ቅዳሜ 20 ጁን 2015

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ) አመራር እና አባላት ላይ እስራቱ ተባብሶ ቀጥሏል

እስራቱ ተባብሷል
/ ለገሰ ወ/ሃና/
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ) አመራር እና አባላት ላይ እስራቱ ተባብሶ ቀጥሏል
በትላንትናው እለት ማለትም 12/10/2007 ዓም ከምሽቱ 2:30 አካባቢ ልዩ ቦታው ሜክሲኮ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ ) የውጭ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አብርሃም ጌጡ ተይዞ ልደታ ፓሊስ መምሪያ ታስሯል በዛሬው እለት ከፓሊስ መምሪያ ወደ አምስተኛ ተዛውሯል ከአዲስ አበባ ውጭም አባላት እየታሰሩ እንደሆነ መረጃ ደርሶኛል የተጠናከረ መረጃ ሲደርሰኝ እመለስበታለሁ አሁን ወደተረጋገጠው ጉዳይ
አቶ አብርሃም ጌጡ ትግል የጀመረው ገና በለጋ እድሜው በ1989 ዓም ነው መኢአድ ካፈራቸው ምርጥ ታጋዮች ግንባር ቀደሙ ነው ከመአሕድ ጀምሮ በተለያዩ የሀላፊነት ቦታ ላይ የጎላ አስተዋጽኦ አበርክቷል በተለይ ከ2001 አስከ 2003 ዓም ሀገራቀፍ የወጣቶች ጉዳይ ሀላፊ ሆኖ በርካታ ወጣቶችን በማደራጀትና በሠላማዊ ትግል ላይ ስልጠና በመስጠት ብዙ ወጣቶችን አብቅቷል በ2002 ሀገራቀፍ ምርጫ በልደታ ክ/ከተማ ለተወካዮች ምክር ቤት ተወዳድሮ ነበር ምርጫው ነጻና ዲሞክራሲያዊ ቢሆን ኖሮ ባለው የህዝብ ፍቅርና መልካም ስነ ምግባሩ የህዝብ እንደራሴ መሆን ይችል ነበር
መኢአድ ታህሳስ 17 - 19 /2003 ዓም ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ድርጅት ጉዳይ ሀላፊ ሆኖ ተመርጦ ነበር በጠቅላላ ጉባኤው ማግስት በወቅቱ መኢአድን በፕሬዝደንትነት የሚመሩት ኢንጂነር ሀይሉ በወሰዱት የተሳሳተ እርምጃ ምክንያት የተመረጠውን አመራር በማገድ እና በመክሰስ ከፅ/ቤት እንድንወጣ ሲደረግ ከተከሰሱት አመራሮች አንዱ ነበር ኢንጂነር ሀይሉ እየሄዱበት የነበረውን የተሳሳተ መንገድ እንዲተው ፊት ለፊት የሞገተ ቆራጥ ታጋይ ነው ሠሚ አጣ እንጂ
ከ2003 ዓም እስከ ጥቅምት 28 -30 2007 ዓም ጠቅላላ ጉባኤ ድረስ በህገወጥ መንገድ ከፅ/ቤት የወጣውን አባልና አመራር በአላማው አፀንቶ ለአሸናፊነት ያበቃው ዋናው ሰው አብርሃም ነው አብርሃም ልታይ ልታይ ማለት አይወድም የፓርቲ መሪ ከመሆን ይልቅ መሪ ሊሆኑ የሚችሉ ሰዎች ማብቃት ላይ ያተኩራል ከአብዛኛው የመኢአድ አመራር የሚልቅበት የወጣለት ዲፕሎማት መሆኑ ነው እጅግ አስተዋይ እና በሰላማው ትግል ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በፅኑ የሚያምን ነው
ጥቅምት 28-30 በተደረገውጠቅላላ ጉባኤ መኢአድን ለመምራት ታጭቶ በአቶ ማሙሸት አማረ በጥቂት ድምፅ ተበልጦ የመኢአድ ፕሬዝደንት መሆን ባይችልም በአቶ ማሙሸት ካቢኔ ውስጥ ባለው ጠንካራ የዲፕሎማሲ ችሎታ እና በፓለቲካል ሳይንስና አለማቀፍ ግንኙነት የማስትሬት ድግሪ ያለው በመሆኑ የመኢአድ የውጭ ግንኙነት ሀላፊ ሆኖ ቢሰራ ትልቅ ስራ እንደሚሰራ በመታመኑ ሀላፊነቱ ተሰጥቶት በአጭር ጊዜ አስደናቂ ሥራ ሰርቷል
አንባገነኑ መንግስት በምርጫ ቦርድ በኩል በወሰደው እርምጃ የነ አብርሃም ጌጡ አመራር ከፅ /ቤት በፌደራል ፓሊስ እንዲወጣ ተደረገ እንጂ
በደረሱብን በርካታ ችግሮች ሳይደናገጥ መፍትሄ መሻትን የሚመርጠው ፍፁም መደናገጥ ውስጥ የማይገባው አብርሃም መውጫ ቀዳዳ የሌለው የሚመስለን ነገር በጥልቀት ካሰብን መውጫ አለው ይላል አብርሀም ምርጫ ቦርድ በአዋጅ ከተሰጠው ስልጣን ውጭ ድርጅታችንን በጠራራ ፀሀይ ተነጥቀን ዝም አንልም በማለት ከፕሬዝደንቱ ከአቶ ማሙሸት አማረ ጋር በመሆን ጉዳዩን ወደ ህግ በመውሰድ ምርጫ ቦርድን በመሞገት ትልቅ ስራ በመስራት ላይ እያለ ነው ተይዞ ለእስር የተዳረገው
ቀጣይ ክፍል ጊዜ ሲገኝ አመለስበታለሁ፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ