ቅዳሜ 19 ጁላይ 2014

Police detained more than 6 andnet party members at the get of Arada court. As Finote netsanet’s informers

Police detained more than 6 andnet party members at the get of Arada court. As Finote netsanet’s informers
- Daniel Feyisa –from udj
-Abinet regasa - from udj
-Fasika -from udj
- Berhanu YegelTu -from udj
- Mesele Admase from udj
-Tilaye Tarekegne - from udj are detained at ‘’Maekelawi’’ will list all lists soon.

ወይንሸት ሞላ ክፉኛ ተደብድባ ዝግ ችሎት ቀረበች!


ወይንሸት ሞላ ክፉኛ ተደብድባ ዝግ ችሎት ቀረበች!

(EMF) በትላንትናው እለት አንዋር መስጊድ ህዝበ ሙስሊሙ ሲደበደብ ወይንሸት ሞላ በስፍራው ነበረች። አንድ ከዚህ በፊት የሚያውቃት የደህንነት አባል በቀጥታ ወደሷ መጥቶ ይደበድባት ጀመር። በወቅቱ በስፍራው የነበረው በፍቃዱ ጌታቸው ስለሁኔታው እንዲህ በማለት ጽፎ ነበር።
በወቅቱ የሰማያዊ ፓርቲ የሰማያዊ ፓርቲ የብሄራዊ ምክር ቤት አባል የሆነችው ወጣት ወይንሸት ሞላ አብራኝ ነበረች፡፡ አንዋር መስጊድ በወንዶች መግቢያ ፊት ለፊት ካለው ህንጻ ላይ ሆነን ሁነቱን ስንከታተል ከአሁን ቀደም የሚያውቃትና ከህንጻ ላይ ሆኖ ሲቀርጽ የነበር ደህንነት ብቻዋን ነጥሎ እየደበደበ ወሰዳት፡፡  ‹‹ለምን ተወስዳታለህ!›› ብዬ በጠየኩበት ወቅት ከእነዛ ከመንገድ ተለቃቅመው ለድብደባ የተሰማሩት ወጣቶች መካከል አንዱ ሽጉጥ አወጣብኝ፡፡ ለመሳሪያ ልምድ የሌለው በመሆኑ ካርታው እግሩ ስር ወደቀበት፡፡ ወይንሸትን ይዘውም ወደ ውጭ ከነፉ!
ወይንሸት ሞላ
ወይንሸት ሞላ
ዛሬ ፍርድ ቤት ይዘዋት ቀርበዋል። ሁኔታውን የተከታተለው ዮናታን ተስፋዬ የታዘበውን እንዲህ በማለት ነው ያቀረበው። “እጇቿ ክፉኛ ተጎድተዋል፡፡ ጣቷ አብጧል፡፡ ፊቷ ገርጥቷል፡፡ የግራ እጇ በፋሻ ተጠቅልሎ አንገቷ ላይ እንደታሰረ በአንድ ፖሊስ እርዳታ ወደ ፍርድ ቤቱ ግቢ ገብታለች፡፡” ብሎ ነበር። ጥቂት ቆይቶ ባስተላለፈው መልእክት ደግሞ “ወይንሸት ጭንቅላቷን በቀኝ በኩል ተፈንክታለች፡፡ ተሰፍቶ ይታያል፤ ቀኝ እጇ መሰበሩ ተረጋግጧል፡፡ ሰውነቷ በጣም መጎዳቱ ያስታውቃል፡፡ ከፍርድ ቤት መልሰው አዲስ አበባ ፖሊስ ከሚሽን ወስደዋታል፡፡ ማንም እንዲያያት አልተፈቀደም የፍርድ ሂደቱንም ማንም መከታተል አልቻለም፡፡ ስንቅ ማቀበልም ተከልክሏል፡፡” በማለት ሁኔታውን አስረድቷል።

አሁን በደረሰን ዘገባ መሰረት በዝግ ችሎት የቀረበችው ወይንሸት ሞላ 14 ቀን ተጨማሪ ምርመራ ተጠይቆባት፤ 14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባታል፡፡ የፍርድ ቤቱን ሂደት ማንም ሰው እንዲከታተል አልተፈቀደም የህግ ሰውም እንዳያናግራት ተከልክሏል፡፡  አሁን ከማዕከላዊ አጠገብ በሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እስር ቤት ነች፡፡ የፖሊስ ጣቢያው ኃላፊዎች ማንም ሰው ሊያያት እንደማይችልና ስንቅም ሆነ ልብስ ላልተወሰነ ቀናት እንዳይመጣ በማለት መልሰውናል፡፡
አሁን ያለው ሁኔታ ይህን ይመስላል። ትንሽ ቆይተው እሷንም አሸባሪ ብለው መክሰሳቸው የማይቀር ነው። ሌላ የሽብር ክስ ከመስማታችን በፊት፤ ትክክለኛውን ነገር ከወዲሁ እንዲረዱት፤ ወይንሸት ሞላ ወደ አንዋር መስጊድ ከመሄዷ በፊት አግኝቷት የነበረው ዮናታን ቀደም ብሎ የዘገበውን እናስነብብዎ። እንዲህ በማለት ጽፎ ነበር።
ወይኒ ትናንት ጠዋት ላይ ቢሮ ቁጭ ብዬ ከላፕቶፕ ላይ እንደተደፋሁ መግባቷንም ሳላስተውል . . .
“እዚህ አፍንጫችን ስር ይህን የመሰለ ሰላማዊ ትግል ሲካሄድ ቢያንስ ሄደን አንታዘብም!? እዚህች መርካቶ አጠገብ ተቀምጠን ዘመን እየተጋራን – ታሪክ እየተጋራን . . .” ስትል ቀና ብዬ አየኋት።  . . . ምንም ማለት አልደፈርኩም. . . ለብዙ ጊዜ አንዋር መስጂድ እሄድ ነበር (በተለይ ባለፈው ዓመት)  የግልና የፖለቲካ ስራ ጊዜ አይሰጥም እንጂ አሁንም ብገኝ ምኞቴ ነው ፤ ሰው በጨካኞች ተከቦ ለመብቱ በፅናት ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ሲጮህ መመልከት በራሱ ትልቅ መነቃቃት እና ተስፋ ይሰጣል፡፡
ወይኒን ተረዳኋት ግን ሰጋሁ፡፡ ምክንያቱም ወይኒ ቀጥተኛ ሰው ነች . . . የሰው ጥቃት አትወድም . . . ሰው ሲበደል እያየች ዝም የሚል አፍ አልፈጠረባትም . . . ትናገራለች በጣም ተቆጥታ ትናገራለች . . . እንኳን በቆመጥ ሲደበደቡ እያየች በክፉ ሲታዩም ይተናነቃታል . . . ከእንባዋ እየተናነቀች ምራቋን ውጣ ትናገራለች . . . ወይኒ እንዲህ ነች . . . ምናልባትም ይህ ተቆርቆሪ ስብዕናዋ ይሆናል ሰማያዊ ፓርቲ ከትማ ያገናኘን፡፡ እናም ሰጋሁ፡፡
እንጃ ቀልቤ የሆነ ነገር ሊፈጠር እንደሚችል አስቀድሞ አሳወቀኝ መሰል . . .  “ምንም እኮ አዲስ ነገር አይፈጠርም I’ve been there, you know, it’s all the same every Friday” ከልቤ አልነበረም …
“መርካቶ ጉዳይ አለኝ በዛው ሙስሊም ወገኖቼን አየት አየት አድርጌ እመለሳለሁ” ከነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ ጌታቸው ሽፈራዉ ጋር እንደምትሄድ ነግራን ሄደች። ጌች ተደብድቦ ሲመለስ እሷ በዛው ቀረች . . . የፈራሁት ሆነ የህወሓት ካድሬዎች እንደሚጠሏት አውቃለሁ፤ ግን ፅናቷ ያፅናናኛል፡፡
ጎንደር አብረን ታስረን የማይረሳ ትዝታ ቀርፃብኝ ነበር . . . የሳዑዲ መንግስትን ተቃውመን አደባባይ ስንወጣ ሶስት ጨካኝ ፌደራሎች ብቻዋን ደብድበዋት ኢያስፔድ ታቅፎ ከወደቀችበት ነጥቆ አስጥሏት ሮጦ ከጨካኞች ሲያመልጥ እንኳን በደከመ ሰውነቷ ወደ ተቃውሞው ለመመለስ ፍላጎት ነበራት . . . ማርች 9 የሴቶች ሩጫ ጊዜ ከጣይቱ ልጆች ጋር ከፊት ሆና እየመራች የህወሓት ደህንነቶች አይን ውስጥ መግባቷ በምርመራ ወቅት ለረጅም ሰዓት ያቆዩአት ነበር . . .
የሆነ ሆኖ የወይንእሸት ሞላ ዛሬ በእጃቸው ድጋሚ ገብታለች . . . በመጥፎ ሁናቴም ተደብድባ ተጎድታለች፡፡ ደስተኛ እንደሆነች ግን ውስጤ ይነግረኛል . . . እሷ ነፃ ነች የውስጧን ጥያቄ መልሳ ሰላም አግኝታለች፡፡
በርካታ ሙስሊም ወገኖቻችንም ይህ ሰላምና እርካታ በመከራና በእስር ውስጥ ሆነው እንደሚሰማቸው አምናለሁ፡፡ ለእውነት በፍቅርና በይቅርታ የቆሙ አይወድቁም ነብዩም መሲሁም ያስተማሩን ይህን ነው!!! በርቱ!” በማለት ነበር የትላንቱን ውሎ የገለጸው። ዛሬ ደግሞ ሌላ ቀ ነው፤ ወይንሸት ክፉኛ ተጎድታ ጉዳይዋ በዝግ ችሎት ታየ። መልሰውም ወሰዷት። እኛም መጨረሻዋን ሰላም ያድርገው፤ በማለት እንሰናበታለን።

የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራር በዞኑ አቃቤ ህግ ይግባኝ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራር በዞኑ አቃቤ ህግ ይግባኝ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ
**************************************************************
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በደቡብ ክልል የወላይታ ዞን የፓርቲው አመራር የሆኑት ወ/ሪት ሀዲያ መሀመድ ዓሊ አንድነት ፓርቲ በወላይታ ለሚያደርገው ሕዝባዊ ስብሰባ በፓርቲው የተዘጋጀ ፍላየር ከፓርቲው አባሎች ጋር በመሆን ሲያሰራጩ በፖሊስ ተይዘው መታሰራቸው የሚታወስ ሲሆን ጥር 8 ቀን 2006 ዓ.ም በወላይታ ዞን ፍ/ቤት ቀርበው በ1000. 00 /አንድ ሺህ ብር/ ዋስትና መለቀቃቸውን ፍኖተ ነፃነት መዘገቧ ይታወሳል፡፡
በወላይታ ዞን ከ/ዐ/ህግ ይግባኝ ባይነት ጥር 8 ቀን የተሰጠው ውሳኔ ተከሳሿ ጥፋተኛ የተባሉበት ወንጀል በዓለም አቀፍ ሽብርተኞች አስተሳሰብ ሲቀሰቅሱ የነበሩትን እንዳለ በመውሰድ ከአስተሳሰብ ባለፈ መልኩ በተግባር በአገራችን ውስጥ ተቻችሎ የመኖር ሁኔታ የሚያቃውስና ወደ ጦርነት የሚያመራ ጽሑፍ በርካታ ገፆች ይዛ የተገኙትን ግለሰብ በጥፋታቸው ልክ መቅጣት ሲገባ በጣም ዝቅተኛና ተመጣጣኝ ያልሆነ ቅጣት በመሰጠቱ ቅር ብሎኛል በማለት የስር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማሻሻል ከጥፋታቸው ጋር የሚመጣጠን ቅጣት እንዲሰጣቸው በማለት በወላይታ ከተማ ለሚያስችለው መደበኛ ተዘዋዋሪ ችሎት እንዲቀርቡ አዟል፡፡
በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች የተቃዋሚ ፓርቲ አባሎችን በማስፈራራት፣ በመደብደብና በማሰር ሀሰተኛ ምስክር አዘጋጅቶ ክስ መመስረት ለማሸማቀቅ የሚደረገው ሙከራ አባላትን እያጠናከረ እንጂ እነሱ እንደሚያስቡት እንዳልሆነ ለፍኖተ ነፃነት የገለጹት የፓርቲው አባላት ወደፊትም ሰላማዊ ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡

ረቡዕ 16 ጁላይ 2014

የመኢአድና አንድነት ውህደት አመቻች ኮሚቴ የባንክ አካውንቱን ይፋ አደረገ


የመኢአድና አንድነት ውህደት አመቻች ኮሚቴ ስራውን በቅልጥፍና እና በትጋት እየተወጣ መሆኑን ለፍኖተ ነፃነት የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በዚህም መሰረት ለጉባኤው መሳካት ይረዳ ዘንድ መላው ኢትዮጵያውያን እንዲተባበሩ ጥሪ በማድረግ የባንክ አካውንቱን ይፋ አድርጓል፡፡
የባንክ አካውንት ቁጥር አቢሲኒያ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ UDJ A/C 47
የባንክ አካውንት ቁጥር አቢሲኒያ ባንክ ቦሌ ቅርንጫፍ AEUP SP 235

ማክሰኞ 8 ጁላይ 2014

ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ለኢትዮጵያ ሕዝብ የቀረበ የሰላማዊ ትግል ጥሪ


“ኢትዮጵያን ለመታደግ በንቃት እንደራጅ!!

ዛሬ በረገፈ ዘውዱና በረገበ ዙፋኑ ላይ ያለ አቅሙና ያለ ህዝባዊ ይሁንታ የቆጥ ላይ እንቅልፍ የሆነበትን “ሥልጣን” የሙጥኝ ብሎ ያለው መካሪና ዘካሪ አልባው የህወሓት /ኢህአዴግ “መንግሥት” የሚንሊክ ቤተ-መንግሥትን ከተቆጣጠረ ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ የራሱን ስውር ደባ ለማስፈፀም በሚያመቸው መንገድ ጥንተ ገናናዋን፣ የዓለም የነፃነት ተምሳሌቷን፣ የጥበብና የሥልጣኔ ጮራዋን፣ የይሁዲ የክርስትና የእስልምና ማደሪያ የሆነች ምድረ ገነት የብዙሺህ ዓመት እመቤት ውዲት ሀገራችን ኢትዮጵያን ከፋሺስት ጣሊያን ተውሶ ባመጣው ሽንሸና በዘርና በቋንቋ አቧድኖ ላለፉት 22 ዓመታት በአሰቃቂ ጭቆና በግፍ ረግጦ ሲገዛህ ቆይቷል፤ ይህንን ህዝብን በሙልጭልጭ ሰንካላ ምክንያቶች በመከፋፈል /በመለያየት፣ በማባላት /በማናከስ፣ በመናቅ/ በማዋረድ፣ በማሸማቀቅ /አንገት በማስደፋት ለመዋሸት /በመቅጠፍ ላይ የተመሰረተ የእውር ድንብር አስተዳደሩን የሚቃወሙ ዜጎችን በማሳደድ፣ በመደብደብ፣ በመግደል፣ ከሥራና ከመኖሪያ በማፈናቀል፣ ያፈሩትን ሃብት በመዝረፍ፣ ከቤተሰብና ከትዳር በመለያየት፣ ዘብጥያ በማውረድ፣ በኃይማኖት ጣልቃ በመግባት ከፈጣሪያቸው በመለየት፣ ራሳቸውን እንዲያጠፉ በማድረግ፣ የገዛ ሃገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ ከፈተኛ ጫና በማድረግ “የነፍስ ውጪ የነፍስ ግቢ” የጣር እስትንፍሱን ለማራዘም ሲፍጨረጨር ቆይቷል እየተፍጨረጨረም ይገኛል፡፡
ህወሓት /ኢህአዴግ የአንባገነንነቱን በትር ከጨበጠበት እለት ጀምሮ ከራሱ መሰል ግለሰቦችና ተላላኪዎች በስተቀር ሌሎች ዜጐች በሀገራችን ባይተዋርና የበይ ተመልካች ሆነን ለአንዲት ቀን እንኳ ከኑሮ ግብግብ አፎይ ሳንል በምንጓዛት አንዲት እርምጃ ሁሉ እንቅፋት የተሞላው ድቅድቅ ጨለማ ሆኖብናል፡፡ በዚህም ምክንያት ቀደም የነበረን የውስጥ ደስታና የርስ በርስ ፍቅር አጥተን በአስከፊ ስቃይ ላይ እንገኛለን፡፡
የሀገሪቱ የፖለቲካ የኢኮኖሚና ማህበራዋ እንቅስቃሴ ፈፅሞ ፍትህ የጐደለው ከመሆኑ የተነሳ ጥቂት አፍቃሬ ህውሓት /ኢህአዴግ የሆኑ ግለሰቦች በአንድ ጀንበር ሚሊየኒየር ሲያደርግ አጠቃላይ ዜጐችን ደግሞ እያንደረደረ ወደ ድህነትና ድንቁርና የሲኦል አዘቅት ያለርህራሄ ይወረውራቸዋል፣ ከዚህም የተነሳ የመላ ሃገሪቱ አዛዥና ናዛዥ እነርሱ አንተ ደግሞ ሁሉ ነገርህን ተነጥቀህ ጭሰኛ ከሆንክ ሰነባብቷል፡፡
ይህንንም አገዛዝ ለማሰንበት ይቻለው ዘንድ የህወሓት /ኢህአዴግ አምባገነን “መንግሥት” በየጊዜው የሚያወጣቸውና የሚያፀድቃቸው ፌደራላዊም ሆነ ክልላዊ ፖሊሲዎች በሙሉ ለሀገርም ሆነ ለህዝብ ጥቅም ታስቦ ሳይሆን ለህወሓት /ኢህአዴግ የፖለቲካ ትርፍ እንዴት እንደሚያስገኙለት ታሳቢ በማድረግ ብቻ ነው፡፡ ይህ ሀገርንም ሆነ ህዝብን አጥፊ የሆነ ሒደት ተገቶ በአገራችን ኢትዮጵያ ለህዝብ ተጠያቂና ተገዢ፣ የሆነ መንግሥት ተቋቁሞ ዲሞክራሲ፣ መልካም አስተዳደር፣ ፍትሕ፣ ሰላምና ብልፅግና ማስፈን እንዲቻል መኢአድ “የስልጣን ምንጭ ሕዝብ ነውና!” ኑ! አብረን በሰላማዊ ትግል ህወሓት /ኢህአዴግን እናበርክከው እያለ ህዝባዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

የአንድነት ስራ አስፈፃሚ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠራ

የአንድነት ስራ አስፈፃሚ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠራ
**************************************************
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊና የመኢአድ እና የአንድነት የውህደት ጉዳዮች አመቻች ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆነው ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ ሀብታሙ አያሌው ዛሬ ጠዋት በመንግስት የደህንነት ሀይሎች መታገቱን ተከትሎ ፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው በምን ሁኔታ እንደሚገኝ ለማጣራት ያደረገው ሙከራ ባለመሳካቱ ምክንያት ስራ አስፈፃሚውን አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል፡፡ ስራ አስፃሚው ከስብሰባው በኋላ ጠንከር ያለ ፖለቲካዊ አቋም ይይዛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የአንድነት ፓርቲ ወጣት አመራሮችን የመሰር ዘመቻው ቀጥሏል

የአንድነት ፓርቲ ወጣት አመራሮችን የመሰር ዘመቻው ቀጥሏል
------------------------
የአንድነት ፓርቲ ም/የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ ዛሬ ጠዋት ሜክሲኮ አካባቢ በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች ከተያዘ በኋላ በአሁኑ ሰዓት አየርጤና አካባቢ የሚገኘው መኖሪያ ቤቱ እየተበረበረ እንደሆነ ለፍኖተ ነፃነት የደረሰው መረጃ አመልክቷል፡፡

አቶ ሀብታሙ አያሌው ተያዙ፤ እስካሁን ያሉበት ሁኔታም ሆነ ቦታ አልታወቀም

አቶ ሀብታሙ አያሌው ተያዙ፤ እስካሁን ያሉበት ሁኔታም ሆነ ቦታ አልታወቀም
+++++++++++++++++++++++++++++++
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው በዛሬው እለት ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ላይ ወደ ቢሮአቸው በማምራት ላይ እንዳሉ ደንበል አካባቢ የፖሊስ የደንብ ልብስ በለበሱ አካላት መያዛቸውን ከስፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች የገለፁ ስሆን እስካሁን የት አውንዳሉና በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ አልተቻለም፡፡

ቅዳሜ 5 ጁላይ 2014

የተቃዋሚ አባላትን ማሰር ማወከብና ማፈናቀሉ ቀጥሏል

--------------------------------------------------
በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የሚኖሩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አባሎች የሆኑት
- አቶ ሞላ ገረመው
- አቶ ብርሃኑ ገረመው
- አቶ ካሳሁን እንዳለ ከረቡዕ ሰኔ 18 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ የተቃዋሚ አባል
በመሆናቸው ብቻ የሚያርሱትን መሬት ቀምተው አሳርሰውባቸዋል፡፡ ለምን እንቀማለን ዜጎች አይደለንም ወይ ብለው ተቃውሞ
ሲያሰሙ ከፓርቲው ለቃችሁ ካልወጣችሁ መሬታችሁ አይመለስም በማለት የቀበሌው ሊቀመንበር አቶ ፀጋዬ ጎሹ አስፈራርተዋቸዋል፡፡
እንዲሁም በምዕራብ ጎጃም በይልማና ዴንሳ ወረዳ (አዴት) የሚገኙ የመኢአድ አባላት ላይ እስርና አፈና የተፈጸመ ሲሆን አቶ በቃሉ
ደፋሩ የተባሉ የወረዳው አባል ከሳምንት በፊት በፖሊስ ተይዘው እስካሁን ፍ/ቤት አልቀረቡም፡፡
በዚሁ ወረዳ - አቶ አትገኝ እምሬ እንዲሁም
- ቄስ ይሁን ዘለቀ ከሐሙስ ሰኔ 19ቀን 2006ዓ.ም ሌሊት ጀምሮ የደረሱበት አይታወቅም ሲሉ የመኢአድ
የህ/ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል፡፡

የተቃዋሚ አባላትን ማሰር ማወከብና ማፈናቀሉ ቀጥሏል
---------------------------------------------------------------------
በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የሚኖሩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አባሎች የሆኑት
- አቶ ሞላ ገረመው
- አቶ ብርሃኑ ገረመው
- አቶ ካሳሁን እንዳለ ከረቡዕ ሰኔ 18 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ የተቃዋሚ አባል
በመሆናቸው ብቻ የሚያርሱትን መሬት ቀምተው አሳርሰውባቸዋል፡፡ ለምን እንቀማለን ዜጎች አይደለንም ወይ ብለው ተቃውሞ
ሲያሰሙ ከፓርቲው ለቃችሁ ካልወጣችሁ መሬታችሁ አይመለስም በማለት የቀበሌው ሊቀመንበር አቶ ፀጋዬ ጎሹ አስፈራርተዋቸዋል፡፡
እንዲሁም በምዕራብ ጎጃም በይልማና ዴንሳ ወረዳ (አዴት) የሚገኙ የመኢአድ አባላት ላይ እስርና አፈና የተፈጸመ ሲሆን አቶ በቃሉ
ደፋሩ የተባሉ የወረዳው አባል ከሳምንት በፊት በፖሊስ ተይዘው እስካሁን ፍ/ቤት አልቀረቡም፡፡
በዚሁ ወረዳ - አቶ አትገኝ እምሬ እንዲሁም
- ቄስ ይሁን ዘለቀ ከሐሙስ ሰኔ 19ቀን 2006ዓ.ም ሌሊት ጀምሮ የደረሱበት አይታወቅም ሲሉ የመኢአድ
የህ/ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል፡፡

ከመኢአድ/አንድነት የውህደት አመቻች ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ!!!

የኢትዮጵያን ህዝብ የለውጥ ፍላጎት እውን ለማድረግ የመኢአድ እና የአንድነት መዋሀድ ወሳኝ የፖለቲካ ምዕራፍ ነው!!!
*****************************************

የኢትዮጵያን ህዝብ የለውጥ ፋላጎት ዕውን ለማድረግ የተቃዋሚው ጎራ በመሰባሰብ አንድ ግዙፍ አማራጭ ኃይል ወደ መገንባት ሊሸጋገር እንደሚገባ መላው የአገራችን ህዝብ ለረጅም ግዜ ሲያሳስብ መቆየቱ የሚታወቅ ነው፡፡
በዚሁ መሰረትም ትግሉ የሚጠይቀውን የፖለቲካ ተክለ ቁመና ለመያዝ የመላ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የደረሱበትን ወሳኝ የፖለቲካ ምዕራፍ እውን ለማድረግ ከሁለቱም ፓርቲዎች በእኩል ቁጥር የተቀወከሉ አሥር አባላት ያሉት የውህደት አመቻች ኮሚቴ ተቋቁሞ የውህዱን ጉባኤ በስኬት ለማጠናቀቅ በርካታ ተግባራት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የውህደት አመቻች ኮሚቴው ሁለቱ ታርቲዎች በተናጠል የሚያካሂዱት እና በጋራ ውህዱ ፓርቲ የሚያደርገው ጉባኤ በተያዘለት ግዜ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ተግባር በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ የሁለቱ ፓርቲዎች መዋሃድ ከፍተኛ ስጋት የፈጠረበት ገዥው ፓርቲም ሆነ ሌሎች አካላት በውህደቱ ሂደት ላይ ተግዳሮት ለመደቀን በርካታ ጥረት እያደረጉ እንደሆነም አስተውለናል፡፡
ስለሆነም መላው የሀገራችን ህዝብ ጉዳዩን በንቃት እንዲከታተልና ገዥው ፓርቲ ከፍተኛ በጀት በመመደብ ከግሉ ሚድያ ጋር ተመሳስለው አፍራሽ ተልእኮ እንዲፈጽሙ ባደራጃቸው አካላት እና ሚዲያዎች ሁለቱ ፓርቲዎች የህዝብ ጥያቄ ለመመለስ የሚያደርጉትን ጥረት በማጠልሸቱ ተግባር ላይ እንዲሰማሩ እየተደረገ ያለውን ስውር ሴራ በጥንቃቄ ማየት እንደሚገባ ለመጠቆም እንወዳለን፡፡
የሁለቱ ፓርቲዎች መዋቅርም ሆነ ዋነኛ ባለቤት የሆነው የውህደት አመቻች ኮሚቴው መረጃዎችን በጥንቃቄ እንደሚከታተል እና ይፋ እንደሚደረግ እየገለፅን በአጭር ጊዜ ውስጥ ውህደቱን በማጠናቀቅ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ እንደምንሸጋገር ለመላው ህዝባችን እንገልጻለን፡፡ ስለሆነም በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ለውህደቱ መሳካት አስፈላጊውን የፋይናንስ፣ የማቴሪያል፣ የሞራልና የሀሳብ ድጋፍ በማድረግ ሀገራዊ ሃላፊነታችንን በጋራ እንድንወጣ ጥሪ እንቀርባለን፡፡
በ1997 ዓ.ም የታየውን የህዝብ የለውጥ ፋላጎት እና የፖለቲካ ተሳትፎ ዳግም ለመመለስ ሳንታክት እንሰራለን!!!
ከውህደት አመቻች ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
ሰኔ 26 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ