“እንዳልወልድ የዘር ፍሬዬ ተኮላሽቷል” መቶ አለቃ ጌታቸው
አንበሳው ያንበሳ ዘር የመኢአዱ ጀግና መቶ አለቃ ጌታቸው መኮነን እና ተስፋየ ታሪኩ ሌሎች 16 የመኢአድ የቁርጥቀን ልጆች ልደታ ፍርድቤት 19ኛው የወንጀል ችሎት ቀረቡ
ግንቦት 28 ቀን 2007
መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የደረሰበትን አስከፊ ወንጀል ለዳኛው ቢያቀርብም ተቀባይነት አላገኘም። አቶ ተስፋየ ታሪኩ እሱም እየተፈፀመበት ያለውን ግፍ ለመናገር ቢያስፈቅድም፣ ያቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት የለውም በማለት ዳኛው አስቁመዉታል። ዳኛው “የናንተ ጉዳይ ወደ እኛ ከመጣ በኋላ የተፈፀመውን ለማስተካከል እንሞክራለን። ማእከላዊ በነበራችሁበት ወቅት የተፈፀመውን የማየት ስልጣን የለንም” ብለዋል።
በመቶ አለቃ ጌታቸው ላይ የተፈፀመው ወንጀል እግሩን በመስበር “አማራን ማጥፋት አለብን” በማለት የዘር ፍሬውን በማኮላሸት እራሱን እንዳይተካ (እናዳይወልድ) ተደርጓል። ሕክምናም እንዳያገኝ ተደርጓል።
አቶ ተስፋየ ታሬኩ “ፍርድ ቤቱ ያቀረብነው አቤቱታ የማይሰማ ከሆነ፣ ምንም ጠበቃ አያስፈልገንም። ለፀረ ሺብር ህጉም ሆነ ለዚህ ፍርድ ቤት እውቅና አንሰጥም። ያሰረንም ያሳሰረንም የደበደበንም የሚያስደበድብንም የሚመሰክርብንም የሚያስመሰክርብንም የሚፈርድብንም ወያኔ ነው። እኛ ለግንቦት 7 እና ለአርበኞች ግንባር ያደረግነው ነገር የለም። እነሱም የሳላማዊ ትግሉ ሲዘጋ ነው ወደትግል የገቡት” ብለዋል።
ሁሉም የመኢአድ አመራሮች እና አባሎች 16ቱም የተከሰሱበት ክስ ግንቦት 7 አርበኞች ግንባር እና ያማራ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ አባሎች ናችሁ የሚል ነው።
ቀጠሮ ለሐምሌ 1 ተወስኖአል።
ቀጠሮ ለሐምሌ 1 ተወስኖአል።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ