማው የሰፈረው ታጣቂ ከከተማዋ አጎራባች ቀበሌዎች እየዘመተ በህዝቡ የተዘጉ መንገዶችን ለማስከፈት በሚል በዜጎች ላይ በሚወስደው የኃይል እርምጃ በ- ደቤና ቀበሌ ገ/ማ አቶ ‹‹ሷይታ ጋራ ›› ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ወጣት ‹‹ ተስፋዬ ማሙሽ›› ከ -ከርታሌ ቀበሌ እግሩ ተሰብሮ በባህል ህክምና እየተደረገለት በካራት ከተማ የሚገኝ ሲሆን አንድ የ65 ዓመት አዛውንትም ተሰብረው ባሻ ጤና ጣቢያ ይገኛሉ፡፡ ከባለፈው ዓርብ/25-06-08/ ጀምሮ 23 ሰዎች/ሃያ ሁለት ወንዶችና አንዲት ሴት/ ከፍተኛ ድብደባ ተፈጽሞባቸው በከተማዋ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከል ውስጥ ታስረው እንደሚገኙ ተገልጧል፡፡ በከተማዋ የሚገኙት የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች በሙሉ የተዘጉ ሲሆን የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛው ወደ እስር ቤት ተቀይሯል፡፡
ወደከተማው የሚያስገቡ መንገዶች እስካሁን የተዘጉ ሲሆን በተለይ የ -ደራ እና ጃርሶ ቀበሌ ነዋሪዎች መትረየስ በታጠቁ የልዩ ኃይል አባላት ተወረዋል፡፡ በጃርሶ ቀበሌ ሰገን ወንዝ ዳር የሰፈረው ኃይል የነዋሪዎችን ፍዬሎች እየዘረፈ አርዶ እንደሚበላ፣ የፓፓያ፣ማንጎ አቮካዶ እና የፍራፍሬ ዛፎችን በበቀል ስሜት እያበላሸ/እያወደመ እንደሚገኝም ህዝቡ በምሬት እየገለጸ ነው፡፡
ታጣቂ ኅይሉ በዚህ የኃይል እርምጃ የካራትን ከተማ አቋርጦ የሚያልፈውን የአርባ ምንጭ -ጂንካ መንገድ ማስከፈት ቢችልም ከተማዋን ከማሳለፍ ውጪ የሚሰጠው ዋስትና ያለመኖሩ አሽከሪካሪዎችን ስጋት ላይ በመጣሉ ከመንግስት መኪናዎች ውጪ የትራንስፓርት እንቅስቃሴ አይታይም፡፡ የመንግስት መኪና ተጠቃሚዎችም ቢሆኑ ከልዩ ኃይል ጋር ተነጋግረው መግባባት ባለመቻላቸው በትናንትናው ዕለት የደቡብ ኦሞ/ጂንካ ባለሥልጣናትን ይዞ ይጓዝ የነበረ መኪና ለ2 ሰዓታት ካራት ላይ በታጣቂ ኃይሎች ታግቶ ቆይቶ እንደተለቀቀ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
Minilik Salsawi's photo.
በአጠቃላይ ከተማዋና አካባቢው በመኪና ላይ በተጠመዱና የነፍስ ወከፍ መትረየስ ታጣቂዎች ተወሮ፣ ኮንሶ ልዩ ወረዳ ከዳር እስከ ዳር በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ይገኛል ፡፡ የአገር ሽማግሌዎችና ወጣቶች ፣ሴቶችና ህጻናት ሳይቀሩ ቱንም ዋጋ እንከፍላለን እንጂ ጥያቄኣችን ሳይመለስ ወደቤት አንገባም /አንመለስም በማለት ያላቸውን ቁርጠኝነት እየገለጹ መሆኑን እነዚሁ ታማኝ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡ እኛም የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት ሆይ ‹‹አፈና እና የኃይል እርምጃ ›› የህዝብን ብሶት ሲባብስ እንጂ ለህዝብ ጥያቄ መልስ አይሆንምና ከህዝቡ ላይ እጅህን አንሳ፣ ለሰላማዊ ጥያቄው ተገቢውን ምላሽ ስጠው፣ ህገ መንግስታዊ መብቱን አክብርለት እንላለን ፡፡

እሑድ 13 ማርች 2016

Egregious Human Rights Violations In the OMO Valley of Ethiopia


http://i2.wp.com/ecadforum.com/wp-content/uploads/2016/03/Konso-Poster-Large.jpg

If you think the image you see below is from the archives of the slave trade in the 1800s you are wrong. This is 2016 ‪#‎Ethiopia‬ where the government chains and forcefully removes indigenous peoples from their ancestral homeland for sugar cane plantation.
The minority government thinks it is. In the name of development, dehumanization and the degradation of human dignity are the order of the day throughout Ethiopia. These gross violations of human rights are taking place with the blessing of the West especially, the US and UK - the unconditional financial, political, diplomatic, and military aid for the TPLF for the past 25 years has enabled the regime to terrorize Ethiopian citizens with impunity.

ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

በአገራችን እየተነሱ ያሉ ግጭቶች መኢአድን በእጅጉ አሳስቦታል!

ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
I. የኢህአዴግ መንግሥት በ1983 ዓ.ም ሥልጣን ከመያዙ በፊት የኢትዮጵያ ሕዝብ በተወለደበት ቀዬ፣ በዘሩና በቋንቋው ሳይሆን በኢትዮጵያዊ ማንነቱ በመኩራት በአንድነትና በመተባበር የአገሩን ዳር ድንበር ሲያስከብርና አገሩን ሲገነባ ኖሯል፡፡ በ1983 ዓ.ም የተቋቋመው የሽግግር መንግሥት በተደነገገው በሕገመንግሥት አንቀጽ 39 ላይ ባወጣው የራስን እድል በራስ መወሰን እንከመገንጠል መብት በመገፉፉት የኢትዮጵያ ሕዝብ ከኢትዮጵያዊነቱ ይልቅ ለተወለደባት ቀበሌና ለወጣበት ዘር፣ ከአንድነት ይልቅ መለያየት፣ አብሮ በመሥራትና አብሮ በማደግ ከመበልጸግ ይልቅ ተበታትኖ የጐሪጥ ስለሚተያይ በአገራችን ዕድገት ላይ መሰናከል በመፈጠሩ በችግር ላይ ይገኛል፡፡
ይህ የመለያየትና የመከፋፈል በሽታ ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥ እያደገ መጥቶ ዛሬ ልንወጣው በማንችልበት የገደል አፋፍ ላይ ጥሎናል፡፡
በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል ሕዝብ የቀረበው ጥያቄ በወጉና በባህሉ መሠረት ሊመለስ ባለመቻሉ ጥያቄው ወደ ሕዝባዊ አመፅ ተቀይሮ በሰውና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ ይገኛል፡፡ ይህ ጥያቄውን በሰላማዊ መንገድ መመለስ አለመቻልና በድብደባ፣ በእስራትና በግድያ ለማብረድ መሞከሩ አመፁን ከማባባሱና ጉዳቱን ከማስፋት ውጭ የሚፈይደው አንዳችም ነገር የለም፡፡
ከዚህ ቀደም ከአለን ተሞክሮ እንደምንረዳው እንደነዚህ ያሉ ቅራኔዎች በሚከሰቱበት ወቅት እየተናቁና ትኩረት እያጡ በመቆየታቸው በአገራችንና በሕዝባችን ላይ ከፍተኛ ቀውስና ውድቀት ሲያስከትሉ ቆይተዋል፡፡
ከኢህአዴግ መንግሥት ባለሰልጣናት የሚነገረው የቅራኔው መነሻ የመልካም አስተዳደር እጦት ነው የሚል ነው፡፡ ይህ አባባል መልካም ሰው ከአገር አጥፍቶ መልካም አስተዳደርን አመጣለሁ ማለቱ ስህተት ቢሆንም ቅሉ በአገሪቱ ውስጥ እየተነሱ ያሉ ቅራኔዎች ከመልካም አስተዳደር እጦት የዘለሉና ብዙ ድርብርብ ጥያቄዎችን ያዘሉ ለመሆኑ መንግሥት ሊጠራጠር አይገባውም፡፡ ምክንያቱም በሀገራችን ያለው የኑሮ ውድነት፣ ሙስና፣ ፍትሀዊ ያልሆነ የኢኮኖሚ ክፍፍልና የመለካም አስተዳደር እጦት በአገሪቱ ተንሰራፍተዋልና ነው፡፡
ስለዚህ፡-
1. በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ሰላማዊ በሆነ ውይይትና መግባባት እንዲፈታ አጥብቀን እንጠይቃለን፤
2. እስራት፣ ድብደባውና ግድያው ቅራኔውን ከማባባሱ ውጭ የሚያመጣው ፋይዳ ስለማይኖር በአስቸኳይ ቆሞ ለጉዳዩ ሰላማዊ መፍትሔ እንዲፈለግለት
II. በአንዳንድ አላዋቂ እና ፅንፈኛ የፖለቲካ ሰዎች የተደረጉ ውሳኔዎች በፍቅርና በአንድነት ለብዙ ሺ ዓመታት አብሮ የኖረውን ወንድማማች ሕዝብ ወደማይመለስ ቅራኔ እየከተቱት ይገኛሉ፡፡ ይኸም በወልቃይት ጠገዴ፣ በፀለምትና በሴቲት ሁመራ አካባቢ የሚገኘው መሬት በአማራ ክልል ወይስ በትግራይ ስር ነው? በሚል የተነሳው ጥያቄ ሁለቱን ወንድማማች ሕዝቦች ወደከፋ ግጭት ውስጥ ለማስገባት ከጫፍ ላይ ደርሶ ይገኛል፡፡ እንደነዚህ ያሉ ግጭቶች በአሁኗ ኢትዮጵያ አዲስ አይደሉም፡፡ ለምሳሌ፡- በቦረናና በጉጂ፣ በሀሪና በኮንሶ፣ በደቡብና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል እንዲሁም በኦሮሚያ በደቡብ ክልሎች መካከል በመሬት ይገባኛል ስበብ ተመሳሳይ ቅራኔዎች ተነስተው ህይወት ጠፍቷል፣ ንብረትም ወድሟል፡፡ ይሁን እንጂ ሁኔታው በሁለቱ ክልሎች ባለስልጣናት ሰፊ ውይይት እንዲፈታ ተደርጓል፡፡ በወልቃይትና በሁመራ ምክንያት የተነሳው ቅራኔ ግን በሰላማዊ መንገድ ከመፍታት ይልቅ በቅራኔ ብቻ በመጦዝ ላይ በመገኘቱ መኢአድን እጅግ አድርጐ አሳስቦታል፡፡ ይሀ ሁኔታ ማንንም የማይጠቅም ስለሆነ ጊዜ ሳይሰጠው በውይይትና በሰላማዊ መንገድ መፈታት አለበት የሚል እምነት አለን፡፡
ከዚህ ላይ የህውሓትና የትግራይ ክልል አመራሮች በጉዳዩ ላይ የተለያዩ ፍንጮችን ሲሰጡ የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) በኩል አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ መልስ ሲሰጥ ተሰምቶ አያውቁም፡፡ ይኸም እወክለዋለሁና እመራዋለሁ ለሚለው ሕዝብ ትክክለኛውን አቅጣጫ ሊያመላክተው አለመቻሉ ከትዝብት ላይ የሚጥለው ሆኖ አግኝተነዋል፡፡
ስለዚህ መኢአድ ለሁለቱም ክልል አመራሮችና የፖለቲካ ድርጅቶች የሚያሳስበው፤
1ኛ. በሁለቱ ወንድማማች መካከል የከፋ ቅራኔ ሳይፈጠር የሚመለከታችሁ አካላት ሕግንና ከዚህ ቀደም የነበረን የአመጣጥ እና የአሰፋፈር ታሪክን መሠረት በማድረግ በአስቸኳይ መፍትሄ እንዲያፈላልጉለት፡፡
2ኛ. የፌዴራሉ መንግሥትም ቅራኔውና ብጥብጡ እንስከሚነሳ ዝም ብሎ ከመመልከት ይልቅ በእነዚህ ሁለት ወንድማማች ህዝቦች አመጣጥና አሰፋፈር ታሪክ ላይ በመመርኮዝ የመፈትሄ ሀሳብ መሰጠት ይቻል ዘንድ እንዲያመቻች አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
3ኛ. ከዚህ በተጨማሪ በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሁኔታው በህግ በሞራልና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ጥረት እንዲያደርጉ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
III. የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ለኢትዮጵያ የተቀዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር ፈር ቀዳጅ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ መኢአድ ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ ከውስጥና ከውጭ በሚነሱ ችግሮች የተነሳ መጠነ ሰፊ የሆነ ፈተና ሲጋረጥበት መቆየቱ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ መሪውን ክቡር ኘሮፌሰር አሥራት ወልደየስን ጨምሮ ብዙ አመራሮቹና አባላቱ በውስጥ አርበኞች ጠቋሚነትና መስካሪነት ታስረዋል፣ አካላቸው ጐድሏል፣ ተገድለዋልም፡፡ መኢአድን ለማፍረስ ብዙ ቡድኖች በተለያዩ አካላትና በተለያዩ ጊዜያት ተቋቁመዋል፡፡ ነገር ግን መኢአድን ለማዳከም የቻሉ ቢመስልም ሊያጠፉት ግን አልቻሉም፡፡ አሁንም በቅርብ ጊዜ በቀድሞው የመኢአድ ኘሬዝዳንት የግል ሹፌርና በሌሎች ምንደኛ ግለሰቦች የሚመራው ቡድን በተለያዩ ጥቅማጥቅሞች በመደለል ፓርቲውን ለማዳከም ብዙ ጥረት አድርጓል፡፡ እነዚህ ግለሰቦች የአራዳ ምድብ ችሎትን በሀሰት ቃለ-መሐላ በማሳሳት የፓርቲውን ማህተም አሳግደው ኘሬዝዳንቱን አግደናል በሚል ለአንድ ሳምንት ብዙ አካላትን አሳስተው ሲያወናብዱ ቆይተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ፍ/ቤቱ በአደረገው ማጣራት ሕገወጦች ናቸሁ በማለት ፋይሉን ዘግቶ አባሯቸዋል፡፡ ከዚህ በላይ በጣም ያሳዘነንና ያስቆጨን ኘሮፌሰር አሥራት በተቀመጡበት ወነበር ላይ የቀድሞ የመኢአድ ኘሬዝዳንት የግል ሹፌር የሆኑት በኘሬዝዳንትነት ተሰየምኩ በማለት ኃላፊነቱን ለመውረስ መምጣታቸው ነው፡፡
ከዚህ ላይ በጣም ያሳዘነንና ተስፋችንን ያሟጠጠው አንዳንድ በሕዝብ ዘንድ ተነባቢነት ያላቸው ጋዜጦችና የሬዲዮ ባቢያዎች እነዚህ ህገወጥ ግለሰቦች የሰጧቸውን ወረቀት በመያዝ ሁኔታውን ሳያጣሩ ሚዛናዊነቱን ያጣ ዘገባ ማድረጋቸው ነው፡፡ እንደዚህ ያለው ድርጊትም በአገራችን ዲሞክራሲን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ስለሚኖረው ጥንቃቄ ሊደረግበት ይገባል እንላለን፡፡
በአጠቃላይ እነዚህ ግለሰቦች በአሰራጩት የሀሰት ኘሮፓጋንዳ የተነሳ፤
1. በአገር ውሰጥ የምትገኙ የመኢአድ አባላት እና ደጋፊዎች እንዚህ ህጋዊ ያልሆኑ ግለሰቦች ባሰራጩት ውዥንብር ሳትደናገጡ በፅናትና በአንድነት ከፓርቲያችሁ ጋር እንድትቆሙ፤
2. በውጭ የምትገኙ የመኢአድ አባላትና ደጋፊዎች እንደነዚህ ያሉ ግለሰቦች እየሰሩት ያለው የውሸት ውዥንብር በመፍጠር ፓርቲውን ለማዳከም ስለሆነ በውዥንብሩ ሳታዝኑና ሳትጨነቁ የተለመደ አብሮነታችሁ ከፓርቲያችን እንዳይለይ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
3. እንደነዚህ ያሉ ጥቅመኞች ከተለያዩ አካላት ገንዘብ በመቀበል ፓርቲዎችን ለማፍረስ ጥረት ማድረጋቸው የተለመደ ሆኗል፡፡ ስለዚህ የየፓርቲዎቹ አባላትና ደጋፊ እንደነዚህ ያሉ ግለሰቦችን በአንድነት ሊያወግዟቸውና ሀይ ሊላቸው ይገባል፡፡
አንዲት ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
አዲስ አበባ
የካቲት 28 ቀን 2008 ዓ.ም

ረቡዕ 9 ማርች 2016

ፍርድ ቤት የመኢአድ ፕሬዚዳንት የፓርቲውን ማኅተም እንዳይጠቀሙ አሳልፎት የነበረው ዕግድ ተነሳ

ፍርድ ቤት የመኢአድ ፕሬዚዳንት የፓርቲውን ማኅተም እንዳይጠቀሙ አሳልፎት የነበረው ዕግድ ተነሳ


የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ሦስተኛ ፍትሐ ብሔር ችሎት፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ የፓርቲውን ማኅተም እንዳይጠቀሙ አሳልፎት የነበረውን የዕግድ ውሳኔ የካቲት 22 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰጠው ውሳኔ አነሳ፡፡
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንቱ ማኅተሙን እንዳይጠቀሙ ጥር 25 ቀን 2008 ዓ.ም. የዕግድ ውሳኔ አሳልፎ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ እዚህ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ ያደረገው የፓርቲው ላዕላይ ምክር ቤት አባላት በፕሬዚዳንቱ ላይ ያቀረቡት ክስ ነበር፡፡
ፓርቲው ዕገዳው እንደተነሳለት ያሳወቀው ሰኞ የካቲት 28 ቀን 2008 ዓ.ም. ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ዋና ጽሕፈት ቤት በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ነው፡፡ ፓርቲውን የማዳከም ሥራ ከውስጥም ከውጭም ተጠናክሮ እንደቀጠለበት የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባው በመግለጫው ወቅት ገልጸዋል፡፡
‹‹መኢአድ ለኢትዮጵያ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር ፈር ቀዳጅ ነው፡፡ ፓርቲው ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ ከውስጥና ከውጭ በሚነሱ ችግሮች የተነሳ መጠነ ሰፊ የሆነ ፈተና ሲጋረጥበት ቆይቷል፡፡ አሁንም በቅርቡ የግል ጥቅማቸውን ባስቀደሙ ግለሰቦች የሚመራ ቡድን በተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች በመደለል ፓርቲውን ለማዳከም ብዙ ጥረት አድርጓል፤›› በማለትም የቀረበባቸው ክስ ፓርቲውን ለማዳከም በተነሱ ኃይሎች እንደተቀነባበረ አመልክተዋል፡፡
የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት ጥር 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ፕሬዚዳንቱ አቶ አበባው መሐሪ ቀጣዩ ጠቅላላ ጉባዔ እስከሚካሄድ ድረስ ማገዱንና ቀዳሚው ምክትል ፕሬዚዳንቱ አቶ አንድርያስ ኤሮ ፓርቲውን እንዲመሩ መወሰኑን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡
ሆኖም የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባውና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ሙሉጌታ አበበ ይህን ውሳኔ ክፉኛ የተቹትና የተቃወሙት ሲሆን፣ ይህን ውሳኔ ያስተላለፉት ግለሰቦች በተለያዩ ምክንያቶች ከፓርቲው የተባረሩና ራሳቸውን ከፓርቲው ያገለሉ ግለሰቦች እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡
‹‹ፕሬዚዳንቱን አግደናል የሚል ውሳኔ ያሳለፉት ግለሰቦች 16 ብቻ ናቸው፡፡ ከእነዚህ 16 ግለሰቦች መካከል ደግሞ ከፓርቲው ጋር ያልተቋረጠ ግንኙነት የነበራቸው አራቱ ብቻ ናቸው፡፡ ስለዚህ ውሳኔው የፓርቲውን መተዳደርያ ደንብም ሆነ የአብዛኛውን አባላት ይሁንታ ያገኘ አይደለም፤›› በማለት አቶ ሙሉጌታ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
‹‹የመኢአድ የምክር ቤት መቀመጫ ብዛት 105 ነው፡፡ እንዴት ነው 16 ግለሰቦች ፕሬዚዳንቱን ማውረድ የሚችሉት?›› በማለት ውሳኔው የአካሄድ ችግር እንደነበረበት ጠቁመዋል፡፡ ‹‹እንኳን 16 ግለሰቦች 105ቱም የምክር ቤቱ አባላት ቢገኙና ቢስማሙም ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንቱን የማውረድ ሥልጣን የለውም፡፡ በፓርቲው ደንብ መሠረት ፕሬዚዳንቱን የሚያስቀምጠውም ሆነ የሚያነሳው ጠቅላላ ጉባዔው ነው፤›› ሲሉም አብራርተዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱን ያገደው ቡድን በምክንያትነት ከሚያስቀምጣቸው ነጥቦች መካከል አንዱ ፕሬዚዳንቱ ጠቅላላ ጉባዔ ለማድረግ ፈቃደኛ አይደሉም የሚል ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር ፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔውን መቼ ያካሂዳል በማለት ሪፖርተር ላቀረበው ጥያቄ አቶ አበባው ሲመልሱ፤ ‹‹ምንም እንኳን ቀኑን ባንወስንም በመጋቢት ወር ውስጥ ለማድረግ ዝግጅት አጠናቅቀናል፤›› ብለዋል፡፡
ፓርቲው ከዚህ በተጨማሪም በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ አለመረጋጋቶች በሰላማዊና በድርድር እንዲፈቱ ጥሪ አስተላልፏል፡፡ አቶ አበባው ‹‹የከፋ ቅራኔ ሳይፈጠር የሚመለከታቸው አካላት ሕግንና ከዚህ ቀደም የነበረን የአመጣጥና የአሰፋፈር ታሪክን መሠረት በማድረግ በአስቸኳይ መፍትሔ ይፈለጉለት፤›› ብለዋል፡፡
በሽግግሩ መንግሥት የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) በሚል በታዋቂው የሕክምና ባለሙያ በፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የተመሠረተው ፓርቲ በ1994 ዓ.ም. ለሁለት ሲሰነጠቅ፣ አንዱ ቡድን መኢአድ በሚባል ኅብረ ብሔራዊ ቅርፅ ወዳለው ፓርቲነት ከተለወጠ በኋላ በኢንጂነር ኃይሉ ሻውል እየተመራ በ1997 ዓ.ም. ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲ የነበረው ቅንጅት ቁልፍ አባል እንደነበር ይታወሳል፡፡
መኢአድ በሌሎች የቅንጅት የቀድሞ አባላት ከተመሠረተው አንድነት ፓርቲ ጋር ባለፈው ዓመት በተካሄደው ምርጫ ተፅዕኖ ሊኖራቸው ይችላል ተብለው የተገመቱና በአንድ ወቅትም ወደ ውህደት ሊያመሩ ነው ተብሎ የተነገረ ቢሆንም፣ የምርጫ ቦርድ በውስጥ ክፍፍል ጉዳይ ላይ የሰጠው ውሳኔ እጅግ በተዳከመ ሁኔታ ለምርጫው እንዲቀርቡ አድርጓል ተብሎ ይተቻል፡፡
ከምርጫ ቦርድ ውሳኔ በኋላ ይህን መሰል ውዝግቦች ከሁለቱም ፓርቲዎች መስማት የተለመደ ሲሆን፣ ፓርቲዎቹ ይህ ነው የሚባል እንቅስቃሴ ሲያደርጉም አይስተዋልም፡፡

ማክሰኞ 8 ማርች 2016

በዋሽግተን ዲሲና በተለያዩ የአለም ክፍሎች ኢትዮጵያዊያን የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ

‪#‎ETHIOPIA‬ | በዋሽግተን ዲሲና በተለያዩ የአለም ክፍሎች ኢትዮጵያዊያን የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ በዲሲ የፊታችን ማክሰኞ የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ ተደርጓል ቦታውንና ሰአቱን እናሳውቃለን። ‪#‎SurmaProtests‬
ሰሙኑን ኢትዮጵያዊያንን በአንድ ስሜት ቆንጥጦ የያዛቸው ጉዳይ የሰው ልጅ የጭካኔ ጣሪያ እስከየት ሊደርስ እንደሚችል የተረጋገጠበት አጋጣሚ ደቡብ ኦሞ ሱርማ በገመድ አንገትና እጃቸው ተቆላልፎ ከአፍና አፍንጫቸው በድብደባ ብዛት የሚፍሰው ደማቸው እያሳዩ የሚያስጥል ወገን አተው በሃዘን የተገላታው ገፅታቸው የሚታይ ፊቶግራፎች ከሰተራጩ በኋላ ኢትዮዽያውያን በያሉበት ቁጣቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው። ይህን በህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ ጉጀሌ መንግስት የተፍፀመን ግፍ ሁላችንም ሰልፉ ጥሪ በተደረገበት ሃገሮች ላይ በነቂስ በመውጣት ልናወግዝ ይገባል።

Indignation and condemnation against inhumane treatment of indigenous people by Ethiopian police

A photo that surfaced on the social media on Sunday showing the Surma people of South Ethiopia in a chain gang has triggered an uproar and condemnation against the brutality of the forces of the tyrannical regime in the country.
The undated pictures show a group of men, loaded on a police pickup truck, one’s neck tied to the upper arm of another while also tied at their knees. The story that circulates with the picture in the social media say the people were arrested while protesting the encroachment of their natural habitat by the regime for sugar plantation. The exact location of the pictures is not clear but the insignia on the pickup truck is of the police in South Ethiopia.
Previous reports by media and rights groups show thousands of indigenous people in Ethiopia’s lower Omo valley were uprooted due to land grab by officials of the government and their cronies, commercial plantation as well as the building of hydroelectric dams.
Statistics show there are about eight tribes with a total of 200,000 indigenous people in South Omo whose way of life has not been tampered by modernization.
Survival International say it has been a documented fact that those indigenous people were being uprooted from their land without their consent and were exposed to health problems in their new settlement. SI also recalled the recent brutal action by the police against the people of Omo.
The people of the lower Omo valley in Ethiopia have been one of the top tourist attractions in country due to their unique way of life, culture and their interaction with the natural environment.

ዓርብ 4 ማርች 2016

የጃዋር መሃመድ ቅኝቶች

ክንፉ አሰፋ
Jawar Mohamed Muslim fundamentalist
ጃዋር መሃመድ
መገናኛ ብዙሃንን መቼ እና እንዴት መጠቀም እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል። የሚፈልገውን  ነገር ሁሉ ከፈጸመ በኋላ ግን እንደ በረሃ ተኩላ እያደፈጠ ይናከሳል። ሲናከስ ደግሞ ማንንም አይምርም።  ውለታ የሚባል ነገር አያውቅም። ይሉኝታ አይነካካውም። እፍረትም በእርሱ ዘንድ የለችም። ከቶውን መቀበል እንጂ መስጠትን አያውቅም። አስር ተቀብሎ በዜሮ የሚሸኝ ጀግና ነው። በዚህ ተግባሩ አድናቂው ነኝ። “እኔ-ነኝ” ያለ የዲሲ ፖለቲከኛን ሳይቀር ከአንዴም ሁለቴ እንደማስቲካ እያኘከ መትፋቱን እንመሰክራለን። የጡት አባቱ የሆነው  ኦነግንም ቢሆን ‘A Critical Assessment of the Oromo Liberation Front” በሚለው መጣጥፉ እንዳይሆን እንዳይሆን አድርጎ የጠረበ ፍጡር ነው። ይህ ሰው እንደገና ተመልሶ የ”ነፍጠኛውን ሜድያ” ለመጠቀም የማይሞክርበት ምክንያትም የለም።
ጃዋር  በኢትዮጵያ  የፖለቲካ ብቅ ያለው በቅርቡ ነው። በመጀመርያም ሆነ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በተማረባቸው ዱሙጋም   እና  ጭላሎ፣ አዳማም  ሆን  ሲንጋፖር ሆኖ ድምጹ  አልተሰማም። የፖለቲካ ሂሳቡን ሰርቶ ሲያበቃ የበግ ለምድ ለብሶ ብቅ አለ።  በሚኖሶታ ያለመውን  ቅዠት ይዞ  ዋሽንግተን ዲሲ ላይ ሲደርስ ባነነ። እዚያው  ላይ ፈነዳ። ከዚያ በፊት ስሙም ተሰምቶ አያውቅም። እስከ ዲሲ ጉዞ ድረስ የኦሮሞ ህመም አይሰማውም ነበር። “ትንሽ ቆሉ ይዞ ወደ አሻሮው… “ እንዲሉ የኦሮሞነት ጆከሩን ይዞ ፖለቲከኞችን እና መገናኘ ብዙሃኑን  መቅረብ ነበረበት።  እነሱም ከሚገባው በላይ አስተዋወቁት። በደንብ አድርጎ ቦነሳቸው። ምሁር በሃገር የጠፋ እስኪመስል ድረስ መድረኩን  እሱ በቻ ተቆጣጠረው።  ቪ.ኦ.ኤ.፣  አልጃዚራ፣ ሲ.ኤን. ኤን፣  እና ዶች ቬለ ላይ ሳይቀር እየወጣ የኛን እጣ ፈንታ እስኪበቃን ነገረን።  “ወጣቱ ምሁር”  አንቱ የተባለ የኢትዮጵያ  ጉዳይ ተንታኝ ሆኖ ከረመ።  ድምሩን ካወራረድ በኋላ ፊቱን አዞረ። አዟዟሩ አደገኛ ነው። የፍሬቻ ምልክት ሳያሳይ እንደሚታጠፍ መኪና አይነት። “ይህ ሰው በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የጫነው ዲግሪ  ነው ወይንስ ድንጋይ?”  እስኪያስብል ድረስ በዘርና በሃይማኖት በፖለቲካ  ፈነዳ።
ባጣ ቆዩን ትግል ሲቀላቀል ለአፍ  ሟሟሻው  አጼ ምኒሊክን  አነሳ። የእምዬ ምኒሊክ አጽም እና ሃውልት ላይ ክተት አወጀ። ግዜ የሰጠው ቅል… እንዲሉ እንጂ የመላው ጥቁር ሕዝብ ማንነት መነሻ የሆኑት ምኒሊክ በሱ አፍ የሚጠሩ እንኳን አልነበሩም። ዳሩ መነሻውን የማያቅ መድረሻ የለውም። ሁለት አይን ያለው፤ ከሁለት አቅጣጫ ይመለከታል።  ሁለት ጆሮ ያለውም ሁሉንም አመዛዝኖ ይሰማል።  አንገት ያለው ደግሞ  አዙሮ ያለፈውን ይመለከታል። ያለፈው ከሌለ የወደፊቱ ከምን ሊነሳ? ጃዋር  በአምሳሉ  የፈጠራቸውን  ምስለኔዎችን   በሱ የፖለቲካ ዜማ ቃኝቶ ሲያበቃ በፓልቶክ ክፍሎች አሰማራቸው።
ከሁሉም የሚያሳዝነው  ደግሞ ገና ነብስ ያላወቁ ሕጻናትን ፎቶ በማህበራዊ ድረ-ገጾች እየበተኑ ለራሳቸው የፖለቲካ ግብ መጠቀም መሞከራቸው ነው። በሞራልም፣ በስነ-ምግባርም ሆነ  በባህል  ፍጹም ነውር የሆኑ ነገሮችን እያሰሙን አብረን ከረምን።  በቃ! የጃዋር ፖለቲካ ይኸው ነው።   ይህ ነው የሱ ጀግነነት።  ምኞቱ ጀግና መሆን ከሆነ ደግሞ ቦታው  ሚነሶታ አልነበረም።  ስለ አመጽ የሚሰብክ ወንድ ልጅ መኖርያው ልክ እንደ አንበሳ ከወደ በረሃው ነው።
ይህ ሰው በፌስቡክ ገጹ ላይ ያሰፈረውን አንድ ጽሁፍ ካነበብኩ በኋላ፤ ለዚያ አሳፋሪ  ጽሁፍ ምላሽ በመስጠት እና ባለመስጠት ላይ ከራሴ ጋር ሙግት ገጥሜ ነበር። በጃዋር ገጽ ላይ የሰፈረው በዚያ አስጸያፊ ጽሁፍ ያልቆሰለ ቢኖር ጉዳዩ ያልገባው ብቻ መሆን አለበት።  በእርግጥ ሌሎች እንዳደረጉት ነገሩን  ንቆ  መተው ይቻላል።  ታድይ የሰው ዝምታ እንደስምምነት የተወሰደ ይመስል የሰውዬው ሙቀት እየጨመረ ሄደ። በተቀረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ላይ የጥላቻ ዘመቻውን ገፋበት። በዓድዋ እና የአጼ ምኒሊክን ቅኝት በአዲስ ዜማ ይዞ ዳግም ብቅ አለ። እንደራሴውን በስውር እየሰበሰበ በባንድራችንና በኢትዮጵያዊነት ላይ ዘመቻ አቀደ። ይህንን በሰፊው እመለስበታለሁ።
በፌስቡክ ገጹ ላይ የሰፈረው የጃዋር መልእክት እንዲህ ይነበባል፤
…Enjoy the show, the bill is on us… ወደ አማርኛ በግርድፉ ሲመለስ “(የኦሮሞ አመጽ) ትዕይንቱን እያያችሁ ተዝናኑ። ሂሳቡን በኛ ተውት።”  እንደማለት ነው።
አሳዛኙን  የኦሮሞ  ወገኖቻችን  እልቂት ነው ተዝናኑበት እያለን ያለው።  ይህንን አሰቃቂ ድራማ ከሚነሶታ ሆኖ ሲመለከተው   አስቂኝ ነው  የሆነበት። እሱ ምን አለበት? እሳቱ  ውስጥ አልገባ።  ወላፈኑም ፈጽሞ አይነካው። ምሰቆቃውን እንደ ሆሊውድ ፊልም  ቁጭ ብሎ መመልከቱ ሳይንሰው ሌሎችንም በራሱ ወጪ  ለመጋበዝ የሚዳዳው ደፋር።  ይህ  ስላቅ ነው ወይስ  ፌዝ?  ከሞቀ ቤቱ መሽጎ  በሰው ልጅ ሰቆቃ መቀለዱ አንድ ነገር ነው። ከሁሉም  የሚያስገርመው ደግሞ በዚህ ጽሁፍ ስር ድጋፋቸውን የሚገልጹ   እንደራሴዎቹ ብዛት ነው። ሰው በዘር ፖለቲካ ሰክሮ ማሰብና ማገናዘብ ተስኖታልም ያሰኛል። ጽሁፉ በግልጽ እንደሚያስረዳው እየተካሀደ ያለው እልቂት ላይ ጃዋር ማፌዙ አልገባቸው ይሆን? በዚያው የፌስ ቡክ ገጽ ላይ የሚወጡ  ዘግናኝ ፎቶዎችን  እየተመለከተ የሚዝናና ሰው  ካለ ይህ ጤነኛ አይደለም። የአእምሮ ችግር ያለበስ ሰው እንኳን በዚህ አይነቱ የሰዎች ሰቆቃ  የሚዝናና አይመስለኝም። ግን የዚህ ሰው ፍላጎት ምን ይሆን?
በዚያ ሰሞን ወዳጄ ሄኖክ የሺጥላ የለቀቀው ጽሁፍ ጃዋርን በደንብ አድርጎ ይገልጸዋል።
“እንጀራውን” በተገፉ እና በተከፉ ሰዎች ታሪክ ላይ ያደረገ ሰው ፣ ህይወቱን በሰዎች መከራ ላይ የገነባ ፣ ኑሮውን ባጋጣሚ ለድምጽ አልባ እና አቅም አልባ ወገኖቹ  ለታይታ የሚቆጭ…. ራሱን ትልቅ ለማድረግ፣ ከፊት ሆኖ ለመታየት እና ለመግነን ማናቸውንም አይነት ክፋት ከመፈጸም ልቡ ተው የማይለው ሰው።  ሲል ሄኖክ ይገልጸዋል። እኔም ጃዋርን ከዚህ በተሻለ አልገልጸውም።
ሲጀመር እየተካሄድ ባለው የኦሮሞ ወንድሞቻችን የመብት ትግል ውስጥ የእነ ጃዋር እጅ መግባቱ አብዛኞችን ጥርጣሬ ውስጥ ከትቷል። ምክንያቱም ግልጽ ነው። የኦሮሞ ወጣቶች እና ገበሬዎች ስለ መብት ሲሟገቱ የእነ ጃዋር አጀንዳ ደግሞ ሌላ በመሆኑ።
የኦሮሞ ተማሪዎችና ገበሬዎች ይዘውት የተነሱት ጥያቄ አግባብ ያለውና በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊደገፍ የሚገባው ጉዳይ ሆኖ ሳለ ሌላው ወገን ዳር ቆሞ የመመልከቱ ምስጢር ግልጽ ይመስላል። እነዚህ ወገኖች መብታቸውን  ለማስከበር የማያባራ  ትግል እያደረጉ ባሉበት ወቅት እነጃዋር በረጅሙ ምላሳቸው ሌላውን ወገን የሚያስበረግጉ መፈክሮችን ይዘው ብቅ አሉ።  “ኦሮሚያ ለኦሮሞ!” እና “የክርስትያኑን አንገት መቁረጥ!”  መፈክር!
እርግጥ ነው። ጃዋር ረጅም  ምላስ አለው። ወገን የሚሻው ደግሞ ረጅም ምላስ ሳይሆን ረጅም  ጭንቅላት ነበር።  የሁለቱ  ልዩነት የትየለሌ ነው። ረጅም ጭንቅላት አርቆ ሲያስብ ረጅም ምላስ ደግሞ ከሩቅ ይስባል። እንደ አለመታደል ሆኖ ባለ ረጅም ምላሶች የህዝብን የመብት ጥያቄው እየነጠቁ በራሳቸው አጀንዳ ይተኩታል።  እናም የዚህ ትግል ውስጥ  ሌላው ወገን  ተመልካች ብቻ እንዲሆን ያደረጉት ጃዋር እና በሱ የፖለቲካ ቅኝት ውስጥ ያሉት ደቀ መዛሙርቱ  ናቸው። እነዚህ ሰዎች ይዘውት የተነሱት መፈክር ሌላውን ወገን ባያስበረግግ  ነበር የሚገርመው። አንዳንድ ቦታዎች የጃዋርን መፈክር የያዙ ሰልፈኞችን  የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች ማሰማራታቸውን ማስተዋሉ ለዚህ ማስረጃ ይሆናል።
በአንድ ወቅት  በጃዋር የሚመራ ይህ  ቡደን ዋሽንግተን ዲሲ ስቴት ዲፓርትመንት በር ላይ ቆሞ፣  “Ethiopia out of Oromia”!  “ኢትዮጵያ  ከኦሮሚያ ጥውጣ!”  እያለ ፈረንጆችን ይማጸን  የነበረበትን ማስረጃ ከዩቱብ ላይ መመልካት ይቻላል። (https://www.youtube.com/watch?v=uXah_qtW8sg)
በሌላ ግዜ ደግሞ “…እኔ በምኖርበት አካባቢ ቀና የሚል ክርሲያን ከተገኘ አንገቱን  በሜንጫ ቆርጠን እንጥላለን::”(https://www.youtube.com/watch?v=RMLLmAMWdG8)  ሲል የአይሲስን አንገት  ቆረጣ በአደባባይ ያበሰረ ሰው ነው።    እዚህ ላይ ልብ በሉ። ወንጀል የሰራን ክርስትያንን  ሳይሆን “ቀና የሚል” ከተገኘ ነው እናርዳለን ያለው። ልቡ ያሰበውን እና አእምሮው የሚትያሰላስለውን ነው ያፈነዳው። የተናገረው በስህተት እንኳን ቢሆን ንግግሩን ባስተባበለው ነበር።
ከዶ/ር መረራ ጉዲና ጋር አንድ ምሽት በአምስተርዳም ስንጫወት፣ “በእርግጥ ጃዋር መሃመድ የክርስቲያን  አንገት  እቆርጣለሁ ብሎ ተናግሯል?” ሲል ጠየቀኝ። አብሮን የነበረው ገረሱ ቱፋም  “ንግግሩን  ከኮንቴክስት መረዳት አለብን…”  እያለ ሲያስረዳ  ሞከረ። ገረሱ ቱፋ በዩኒቨርሲቲ  ለኦሮሞ መብት ሲታገል ቆይቶ በኋላም በአስመራ በኩል ሞክሮ  ሲያበቃ በሆላንድ በስደት የሚኖር ወጣት ነው።  ኮንቴክስቱ ባይገለጽልንም  ከዩትዩብ ላይ ያወጣሁት ቪድዮ አንገት በሜንጫ ስለመቁረጥ በግልጽ አማርኛ አስቀምጦታል።  በዚያ እለት ነበር የኦሮሞ ሕዝብ በብዛት የሚኖረው በሸዋ እንድሆነና ይህም የክርስትና እምነት ተከታይ  መሆኑን ዶ/ር መረራ ያስረዳን።
በእነ ማልኮሜክስና በእነ ማርቲን ሉተር ምድር ቁጭ ብሎ አይሲስን አንገት መቅላት ወንጀል መናገሩ አይደለም የሚገርመው። ይህንን በአደባባይ በኩራት ሲናገር ህግ ባለበት ሃገር ዝም መባሉ እንጂ።
አል ጃዚራ ላይ ወጥቶ ኢትዮጵያዊነት በላዩ ላይ እንደተጫነበትም ደስኩሯል። ይህንን ዲስኩር ከሱ ውጭ ከሌሎች የኦሮሞ  ልሂቃን አልሰማንም። በማንነት ቀውስ ውስጥ ካለ ሰው ይህንን መስማቱም ሊደንቀን አይገባም። ይልቁንም ይህንን ከነ በቀለ ገርባ ፣ ከዶ/ር  መረራ፣  ከበአሉ  ግርማ ፣  ከሎረት ጸጋዬ ገ/መድህን፣  ከዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ወይንም ከአቶ ቡልቻ ደመቅሳ አንደበት ብንሰማው እበር የሚከብደን።      በእንደዚህ አይነት የጥላቻና የዘረኝነት እምሮው  የታወረ  ሰው  እመራዋለው የሚለው አመጽ ላይ ለማበር የኢትዮጵያ ህዝብ ፈቃደኛ ባይሆን ሊደንቀን አይገባም።  ከየትኞቹም  የኦሮሞ  ልሂቃን  እንዲህ አይነት  የኦሮሞ ሕዝብን ክብር የሚነካ ንግግር ሰምተን አናውቅም። “ኢትዮጵያ ከኦሮሚያ ትውጣ” “የክርስትያኑን አንገት በሜንጫ እንቆርጣለን” ሲል የትኛው የኦሮሞ ወገን ወይንም የትኛው የሙስሊም  ህብረተሰብ  ጃዋርን  እንደወከለው አናውቅም።  ልቡን ሞልቶ ሲናገር ግን የኦሮሞን ህዝብ ከሌላው ወገን ነጥሎ ለማስመታት የታቀደ አደጋ ላይ ሊጥለው እንደሚችል ግልጽ ነው።
የፖለቲካውን ምህዳር ጠቆጣጥረው ዘረኝነትን እና ጥላቻን ሲሰብኩ ምን እናደርጋለን? ንቆ መተው ወይንስ ቀይ መብራት ማሳየት?  ቤንጃሚን  ፍራንክሊን፣  ስለጥቃቅን  ነገሮች  ሲናገር፣  “በጥቃቅን ነገር ተጠንቀቅ፤ ትንሽ ፍሳሽ – ትልቅ መርከብን ታሰምጣለች።” ብሎ ነበር።  በእርግጥ  መርከቡ ሊሰምጥ የሚችለው  ውሃ መርከብ  ውስጥ እንዲገባ  ስንፈቅድላት  ብቻ ነው።
የጃዋርን አካሄድ ሳሰላስለው ቦካሳ ይታወሰኛል። የትም አይደርስም  የተባው  የማእከላዊ  አፍሪካው አስር አለቃ  ቦካሳ፣ ሁለቱም ተመሳሳይ አመጣጥ አላቸው። ሁለቱም በማንነታቸው የሚያፍሩበት የበታችነስ ስሜት ውስጥ የኖሩ ናቸው። ሁለቱም  የማንነት ቀውስ ውስጥ የነበሩ ናቸው። ጃዋር  በአንደበቱ  እንደነገረን  የአማራ እና  የኦሮሞ፣  የክርስትያን እና የሙስሊም ቅልቅል ነው። እንደዚህ የተበሳተሩ  ብዙ አሉ። አብዛኞቹ ታዲያ በማንነታቸው ይኮራሉ።   እንደ ጃዋር ያሉ ጥቂቶች ግን የስነ-ልቦና ቀውስ ውስጥ ቢገቡ አይደንቅም።  አባት እና እናቱን የማያውቀው ቦካሳ  ከ 12 አመቱ ጀምሮ የማንነት ጥያቄ  ሲያንገላታው የነበረ ሰው ነው። የም ሆኖ የትም አይደርስም እየተባለና የተናቀ ወታደር ነበር።  የሃገሪቱ  ርእሰ ብሄር ይሆናል ብሎ ያሰበ አልነበረም።  አስር አለቃ ቦካሳ በለስ ቀንቶት እ.ኤ አ. 1966 በመፈንቅለ መንግሰ ስልጣን ይዞ ሲያበቃ  የማእከላዊ አፍሪካን ህዝብ ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ፈጀ ሀገሪቱን እንዳልነበረች አደረጋት።
ሰዎች ለአዶልፍ  ሂትለርም  የነበራቸው አመለካከት  ከዚህ የተለየ ልነበረም። አንድ  የጀርመን ታሪክ ተመራማሪ  ሁኔታውን ሲገልጸው “They all had one thing in common – they underestimated Hitler” ነበር ያለው። ሁሉም  የሚጋሩት አንድ ነገር ነበር።  ሁሉም  ሂትለርን ንቀውት ነበር። በመጨረሻ  ሂትለር የጀርመን  አዲሱ  ቻንስለር ሆኖ ብቅ ሲል የናዚ ፓርቲ አባላት በደስታ እና በእንባ ተቀበሉት።  በሀገሪቱ  ህግ ሳይሆን በሂትለር  አምላኪ ሆኑ።  የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ሳይሆን የጃዋር አምላኪዎች እያደረጉ እንዳሉት ማለት ነው።  ጃዋር “የእልቂቱን ትእይንት በኔ ሂሳብ እያያችሁ ተዝናኑበት” ያለውን  አጢነው አይመስለኝም። በደፈናው ስለሚያመልኩት እንጂ።
ቦካሳም ሆነ ሂትለር በጥላቻ የመጡ ስለነበሩ ከምደር-ገጽ ጠፍተው ታሪክ ሆነው አልፈዋል። ጥለውት የሄዱት አሻራ ግን እስካሁን አለ።