ዓርብ 18 ዲሴምበር 2015

የኦሮሞ ህዝብ ብሶት፥ ወደ የጋራ ነጻነት

የኦሮሞ ህዝብ ብሶት፥ ወደ የጋራ ነጻነት


“ከአዲስ አበባዉ የእርሻ መሬት እስከ አሜሪካዊ ቤተ መንግስት፥መብትን የማስከበር ጣምራ ሒደት!”
በአሜሪካዉ ቤተ መንግስት እና በዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የኢትዮጵያ መንግስት በሰላማዊ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ የሚያደርገዉን ግድያ፣ድብደባ፣ እስር፣ወከባና ማፈናቀልን በመቃወም በተደረገዉ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በመገኘት ሳዲቅ አህመድ ያዘጋጀዉ ልዩ ፕሮግራም።

Washington DC protest against the killing of Oromo students

ረቡዕ 11 ኖቬምበር 2015

ረሃቡና እድገታችን፡ ተጠያቂው ማን ነው? (በአብዱረዛቅ ሑሴን)

ክፍል አንድ፡ እድገቱን የጎሪጥ!
ምስራቅ አፍሪካ ላይ በዚህ አመት 22 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች በረሃብ እንደሚጠቁና ከዚያም ውስጥ 68% (15 ሚሊየኑ) ከኢትዮጵያ እንደሚሆን የተባበሩት መንግስታት እየተናገረ ይገኛል፡፡ መጀመሪያ ምንም አይነት ስጋት እንደሌለ፣ ከዚያም 4 ሚሊየን ቆየት ብሎ ደግሞ 8 ሚሊየን ህዝብ ተጠቂ እንደሆነ ዘግይተው ላመኑት ሹማምንቶቻችን ከፍተኛ ዱብ እዳ እንደሚሆንባቸው አያጠያይቅም፡፡ የሀገርም ውስጥ ይሆን አለም አቀፉ ህብረተሰብ አንድ ተመሳሳይ ጥያቄ እንደሚጠይቅ ይጠበቃል፡- ‪ላለፉት‬ አስር አመታት በሁለት ዲጅት ያደገ ኢኮኖሚ እንዴት የህዝቡ 15% በረገብ ሊጠቃ ቻለ?15 million people in need of food aid
ለዚህ ጥያቄ የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትራችን ያላቸውን የኢኮኖሚክስ እውቀት ተጠቅመው ቢያንስ መልስ ሚመስል ነገር ይሰጡን እንደነበረ እርግጠኛ መሆን ይቻላል፡፡ እሳቸው ከነጎዱ ወዲህ ግን ‪‎ወይ‬ አያውቁ፣ ወይ የሚያውቁትን አያመጡ፣ ወይ አይወጡ; ሆኖብን እንጨት እንጨት የሚል የወረዱ ትንታኔዎቻችን የሚሰጡን ከጠቅላይ ሚንስተሩ እስከ ኮሚኒኬሽን ሚንስትሮቻቸው ድረስ ያሉ ባለስልጣናት ግራ አጋብተውናል፡፡ የዋጋ ግሽበት ፣የኑሮ ውድነቶችን እና የመሰረታዊ አገልግሎት አቅርቦት እጥረትን የመሳሰሉ ችግሮች ሲነሱ አቶ መለስ በተደጋጋሚ የእድገታችን ውጤት እንደሆነ ለኛም ለተተኪዎቻቸውም ሲነግሩን ነበር፡፡ ይህ ምላሽ መንግስትን ከተጠያቂነት ባያስመልጥም በከፊልም ቢሆን ኢኮኖሚክሲያዊ መሰረት ያለው ምሁራዊ ትንተና ሊባል የሚችል ነው፡፡ ከሳቸው መሞት በኋላ የመጡ መሪዎቻችን ለተመሳሳይ ጥያቄዎች ተመሳሳይ መልስን ሲሰጡን ቆይተዋል፡፡ ራእያቸውንም ብቻ ሳይሆን ለጥያቄዎች የሰጡትንም መልሶቻቸውን እያስቀጠሉም ይገኛሉ፡፡ ረሃብ ሀገራችንን ተለይቷት ባያውቅም በዚህ መጠን ግን የሁለት ዲጅት እድገት ትርክት ከተጀመረ ወዲህ ስላልተከሰተ የቀድሞውም ጠቅላይ ሚንስትር አልተጠየቁምም ለወራሾቻቸውም መልሱን አላስቀመጡም፡፡ በተወሰኑ አጋጣሚዎች ወደ ሚዲያ ብቅ ያሉትም ባለስልጣናት ችግሩን ከመካድ፣ መጠኑን ከማስተባበልም አልፎ የወረዱ ምክንያቶችን ሲደረድሩ ታዝበናቸዋል፡፡ መልሽ ያጣውን ጥያቄ ዛሬ በከፊልም ቢሆን ለመመለስ እንሞክር፡፡
ረሃብ! ድሮና ዘንድሮ
የሰባ ሰባቱ ድርቅና ረሃብ ሀገራችንን አለም ፊት አንገት ያስደፋ አሳዛኝ ክስተት ነበር፡፡ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተከሰተው ድርቅ ከፍተኛ የሆነን ረሃብና እልቂት አስከትሎ ነበር፡፡ ዶክተር እሌኒን የመሰሉ ምሁራን እንደሚሞግቱት በወቅቱ የሰሜኑ ክፍል በድርቅ ቢጠቃም በሌላው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ግን በቂ ምርት እንደነበረ ይገልፃሉ፡፡ ሀገሪቱ በዛ ወቅት ምርት ከተትረፈረፈበት ደቡብ እጥረት ወደተከሰተበት ሰሜን እንዲሄድ የሚያስችል በቂ የኢንፍራስትራክቸርና በተለይም የገበያ ተቅዋም አለመኖሩን ለችግሩ መባባስ እንደ ዋና ምክንያትም ያቀርባሉ፡፡ በሌላ አባባል በቂ የኢንፍራስትራክቸር ዝርጋታ ኖሮ በነበረና ምርትን ከፍላጎት ጋር ለማገናኘት የሚያስችል የገበያ መረብ ኖሮ በነበረ ድርቁ ያስከተለውን እልቂት መቀነስ ይቻል ነበር፡፡ ይህ ምልከታም በዶክተር እሌኒ መሪነት የተቋቋመውን የEthiopia Commodity Exchangeን ለመመስረት እንደ ዋነኛ መከራከሪያ ሆኖ በተለያዩ የጥናት ፅሁፎቻቸው ውስጥ ተካቶ እናየዋለን፡፡
አስከፊው የሰባ ሰባቱ እልቂት ከተከሰተ ከሰላሳ አመት በኋላም ይኸው ድርቅ አገሪቱን እያሳሰበ ይገኛል፡፡ እነ ዶክተር እሌኒ የሞገቱለት የኢንፍራስትራክቸርና የገበያ ተቋማት አለመኖር በፊት ከነበረው በእጅጉ የተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጥርጥር የለውም፡፡ የመንገዶችም ሆነ የኮሚኒኬሽን ኢንፍራስትራችቸሩ ከድሮው ጋር ሊወዳደር በማይችል መልኩ አድጓል፡፡ በሀገሪቱ በየትኛውም ቦታ የአቅርቦት እጥረት እናዳለና ተመጣጣኝ ትርፍ ሊገኝ እንደሚችል የሚያውቅ ነጋዴ ወሬውን ሰምቶ ተኝቶ ያድራል ብሎ ማሰብ ይከብዳል፡፡ ወሬውን ለመስማት የሚያስችለው የኮሚኒኬሽን ኢንፍራስትራችቸርም ይሁን ምርቱን እጥረት ወደ አለበት ቦታ ወስዶ ለማትረፍ የሚያስችለው የትራስፖርት አማራጮች በብዙ እጥፍ ተሻሽለውለታል፡፡ ይህ ባለበት ሁኔታ ረሃቡ በድጋሚ መከሰቱ እነ ዶክተር እሌኒ የዘነጉት ወይም ትኩረት ያልሰጡት ሌላ ተጨማሪ የረሃብ መንስኤ እንዳለ ያሳየናል፡፡ ይህም የህዝብ ወይም የመንግስት የመግዛት አቅምን ይመለከታል፡፡
ነጋዴው ያማሩ መንገዶችን ተጠቅሞ ትርፍ ምርት ካለበት ወደ እጥረት ወደተከሰተበት የሀገሪቱ ክፍል ምርቱን ቢያቀርብ ለረሃቡ መፍትሄ ሊሆን አይችልም፡፡ በችግሩ የተጠቃው የህብረተሰብ ክፍል የምርት አቅርቦት ብቻም ሳይሆን የመግዛት አቅሙም ሊኖረው ይገባል፡፡ ምርቱ በድርቅ የረገፈበት ገበሬ በደህናው ጊዜ ተቀማጭ ሀብት እስካላፈራ ድረስ የምርት አቅርቦትን ማሻሻልና ማቀላጠፍ ብቻ በራሱ ችግሩን አይፈታውም፡፡ ኑሮው ከእጅ ወደ አፍ ስለሆነና የመግዛት አቅሙም ስለማይኖረው ከመንግስት እርዳታን መከጀል ብቸኛ ምርጫው ይሆናል፡፡ መንግስት ፈርጣማ አቅሙን በመጠቀም ትርፍ ምርት ካለባቸው አካባቢዎችም ካልሆነም የውጭ ሀገራት ገዝቶ ተጠቂውን ህዝብ የመድረስ ግዴታ ይወድቅበታል፡፡ አሁን እንደሚታየው ከሆነ ግን ገበሬውም ለነገዬ ብሉ ያስቀመጠው ቅሪት ሳይኖረው በረሃብ አለንጋ እየተጠበሰ፤ መንግስትም ሲፎክርበት የነበረው ፈርጣማ አቅሙ በሞት አፋፍ ላይ ላሉት 15% ህዝቡ የቁርጥ ቀን ደራሽ መሆን ያዳገተው ይመስላል፡፡ ላለፉት አስርት አመታት ተኣምራዊ እድገትን ስታድግ የነበረችው ኢትዮጵያ፤‪‎ግብርናን‬ መሰረት ያደረገ; የእድገት ስትራቴጂ እየተከተለች እንዳለች የምትነግረን ኢትዮጵያ፤ ገበሬዋ እራሱን መመገብ ሲያቅተውና መንግስቷም የክፉ ቀን ደራሽ መሆን ሲሳነው እድገቱን የጎሪጥ ብናየው ይፈረድብን ይሆን?

ቅዳሜ 7 ኖቬምበር 2015

ድል ለመቀዳጀት በአንድ ማሊያ መጫወት (ይገረም ዓለሙ)

ይገረም ዓለሙ

የላቀ የኳሽ ችሎታ ያላቸው ተጨዋቾች በሀገራቸውም ሆነ ከሀገራቸው ውጪ በከፍተኛ ገንዘብ እየተሸጡ ይጫወታሉ፡፡ እነዚህ ዘር፣ቀለም ፤ኃይማኖትም ሆነ ቋንቋ ሳይገድባቸው በችሎታቸው ተመርጠው በየትኛውም የአለም ክፍል የሚጫወቱ ተጨዋቾች ገንዘብ የሚከፍላቸውን ቡድን የዋንጫ ባለድል ለማድረግ ለራሳቸውም ተዋቂነት ለማትረፍ በቁርጠኝነት ይጫወታሉ፡፡ የአንድ ሀገር ልጆች የተለያየ ማሊያ ለብሰው ለተለያዩ ቡድኖች ተሰልፈው ሲጫወቱ የተሰለፉለትን ቡድን ለአሸናፊነት ለማብቃት ይሻኮታሉ ይጎሻሸማሉ፡
አህጉራዊ ወይንም ዓለም አቀፋዊ ጨዋታ ሲኖር ግን ከየሄዱበት ተመልሰው ከተበታተኑበት ተሰባስበው በአንድ ማሊያ ለሀገራቸው ይሰለፋሉ፡፡ ለሀገራቸው ቡድን የመሰለፍ ምክንያታቸው በአሰልጣኙ መመረጣቸውና ሀገራቸው ችሎታቸውን መፈለጉ ብቻ ሳይሆን የእነርሱም ሀገራቸው አሸንፎ ባለ ድል አንዲሆን ከምር መፈለጋቸው ጭምር ነው፡፡ ባለፈው የዓለም ዋንጫ የእግር ኳስ ውድድር ላይ ከአሸናፊነት ክብር ብር በልጦባቸው ከሀገራቸው አልፎ አፍሪቃን መሳቂያ ያደረጉትን ተጨዋቾች ሳንጨምር ነው ታዲያ፡፡
በዚህ ተምሳሌት የሀገራችንን ፖለቲካ ብንመለከተው ወያኔ በዚህ መንገድ በሚገባ እየተጠቀመበት መሆኑን እናያለን፡፡ ተቀዋሚው ግን….. ፡፡ ወያኔ አባል አጋር ሌላም በውል ስም ያልወጣላቸው ቡድኖችን አቋቁሞ በተለያየ ማሊያ የክልል ጨዋታውን ያካሄዳል፤ አምስት ዓመት ጠብቆ ሀገራዊው ጨዋታ ሲካሄድ ደግሞ ሁሉንም በአንድ ማሊያ በኢህአዴግ ስም ያሰልፋል፡፡
ወያኔ ማሊያ እየቀያየረ መጫወት የጀመረው በህውኃት ማሊያ ወደ ጎነደርና ወሎ መሸጋገር እንደማይቻል በተረዳበት ግዜ ነው፡፡እናም የአማራ ክልል የሚል ስያሜ በሰጠው የኢትዮጵያ ክፍል ለመረማመድ እንዲቻለው ኢህዴን ይባል የነበረውን ሕብረ- ብሔራዊ ድርጅት ስሙንም ዓላማውን አስለውጦ ብአዴን በሚል መጠሪያ የአማራነት ማሊያ አለበሰው፡፡ወያኔ ይህን ሲያደርግ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ነው የመታው፡፡ አንዱ በአማራ ክልል ለመረማመድ የሚያስችለው ቡድን መፍጠር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የማይፈልገውንና ለእቅዱ አንቅፋት አድርጎ የሚያየውን ሕብረ ብሄር ፓርቲ ማክሰም፤ ሀገራዊ አስተሳሰብን ማጥፋትና ዘረኝነትን ማስፋፋት ነው፡፡ ወደ ሸዋ ሲጠጋ ደግሞ እሱም ጋር ሻዕቢያም ዘንድ የነበሩ ኦሮምኛ ተናጋሪ ምርኮኞችን ሰብስቦ በኦሮምያ ውስጥ ለመረማመድ የሚያስችለውን የኦሮሚያ ማሊያ ለብሶ የሚጫወት ቡድን ( ኦህዴድን) ፈጠረ፡፡አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ደግሞ የሱን ሥልጣን የሚያረጋጉና የሚያስጠብቁ ደኢህዴንና እና አጋር የሚባሉትን ቡድኖችን መፍጠሩን ሁሉም የሚያውቀው ነው፡፡
እነዚህ የተለያያ ማሊያ ለብሰው የተለያየ ቡድን ተመስለው የሚጫወቱ ቡድኖች የቡድን መሪያቸው አሰልጣኛቸው አስተዳዳሪያቸው ህወኃውት መሆኑን አሌ የሚል አይኖርም፡፡እናም ለዘወትሩ ጨዋታ በክልል ማሊያ እያሰለፈ በየአምስት ዓመት ለሚካሄደው ጨዋታ ደግሞ የኢህአዴግን ማሊያ እያሰለፈ ሀያ አራት አመት ሙሉ የዋንጫው ባለቤት እንደሆነ አለ፡፡
ይህን ጨዋታ ቅንጅትም ሞክሮት ውጤታማነቱን አሳይቷል፤ምርጫ 97 በአጃቢነት የምንገባበት፣ ለአድማቂነት የምንሰለፍበት ሳይሆን ከምር ተወዳድረን የምናሸንፍበት መሆን አለበት ያሉ ወገኖች ለማሸነፍ ደግሞ በተለያየ ስም ሆኖ የተለያያ ማሊያ ለብሶ ሳይሆን በአንድ ቡድን መደራጀት በአንድ ማሊያ መሰለፍ እንደሚስፈልግ ተናገሩ-ሰሩ፡፡ በዚህ ጥረትም አደረጃጀታው ሀገራዊ መገኛቸው ሀገር ቤት የሆኑ አራት ድርጅቶች ስማቸውን ቅንጅት ብለው ምልክታቸውን ሁለት ጣት አድርገው በአንድ ማሊያ ተሰልፈው መጫወት በመቻላቸው መቼም የማይረሳውንና መቼ ሊደገም እንደሚችል መተንበይ የማይቻለውን ውጤት አስገኙ፡፡
ይህ ከሆነ በኋላ ሁለት ምርጫዎች ተደርገው ተቀዋሚው እንደለመደው ጨዋታውን በተለያየ ማሊያ ማድረጉን በመቀጠሉ በአንዱ አንድ ወንበር ሲያገኝ በሁለተኛው ፓርላማውን ጨርሶ አስረክቧል፡፡ ሀገራዊ ውድድርን በአሸናፊነት ለመወጣት ካልሆነም ትንሽ ወንር ከፓርላማ ለማግኘት አንድ ቡድን መስርቶ በአንድ ማሊያ መጫወት ያለውን ጠቀሜታ ከወያኔ መማር ባይቻል ወይንም ባይፈለግ እንደምን ከቅንጅት መማር ይቸግራል፡፡
ለውጤታማነት በአንድ ማሊያ መጫወት የሚያስፈልገውና የሚጠቅመው በሀገር ቤት ለሚደረገው ትግል ብቻ አይደለም፡፡የትግሉ መነሻ ቦታ ኢትዮጵያም ይሁን አሜሪካ፣ ኤርትራም ይሁን በርበራ፣አሰብም ይሁን ሱዳን በሁሉም የሚፈለገው ውጤት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ማየት ከሆነ በአንድ ቡድን ተሰባስቦ አንድ ማሊያ ለብሶ አንድ ሀገራዊ ገዢ መርህ አንግቦ መጫወት የግድ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ ውጪ እስካሁን በተመጣበት ሁኔታ የሚካሄድ ውድድር(ትግል) ይህን ያህል ቡድን እዛና እዚህ አለ ከመባል ባለፈ ብሎም አንድ ቡድን ብቻውን ለጨዋታ ሜዳ አይገባምና የወያኔ አጨዋች ከመሆን የዘለለ የሚፈይደው ነገር የለም፣ አለ ከተባለ እገሌ የዚህ ቡድን መሪ እገሌ የዛኛው ቡድን ሊቀመንበር እየተባሉ መኖርን ትግልም ድልም ላደረጉ ሰዎች የሥልጣን ጥም ርካታ ማስገኘቱ ብቻ ነው፡፡ የፓርቲ መሪነት ሥልጣን ሆኖ፡፡
ሀያ አራት አመት እጅግ ብዙ ነው፡፡ስለሆነም ከዚህ በኋላ ሊመረን ይገባል፡፡በርግጥ ለውጥን ዓላማቸው አድርገው ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሥረታ ከልብ አምነው ለዚህም ከምር ቆርጠው ለመታገል የወሰኑትና የፓርቲ ሊቀመንበር እየተባሉ መኖርን መነሻ ዓላማቸው መድረሻ ግባቸውም አድርገው የሚኖሩት ይለዩ፡፡ አንድ ቡድን መስርቶ በአንድ ማሊያ ተወዳደሮ የዋንጫ ባለቤት ላለመሆን ምክንያት ተደርጎ የሚቀርበው ቡድኖች ያላቸው የአደረጃጀት ፣ የጨዋት ስልት ፣የሚገኙበት ቦታ ወዘተ ልዩነት አሳማኝ አይደለም፡፡ ዋናው ምክንያት ሀገራዊ ለውጥ እንዲመጣ ያለመፈለግ ወይንም ቁርጠኝት ማጣት ነው፡፡ ለለውጥ በቁርጠኝነት የተሰለፈ ለለውጥ እንቅፋት ለሆኑ ችግሮች መፍትሄ ይፈልጋል እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ሰበቦችን ያስወግዳል እንጂ ልዩነትን ለማስፋት ሲማስን አያድርም፣በእያንዳንዱ ርምጃ ሰበብ እየፈለገ እንቅፋት አይፈጥርም፣ስለ ሀገራዊው ድል እንጂ ስለ እርሱ ቦታ አይጨነቅም፡፡
አንድ በግልጽ የሚታይ ነገር ላንሳ ጀነራል ከማል ገልቹና ጀነራል ሀይሉ ጎንፋ ሁለቱም ከወያኔ ከድተው አስመራ የገቡ የኦሮሞ ተወላጆች ናቸው፡፡እዛ ደርሰው ግን በአንድ ቡድን ተሰልፈው አንድ ማሊያ (ኢትዮጵያዊ ቢቀር ኦሮሚያዊ)ለብሰው መጫወት ተስኖአቸው ተለያይተው በኦሮሞ ስም የተለያየ ቡድን መስርተው እንደሚገኙ ነው የሚሰማው፡፡ ለያዙት ማእረግ የበቁት ውትድርናውን መቼ ጀምረውት እንደሆነ ማስረጃ ባይኖረኝም እዚህ ማዕረግ እስኪደርሱ በቃልም በተግባርም፤ በክፍልም በመስክም ወዘተ ሰፊ ወታደራዊ እውቀት እንደቀሰሙና ልምድ እንዳካበቱ እሙን ነው፡፡ ታዲያ በዚህ ወቅት ከሀገር ቤት ብቻ አይደለም ከአውሮፓና አሜሪካ ጭምር ከፕሮፌሰር እስከ ጳጳስ ከምር ቆርጠው ትግሉ ቦታ ሲወርዱ ጀነራሎቹ አሥመራ ተቀምጠው እንኳን ከሌላው መተባበር ርስ በርሳቸውም መነጋገር አቁመው አመታት መቁጠራቸውን መስማት እንቆቅልሽ አይሆንም!
ከምር ራሳቸውን ለትግሉ የሰጡና ለሥልጣን ሳይሆን ለነጻነት የሚታገሉ ስራቸው ምስክር ነውና በተግባራቸው እንለያቸው በምንችለውም አንደግፋቸው ይጠናከሩ፡ከውጤት አልባው የአመታት ጉዞአቸው ተምረው ለመለወጥ ያልፈቀዱትና ትግሉን ለስማቸው መጠሪያ ብቻ አድርገውት የሚኖሩት እንደዚሁ በተግባራቸው ይለዩ ፡፡ የእነዚህ መኖር ለሀገራዊው ትግል ከሚጠቅም ይልቅ ጉዳት ናቸውና ድጋፍ እንነሳቸው፤ከመኖራችሁ አለመኖራችሁ ይሻላል ብለን በግልጽ እንንገራቸው፡፡
ለነገሩ ሀገር ውስጥ ያሉት ብዙዎቹ ፓርቲዎች በወያኔ ዘንድ ነው እንጂ አሉ የሚባሉት ቆሞ ያልጠቀመ ሞቶ ምን ሊጎዳ ብሎ ሕዝቡ ከሸኛቸው አመታት ተቆጥረዋል፡፡ በውጪም በሚገኙት ላይ ይሄው መደገም አለበት፡፡ ሀገራዊውን ጨዋታ በአሸናፊነት ለመወጣት በአንድ ማሊያ መጫወት በምንልበት በዚህ ሰዐት እንወክለዋለን በሚሉት የአንድ አካባቢ ሕዝብ ስም የተደራጁ ሁለትም ስድስትም ድርጅቶች ስም እንሰማለን፡፡ የድርጅቶቹ መስራቾች ሁሉም ሊቀመንበር መባል በመፈለጋቸው ነው፡፡ ብዙም አባል አንደሌላቸው ይታወቃል፤ደጋፊው ግን ምን ይባላል፡፡ ትግሉን ከምር ያዙት አለያም ተዉት ማለት አያስፈልግም ትላላችሁ፡፡
በመጨረሻም ሎሬትን እንጋራ
Loret Tsegaye Gabre-Medhin

የፓርላማው ድራማ (ይገረም ዓለሙ)

ይገረም ዓለሙ
ሙሉ በሙሉ በአብዮታዊ ዴሞክራቶች በመያዙ የተለየ ሀሳብ የማይሰማበት ሙት የሆነውን ፓርላማ ህይወት ያለው ለማስመሰል የተዘጋጀው ድራማ ማክሰኞ ጥቅምት 16/2008 መታየት ጀምሯል፡፡ ይህ የፓርላማ ድራማ ቤቴሌቭዥን እንደምናያቸው ድራማዎች ሰሞነኛውን ትኩሳት እየተከተለ በየሳምንቱ የሚጻፍና የሚዘጋጅ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በዚህ የመጀመሪያ ቀን ትዕይንት መሪ ተዋናይ ሆነው የቀረቡት ጠቅላይ ምኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ከፓርላማው አባላት መካከል በተመረጡት ተዋንያን እየተጠየቁ በመመለስ ሲተውኑ ታይተዋል፡፡Hailemariam Desalegn in the TPLF parliament
ከቀደሙት ጠቅላይ ምኒስትር ጀምሮ ሲነገር እንጂ ሲተገበር የማይታየው ከተቀዋሚዎች ጋር አብሮ የመስራት ጉዳይ ለመጀመሪያው ቀን ድራማ ማድመቂያነት ከተመረጡት ጉዳዮች አንዱ ነበር፡፡ ተባብሮ መስራት ማለት እንደ ተቀዋሚዎች በመሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመነጋገር ሀገራዊ መግባባት ከመፍጠር የሚጀምር እንደ ወያኔ ደግሞ እሱ በሚፈልገው ጉዳይ ሲፈልጋቸው ብቻ በመጥራት የሚገለጽ ነው፡፡ እንዲ ሆነናም በአምስት ዓመቱ ዕቅድ ላይ ለማወያየት ምርጫ ቦርድ መዝግቦ ለሚያውቃቸው ፓርቲዎች በሙሉ መንግጨሥታቸው ሰነድና ደብዳቤ መላኩን የገለጹት አቶ ኃይለማሪያም ብዙዎቹ በስብሰባው ላይ ሲገኙ ጥቂቶች ውኃ የማይቋጥር ምክንያት በመስጠት አልተገኙም አሉ፡፡ ያልተገኙት ፓርቲዎች ያቀረቡት ምክንያት ውኃ የማይቋጥር ነው ያሉበትን ምክንያትም ሲያረዱ በሕጋዊ መንግድ የተመረጠ መንግሥት ስላልሆነ ከእርሱ ጋር አንነጋርም ማለታቸው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ለመሆኑ ጥሪያችንን ተቀብለው ብዙዎቹ ተገኝተዋል የተባሉት ፓርቲዎች የትኞቹና እነማን ናቸው፡፡ዝቅ ብለን እናያቸዋለን፡፡
የመሳሪያ ትግል የሚያካሂዱትን ድርጅቶች አስመልክቶም ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ለራሱም መሆን ካልቻለው ሻዕቢያ ጋር ሆነው የሚያመጡት ውጤት ስለማይኖር ጊዜያቸውን በከንቱ ባያባክኑ በማለት ምክር ለመስጠት የዳዳቸው አቶ ኃይለማሪያም አንዳንዶቹ እኮ ጭራሽ የሌሉ ናቸው በማለት ኦነግን ኦብነግንና የጋምቤላ ህዝቦች ንቅናቄን ጠቀሱ፡፡ ይቺ ገለጻ የቀረበችው በደራሲውና አዘጋጁ ስህተት ይሁን ወይንም በርሳቸው የጥናት ጉደለት ባይታወቅም ሁለት መልእክት ታስተላልፋለች፡፡ አንደኛ እነዚህ የተጠቀሱት ድርጅቶች ሰሞኑን ተባብረው ለመስራት የደረሱበት ስምምነት እነ አቶ ኃይለማያም ሰፈር የፈጠረው ነገር መኖሩን እንድንጠረጥር ያሚያደርግ ፣ ሁለተኛ ደግሞ በሰሜን በኩል ድምጻቸው የሚሰማው ድርጅቶች እነዚህ ብቻ አይደሉምና ለሌሎቹ መኖሮና ጠንካራ መሆን በዘወርዋራ እውቅና የሰጠ ነው፡፡
አቶ ኃይለማሪያም የአቶ መለስ ሌጋስ አስቀጣይ እንደመሆናቸው ስለ ድርጅቶቹ የተናገሩት ከርሳቸው የወሰዱትን ነው፡፡ አቶ መለስ ብረት አንስተው መንግሥታቸውን የሚታገሉ ድርጅቶችን አስመልክቶ ሲላቸው አጥፍተናቸዋል የሉም ሲሉ ሌላ ግዜ ደግሞ በግላቸው ብዙ ርቀት ሄደው ከድርጅቶቹ መሪዎች ጋር ለመገናኘትና ለመደራደር እንደጣሩ ሲናገሩ ሰምተናል፡፡ ሌላ ግዜ ደግሞ ወድመዋል ተደምስሰዋል የተባሉት ደርጅቶች በዚህ ቦታ እንዲህ አደረጉ ጥፋት አደረሱ የሚል ዜና ስንሰማ ኖረናል፡፡ የሉም በተባሉ ድርጅቶች ስምም ዜጎች እየተወነጀሉ ታስረዋል እየታሰሩም ነው፡፡ አቶ መለስ አይደለም የሀገር ውስጥ ተፋላሚዎችን ሶማሌ ተሻግረው አልሻባብን ድምጥማጡን አጥፍተነዋል ብለውንም ነበር፡፡
አቶ ኃይለማሪያም ባያስታውሱም እኛ አንረሳውም፡፡ አቶ መለስ ከርሳቸው ፍላጎት ውጪ ስንዝር መሄድ የማይችለውን ፓርላማ አስፍቅደው(ነግረው) እንዲህ አስታዋሽ አጥቶ የቀረውን ሰራዊት ሶማሊያ በላኩበት ወቅት የገጠማቸውን ተቃውሞ ዝም ለማሰኘት ሰራዊታችን አልሻባብን ደምስሶ አሁን የቀረው ቃርሚያ ብቻ ነው፣ ያንን አጠናቆ በቅርብ ቀን ይመለሳል ብለውን ነበር፡፡ ነገር ግን ይኸው እስካሁን አልሻባብም አልጠፋ ሰራዊቱም አልተመለሰ፡፡ እንደውም በተቃራኒው ወንድሞቻችን የአልሻባብ ጥቃት ሰለባ እየሆኑ ነው፡፡ አቶ ኃለማሪያም እኔም አንደ መለስ ብለው በንቀት ስሜት የሉም ጠፍተዋል ስላሉዋቸው ድርጅቶች መረጃ ስለሌለኝ የምለው አይኖርም፤ የላችሁም የተባላችሁ መኖራችሁን አሳይዋቸውና አቶ ኃይለማሪም በዚህ አፋቸው ምን እንደሚሉ ለመስማት አብቁን የሚለው ግን መልእክቴ ነው፡፡
አቶ መለስ የሻዕቢያና ወያኔ ጸብና ፍቅር ለወላይታው ምኑ ነው ብለው ለአቶ ኃይለማሪያም አለነገሯቸው እንደሁ እንጂ ወያኔን አዲስ አበባ ያደረሰው ለራሱም የማይሆን ያሉት ሻዕቢያ ነው፡፡ ይህም ብቻ አይደለም ሌላው ኢትዮጵያዊ (የወያኔ ታጋይ ጭምር ) የማይታመን ሆኖ እስከ ተጣሉበት ግዜ ድረስ ቤተ መንግሥቱ ይጠበቅ የነበረው በሻዕቢያ ሰራዊት እንደነበረ የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡ስለሆነም አቶ ኃይለማሪያም ወያኔዎች ስለ ሻዕቢያ ዛሬ የሚሉትን ብቻ እየተቀበሉ መናገር ሳይሆን ትናንት ምን ይሉ ምንስ ያደርጉ እንደነበር የተጻፈ አንብበው የነበረ ጠይቀው ቢናገሩ ቢያንስ ጠቅላይ ምኒስትር ለሚለው ማዕረጋቸው( ይስሙላም ቢሆን) የሚመጥን ይሆናል፡፡
ከላይ እንደተገለጸው አቶ ኃይለማሪያም ስለ አብሮ መስራት ሲናገሩ ምርጫ ቦርድ የመዘገባቸውን ፓርቲዎች በሙሉ ጠርተን አብዛኛዎቹ ተገኝተዋል ነው ያሉት፡፡ አብዛኛው የሚለው የጥቅል መጠሪያ ለወያኔም ለፓርቲዎቹም ለምርጫ ቦርድም እያገለገለ ነው፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች በቁጥር ሲገለጹ እንጂ በስም ሲጠሩ አይሰማም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ምርጫ ቦርድ መዝገብ ላይ ሰፍረው የሚገኙት አንዳንዶቹ የሌሉ ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ምርጫ ሲመጣ ብቻ ብቅ የሚሉና ለምርጫ የሚሰጣቸውን ገንዘብ ተቀብለው የአጃቢነት ሚናቸውን ተወጥተው ለአራት ዓመት የሚጠፉ ናቸው፡፡ ጥቂቶቹም ፓርቲ ለመባል የሚያበቃ ቁመና የሌላቸው አቶ በረከት የፓርቲዎቹ ጥቅማቸው አልታይ ብሉአቸው ይሁን ስሜት ገፋፍቶአቸው ወይንም እውነት ተናንቆአቸው ባይታወቅም በመጽሀፋቸው የቤተሰብ ፓርቲ ሲሉ የገለጹዋቸው ናቸው ፡፡ በርግጥ ለመናገር አንዳንዶቹ ሊቀመንበር ተብሎ ከሚጠራው ሰው ቀጥሎ የሚጠራ ሶስትና አራት ሰው የሌላቸው በመሆኑ የቤተሰብ ፓርቲ የሚለውንም አያሟሉም፡፡ ብዙዎቹ ከተባሉት ከእነዚህ ስመ ፓርቲዎች ውስጥ ብዙዎቹን እንኳን ህብረተሰቡ ምርጫ ቦርድም አያውቃቸው፡፡ ድረ ገጹን ብትጎበኙ ቦርዱ ስለማያውቃቸው የተመዘገቡበትን ቀን መሙላት አቅቶት ቦታው ክፍት ሆኖ ታገኙታላችሁ፡፡ ፤ብቻ ብዙዎች እየተባሉ ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ይውላሉ፡፡እነዚህን በስም እየጠቀሱ መሪ የሚባሉትን ሰዎች ምንነትና ማንነት እያሳዩ መግለጽ የሚቻል ቢሆንም የሚፈይደው ነገር የለም፡፡ የምርጫ ቦርድን ድረ ገጽ ከጎበኙ ሌላም ነገር ይታዘባሉ፣ ምርጫ የማስፈጸም ብቃት አለው ተብሎ ምስጋና የተዥጎደጎደለት ይህ ተቋም ድረ- ገጹን ወቅታዊ ማድረግ ተስኖት ከአስር ዓመት በፊት የነበረ መረጃ ነው የሚያገኙት፡፡
ፓርቲ ማለት በምርጫ ቦርድ ተመዝግቦ የህጋዊነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የተሰጠው ነው ካልተባለ በስተቀር ብዙዎች የሚባሉት ከወያኔ ዳረጎት እየተቀበሉ፤ በምርጫ ቦርድ መልካም ፈቃድ ፓርቲ እየተባሉ፤ በአዳማቂነትና በአጃቢነት የሚያገለግሉ፣ እንኳን አባል የተሟላ አመራር የሌላቸው ናቸውና ፓርቲ ሊባሉ የሚበቁ አይደሉም፡፡ መሪ ለሚባሉት ሰዎች ግን የእለት እንጀራም የሕይወት መንገድም ሆኖ እየጠቀማቸው ነው፡፡ በአንጻሩ ብዙም ባይሆን ለወያኔ ዕድሜ መርዘምም እየረዱ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግን ኖሩም አልኖሩ “ተለበሰ ቀረ የደበሎ ቅዳጅ ”እንደሚባለው ናቸውና ምንም ፋይዳ የላቸውም፡፡ እንደውም የማይቻል ሆኖ እንጂ አለመኖራቸው ይሻል ነበር፡፡
ሙቱን ፓርላማ ህይወት ያለው ለማስመሰል የተጀመረው ድራማ ደራሲና አዘጋጁ ሰልችቶአቸው እስካላቆሙት ድረስ በጀመረው መልኩ ወቅታዊ የትኩረት አቅጣጫዎችን እየተከተለ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ የእኛም ማየትና መስማት ብሎም ከምናይ ከምንሰማው ተነስተን ብዕር ከወረቀት ማገናኘት እንዲሁ ይቀጥላል፡፡እስካላቆሙት ድረስ ያልኩት አቅጣጫ ለማስቀየሻ እየተባሉ በዚህ መልኩ የሚጀመሩ ጉዳዮች ሲዘልቁ ስለማይታይ ነው፡፡ደግሞስ የማስመሰል ስራ መች ብዙ መንገድ ያስኬዳል፡፡ይህ የፓርላማ ድራማ ቀልቡን የሚስበው ሰው ኖር ይሆን!!

ለጥቅምት 22 ሰማዕታት የመታሰቢያ ፕሮግራም ተካሄደ (ነገረ ኢትዮጵያ) ለጥቅምት 22 ሰማዕታት የመታሰቢያ ፕሮግራም ተካሄደ (ነገረ ኢትዮጵያ)

http://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2015/11/semayawi-party-remembering.jpg?bd378dምርጫ 1997 ዓ.ምን ተከትሎ ጥቅምት 22/1998 ዓ.ም በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ቀጥታ ትዕዛዝ በ‹‹ፀጥታ ሀይሎች›› በጭቃኔ ለተገደሉት ሰማዕታት እና ለቆሰሉት ኢትዮጵያውያን በሰማያዊ ፓርቲ ፅ/ቤት መታሰቢያ ተደረገ፡፡ የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች ጥቅምት 22/1998 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የገጠማቸውን በተለይም ኢትዮጵያውያን ሲገደሉ ያዩትንና የራሳቸውን ገጠመኝም አካፍለዋል፡፡
የፕሮግራሙ ተሳታፊዎቹ የተገደሉትን በክብር መቅበር እንዳልቻሉ እና ታፍሰው በተለያዩ እስር ቤቶች መታሰራቸውን አስታውሰዋል፡፡ አዛውንቶችንና ህፃናትን በጭካኔ ተገድለው ባንክ ሊዘርፉ ነው የተባለበትና የሥርዓቱን የህግና ሞራል የማይገድበው መሆኑን ያሳየበት ነውም ብለዋል፡፡ ሥርዓቱ ካለፈው ስህተቱ ሳይማር ዛሬም ለመግደል ዝግጁ እንደሆነ መቀጠሉንም ገልፀዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ሥርዓቱ ወደ ባሰ አምባገነንነት በመግባቱም ትግሉን መቀላቀላቸውን ገልፀው፣ ዘላቂው አማራጭ የሰማዕታቱን የትግል መንፈስ ፅናት ይዞ መታገል ነው ብለዋል፡፡ እነሱ አላማ ያደረጉትን ተጉዘው በአንድነት የኢትዮጵያን እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚገባቸውም ገልፀዋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በ1997 ዓ.ም በኋላ የሥርዓቱ ሁኔታ እየተባባሰ እንደመጣና ለዚህም ዋናው ምክንያት ኢትዮጵያውያን ሥርዓቱ የሚያደርስብንን በደል ችለን ወደ ውስጥ የምናለቅስ መሆናችን ነው ብለዋል፡፡ ሥርዓቱ ይቅር የማይደረግለት ሆኖ፣ ፖለቲካው በመነታረክ መቀጠሉን ትክክል እንዳልሆነም ገልፀዋል፡፡
‹‹ሥርዓቱ ታሪክና የጋራ ነገር የላችሁም ብሎናል፡፡ መናናቅንና ሀይማኖትን ማቃለልን በተግባር አሳይቶናል፡፡ የወደፊት ኢትዮጵያ በእኛ እጅ እንድትሆን ከፈለግን የነበረውን የሀገራችን እሴት ማናናቅ የለብንም፡፡›› ያሉት ኢ/ር ይልቃል ኢትዮጵያውያን የገነቧቸው እሴቶች ሁሉ በወጣቱ ልብ ውስጥ ማደር እንዳለባቸው፣ ሰማዕታቱ የሞቱለት አላማና ኢትዮጵያውያን የገነቡት እሴት መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

ቅዳሜ 26 ሴፕቴምበር 2015

በኢትዮጵያ ታሪክ ጉዳይ ላይ ኢሕአዴግን እንዴት ማመን ይቻላል?!

በኢትዮጵያ ታሪክ ጉዳይ ላይ ኢሕአዴግን እንዴት ማመን ይቻላል?!

በዲ/ን ኒቆዲሞስ
ወንድማችን ዲ/ን ዳንኤል የኢትዮጵያችን ልዩ ቅርስ በኾነው የዘመን አቆጣጠራችንን በተመለከተ አንድ ጥያቄ አንስቶአል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር በተመለከተ ‹‹ጠቅላይ ሚ/ሩን እንመን ወይስ አርቲስቶቻችንን?!›› የሚል ጥያቄ አንስቶ አንድ ትዝብትና ማሳሰቢያ አከል ጽሑፍ አስነብቦናል፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላለሁ በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠርም ሆነ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ታሪክ ጉዳይ ላይ ኢሕዴግን/ክቡር ጠቅላይ ሚ/ሩን እንዳናምናቸው የሚያደርጉን አንዳንድ የታሪክ ሐቆች እንዳሉ ላንሣ፡፡
እስቲ እነዚህን ሐቆች በጥቂቱ ብቻ ለማየት እንሞከር፡፡ በመሠረቱ የአገሪቱን ታሪክ ወደ መቶ ዓመት አውርዶ ለሚተነትነው፣ ጥንታዊው የሆነው ፊደላችን፣ ሦስት ሺሕ ዘመንን ያስቆጠረውን የሥነ-መንግሥት ታሪክ ‹‹የአቢሲኒያውያን/የነፍጠኞች ቅኝ ገዢዎች ታሪክ›› አድርጎ የኢትዮጵያን ሕዝቦች ታሪክ በብሔር ብሔረሰቦች ማዕቀፍ ቀንብቦ ዳግም ለመፍጠር ለሚውተረተረው፤ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የሚመሩት የኢሕአዴግ መንግሥት በምን ሞራልና ተጠየቅ፡- ‹‹ከአፍሪካ አገራት ሺሕ ዘመናትን ያስቆጠረ የራሳችን ፊደልና የዘመን አቆጣጠር ያለን ኩሩ ሕዝቦች …፡፡›› ተብሎ በአደባባይ ሊነግሩን እንደደፈሩ አይገባኝም፡፡ የታሪክ እውነት/ሐቅ ሲያሻን የምንደርበው እንዲያ ሲል ደግሞ አውልቀንና አሽቀንጥረን የምንጥለው የበረሃ ሽርጥ ኾነ እንዴ ጎበዝ …?! ይሄ በእውነት ያስተዛዝባል፡፡ ወይስ ደግሞ እንደው ሳንሰማ ኢሕአዴግ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ያለውን አቋም አስተካክሎ ይሆን እንዴ … እ…እ…እ… አይመስለኝም፡፡
በዚህ ረገድ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትራችን የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊም፣ ‹‹… የኢትዮጵያ ታሪክ የመቶ ዓመት ታሪክ ነው፣ የአክሱም ሐውልት ለወላይታው ምኑ ነው …?! እንዳላሉን ኹሉ የኢትዮጵያ ሚሊኒየም ሲከበር ባደረጉት ንግግራቸው፣ ‹‹… እኛ ኢትዮጵያውያን የሦስት ሺሕ ዘመን ታሪክና መንግሥት ያለን ነጻና ኩሩ ሕዝቦች …›› ሲሉ ሰምተናቸው መገረማችንን አስታውሳለኹ፡፡ እዚህ ጋራ የኢትዮጵያን ታሪክ ‹‹በአቢሲኒያውያን/በነፍጠኞች ቅኝ ግዛት ወረራ›› የታሪክ መነጽር የሚመለከተው ኢሕአዴግ ሙሉ ድጋፉንና ፈቃዱን በቸረበትና የኤርትራውያን ጥያቄ ‹‹የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው›› በሚል የኤርትራውያን ነጻ እንዲወጡ ባደረገበት ወቅት የኾነውን የታሪክ ቀውስም በጥቂቱ ማየት እንችላለን፡፡
ትናንትና የኢትዮጵያ አካል የነበሩት ኤርትራውያን ወገኖቻችን ነጻነታቸውን ባወጁ ማግሥት የዘመን አቆጣጠራቸውን ወደ ጎርጎርሳውያን የቀየሩት የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ቅኝ ገዢዎቹ አቢሲኒያውያን/ነፍጠኞች እንደ ብርድ ልብስ የደረቡብን የእኛ ያልሆነ- ታሪካችንን፣ ቅርሳችንንና ማንነታችንን የሚያራክስ፣ የሚያጣጥል ነው በሚል አመክንዮ እንደሆነ የምንስተው አይመስለኝም፡፡ የኋላ ኋላ የኾነውን ነገር ኹሉ እናስታውሳለን፤ ባልነበረ የፈጠራ ታሪክ ሺሕዎች ጭዳ የኾኑበትን የጦርነት፣ እልቂት መዘዝ በኀዘን እናስታውሳለን፡፡ አሁንም ድረስ የኹለቱ አገራት ጉዳይ የተዳፈነ እሳት ሆኖ አለ፡፡
በዚሁ የፈጠራ ታሪክ ጦስ የሆነውን ሌላኛው ትዝብቴን ላክል፡፡ ኤርትራዊ ብሔርተኝነትን በአዲስ የታሪክ ሂደትና ትንታኔ ለመፍጠር ሲውተረተር የነበረው የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂና ደጋፊዎቹ/ብሔርተኛ ኤርትራውያን ባለፈው ዓመት ደግሞ፣ ‹‹… ለመሆኑ እንደው የሆነስ ሆነና ኢትዮጵያ ከማን ተሸላ ነው እኛን ሥልጡን፣ የራሳችን የዘመናት ታሪክ፣ ቅርስ፣ ባህልና ሥልጣኔና ያለንን ሕዝቦች ቅኝ ለመግዛት የቻለችው?!›› በሚል ለዓመታት ሲያቀነቅኑ የነበረውን ‹‹ኢትዮጵያ ቅኝ ገዘታናለች›› የሚለውን የታሪክ ምጸት በውስጣቸው የፈጠረውን የበታችነት ስሜትና የማንነት ቀውስ በሌላ ተረት ተረት ላማከምና ኤርትራዊ ብሔርተኝነትን በሁለት እግሩ ለማቆም ደፋ ቀና ሲሉ ታዝበናቸዋል፡፡
በተጨማሪም ሰፊው የኦሮሞ ሕዝብንም ለዘመናት ሲጠቀምበት የነበረውን ፊደሉን ከግእዝ ፊደል ወደ ላቲን ፊደል እንዲቀይር ያስገደደው ይኸው ኢሕአዴግ በሚያቀነቅነው ‹‹የአቢሲኒያውያን/የነፍጠኞች የቅኝ ገዢዎች ታሪክ›› ትንታኔ መነሻነት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ታዲያ ባለ ሥልጣኖቻችን እንዲህ የሚያጣጥሉትንና የሌሎችና ታሪክና ቅርስ፣ ማንንት ያመከነና የዘረፈ ነው ብለው የሚከራከሩበትን የኢትዮጵያን ታሪክና ቅርስ እንዴት በአደባባይ ሺሕ ዘመናትን ያስቆጠር የፊደል፣ የዘመን አቆጣጠር ያለን የሦስት ሺሕ ዘመናት ታሪክ ባለቤት ሕዝቦች ሊሉን የቻሉበትን ድፍረት የት እንዳገኙት ለመጠየቅ፣ ለመሞገት እንገደዳለን፡፡ እንዲህ እንደ እስስት በመለዋወጥስ የታሪክ ሐቅን መለወጥ ይቻላል እንዴ?!
ከኢትዮጵያን ታሪክ አንስቶ እስከ ፊደላችን ድረስ በርካታ ጥያቄዎች አሉብን፡፡ ለአንዳንዶች የኢትዮጵያ የሺሕ ዘመናት ታሪክ የአቢሲኒያውያን/የነፍጠኞች ቅኝ ግዛት ታሪክ እንደሆነ ነው የሚሰማቸው፡፡ ለአንዳንዶች ደግሞ ፊደላቱ ያለ ቅጥ በዝተዋልና ይቀነሡ በሚል ሽንጣቸውን ገትረው ይከራከራሉ፡፡ ይህን ጥያቄ መዳኘትና መልስ መስጠት የሚገባቸው ከእውነት ጋር የወገኑ የእውቀት ሰዎች-ጠቢባኑ ደግሞ ከመድረክ ተገፍተው ታሪክን እንዳሻቸው የሚተነትኑ አድር ባዮች፣ በአገሪቱ ታሪክ ማኅፀን ሌላ ለከፋፋይ ፖለቲካቸው የሚመቻቸውን ጽንስ እያበጁ እያየንና እየሰማን ይኸው በፍርሃት ተሸብበን አለን፡፡ እነርሱም ያለ ምንም እፍረት ታሪካችንን ለጊዜያዊ ፖለቲካቸው ጥቅም ሲሉ እንዳሻቸው ሲለዋውጡት በአግርሞት እያየናቸውና እየሰማናቸው ነው፡፡
በመጨረሻም ወደ ዘመን አቆጣጠራችን ጉዳይ ስመለስ ዛሬ ዓለም ኹሉ እየተደመመበት ያለውንና ይህ የዘመን አቆጣጠርም ከሥነ ፍጥረት ሕግና ሂደት ጋራ የተስማማ እንደሆነ የሚያሳዩ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡ ባለፈው ዓመት የካቶሊኩ ፖፕ የነበሩት ጀርመናዊው ፖፕ ቤኔዲክት የአውሮፓውያኑ የዘመን አቆጣጠር ስህትት እንደሆነና ከአውሮፓውያኑ የዘመን አቆጣጠር ይልቅ ይኸው የእኛው የኢትዮጵያ ዘመን አቆጠጠር ትክክል እንደሆነ Jesus of Nazareth: The Infancy Narratives በሚል መጽሐፋቸው ለመላው ዓለም አሳውቀዋል፡፡
የኢትዮጵያን ዘመን አቆጣጠርና ደማቅ ክብረ በዓሉን በተመለከተ ደግሞ ዘንድሮ በተለየ ሁኔታ እንደ ለንደኑ ቢ.ቢ.ሲ፣ የአሜሪካው ሲ.ኤን.ኤን፣ የዶሃው አልጀዚራና የኢራኑ ፕሬስ ቴሌቪዥኖች ሽፋን በመስጠት ዘግበውት ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ የኩባ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በስፓኒሽ ቋንቋ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ኩባውያን ስለ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሰፊ ሽፋን ሰጥተው ልዩ ዘገባ እንዳቀረቡ ተከታትለናል፡፡ ተወደድም ተጠላ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅርስ የኾነው ይህ የዘመን አቆጣጠራችን ከአፍሪካ አልፎ የዓለም ኹሉ ቅርስ ወደመሆን እየተሸጋገረ እንዳለ እየታዘብን ነው፡፡ ይህን ዓለም ሁሉ አምኖ የተቀበለውንና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አሻራ ያለበትን የአገሪቱን የታሪክ ሐቅ መካድ፣ ማፋለስ፣ መበረዝ፣ … ከራስ ጋራ፣ በፍቅርና በአንድነት የጥበብ ልዩ ሸማ ከተዋበው፣ ዘመናት ካልሻሩት ኢትዮጵያዊ ማንነት፣ ታሪክና ቅርስ ጋራ መጣላት መሆኑን በመግለጽ ልሰናበት፡፡
ሰላም!

ሐሙስ 6 ኦገስት 2015

የናትናኤል ማስታወሻ – ጥቂት ስለ ማዕከላዊ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)

የናትናኤል ማስታወሻ – ጥቂት ስለ ማዕከላዊ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)

(ከቂሊንጦ እስር ቤት)
ናትናኤል ፈለቀይህንን ጽሁፍ ስጽፍ ዓላማዬ ማዕከላዊ ያሉ ሥራቸውን አክብረው የኢትዮጵያውያንን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ የሚሰሩ ጥቂት ፖሊሶችን (ምናልባትም በአንድ እጅ ጣቶች ተቆጥረው የሚያልቁ መርማሪዎችን) ለማበረታታት አይደለም፡፡ይህን ዓላማ በሌላ ጽሁፍ እመለስበት ይሆናል፡፡ ለነገሩ ሥራቸውን አክብረው የሚሰሩ ባለሙያ ፖሊሶች የኔ ማበረታታትን የሚፈልጉ አይደሉም፡፡ያሉበት ደረጃ ላይ ለመድረስ በኃላፊነት ማሰብ የቻሉ ስለሆኑ፡፡
ስለዚህ የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በተቋሙ ውስጥ ኢትዮጵያ የምትተዳደርባቸውን ሕጎች ለማክበር(የተላለፉትን ለይቶ ለማስቀመጥና በስህተት የተጠረጠሩትን ነጻ ለማውጣት) ሳይሆን የአገዛዙን ዕድሜ ለማርዘም የሚሰሩትን አብዛኞቹን ሙያቸውን የማያከብሩ ፖሊሶች ‹‹ምርመራ›› ሴራቸውን እንዴት እንደሚፈትሉ ለማሳየት፣ ቢያንስ ሌላ ስልት እስኪፈጥሩ ድረስ በሀገሪቷጉዳይ ያገባናል የሚሉ ኢትዮጵያውያን አንዴ በተቋሙ ውስጥ ከገቡ በኋላ ሊገጥማቸው የሚችለውን የተንኮል መረብ ለማስረዳት እና ቀድሞለማዘጋጀት ያሰበ ነው፡፡
እውነት ለመናገር እነዚህ የስርዓቱ ጠባቂ ሎሌዎች የህዝብን ደህንነት ለአደጋ የሚያጋልጥ ወንጀልን እና ወንጀለኞችን ለይተው አውቀው ፍትህ እንዲያገኙ አድርገው ጭራሹንም አያውቁም ማለት አልችልም፡፡ ስለዚህ አሁን የማብራራው ጉዳይ ለወንጀለኞችም መዘጋጃ ሊሆን እንደሚችል አምናለሁ፡፡ ነገር ግን ወንጀለኞች ከፍትህ እንዲያመልጡ ጠብታ ውሃ ማቀበል አልፈልግም፡፡አንድ ነጻ ሰው ባልሰራው ወንጀል ከሚቀጣ መቶ ወንጀለኞች ቢያመልጡ ይሻላል የሚለው የህግ መርህ የበለጠ አቋሜን ያስረዳል፡፡
ሁለት ማሳሰቢያዎች አሉኝ፤ አንደኛ፡-እኔ ተይዤ ማዕከላዊ እስክገባ ድረስ ልታሰር እንደምችልአስቀድሜ ባውቅም ሊጠብቀኝ የሚችለውን የ‹‹ምርመራ›› ሂደት (የሴራ መረብ የበለጠ ይገልጸዋል) አጽንዖት ሰጥቼ አላሰብኩበትም፡፡የምርመራው ሂደትን ተንተርሼ የማነሳቸውን ሀሳቦች የተረዳሁት በምርመራ ውስጥ ካለፍኩ በኋላ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ይህንን ጽሁፍየሚያነቡ ሰዎች እኔ በፍርሃት ያላደረኳቸውን ነገሮች እንዲያደርጉ (በምርመራ ሂደት) የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ሁለተኛ ይህንን ጽሁፍ በሀገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል እና ሀሳቡን ሕገ-መንግስታዊ ድንጋጌዎች በሚፈቅዱት መሰረት በነጻነት የሚገልጽ ሁሉ ጊዜ ሳይሰጥ ቢያነበው እመክራለሁ፡፡
ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ሀሳብ የአቃቤ ህግ ምስክር ከተሰማ በኋላ በብይን የተለቀቁ ሙስሊምወንድሞች መጻፋቸውን አስታውሳለሁ፡፡ ያ ጽሁፍ የተሻለ የተደራጀ ነው ብየ ስለማስብ እንዲነበብ እጋብዛለሁ፡፡ በተጨማሪም ስርዓቱንየሚደግፉ ሰዎች ይህንን ጽሁፍ በማንበብ ወንጀለኞች ከሚጠቀሙበት ለተሻለ አላማ ያውሉታል ብዬ ስለማስብ ሁለቱም ባያነቡት ይሻላቸዋል፡፡
ወደ ዋናው ሀሳብ ልግባ፤ ከተያዝኩ በኋላ በነበሩ የመጀመሪዎቹ ቀናት ውስጥ የነበሩት‹‹ምርመራዎች›› እውነቱን እና የማውቀውን ብቻ በመናገር እራሴን ነጻ ማውጣት እንደምችል መተማመኛ መስጠትን ያለሙ ነበሩ፡፡ ለምሳሌሚያዝያ 18/2006 (በተያዝኩኝ በማግስቱ ቅዳሜ) የነበረውን ምርመራ ም/ሳጅን መኮንን በተረጋጋ ሁኔታ የምርመራው ሂደት በመከባበርእንደሚቀጥል፣ ልክ እኔ የዕለት ስራየን ለማከናወን ሙያ እንደሚጠይቀው ያክል የፖሊስ ምርመራም ተመሳሳይ እንደሆነ፣ በቁጥጥር ስርየዋልኩት ተጠርጥሬ ብቻ እንደሆነ እና በምርመራው ሂደት ወንጀል አለመፈጸሜ ከተረጋገጠ በነጻ ወደቤቴ እንደምሄድ ነበር ያስረዳኝ፡፡ይንቁናል የሚል ስሜት አስቀድሞ ስለሚያድርባቸው ተቋሙን እና እራሳቸውንም ከፍ የሚያደርግ ነገር በነዚህ የመጀመሪያ ‹‹የምርመራ››ቀናት ይናገራሉ፡፡
‹‹ይህ የወረዳ ጣቢያ አይደለም፡፡ የክልልም አይደለም፡፡ ይህ የፌደራል ወንጀል ምርመራነው፡፡ ሚኒስትር ደረጃ የደረሱ የመንግስት ባለስልጣናት ሳይቀር እዚህ ተመርምረዋል›› ነበር ያለኝ ም/ሳጅን መኮንን በአጽንኦት፡፡ከዚህ ገለጻ በኋላ ነበር ስለህይወት ታሪኬ በመጠየቅ ቃል የመስጠት ሂደቱን የጀመርኩት፡፡
ማስታወሻ- 1. ቃል ያለመስጠት መብት
ቃሌን ያለመስጠት መብት ስላለኝ ቃሌን አልሰጥም ለማለት መጀመሪያ መብቱ እንዳለ ማወቅይጠይቃል፡፡ በወቅቱ ይህ መብት እንዳለኝ ማወቄን እጠራጠራለሁ፡፡ አውቅ ከነበረም ግን በፍጹም ትዝ አላለኝም፡፡ ቃል አለመስጠትአንድ ለምርመራ ሂደቱ ተባባሪ አለመሆንን ማሳያ ነው፡፡ ለተቋሙ የጭቆና መሳሪያ ስለመሆኑ በቂ ማስረጃ እንዳለ አምነን ተጨማሪ ማረጋገጫዕድል (benefit of the doubt) መስጠት የማንፈልግ ከሆነ ይህ ትክክለኛው አማራጭ ይመስለኛል፡፡ ከግምት መግባት ያለበትቃል በመስጠቱ ሂደት ውስጥ ፖሊስ በእርግጠኝነት ስህተት መስራቱ አይቀርም፡፡ ይህም የማይቀረው ክስ ሲመጣ ተቋሙን ማጋለጥ እንደስልት የሚወሰድ ከሆነ እንደማስረጃ ሊቀርብ ይችላል፡፡ ለምሳሌ በኛ ጉዳይ የቀረበብን ክስ የሽብር ቡድን በኅቡዕ አደራጅተዋል በሚልሲሆን ሁላችንም ቃል ስንሰጥ የተጠየቅነው እና ስናብራራ የነበረው ግን በይፋ ስንጽፍበት እና ዘመቻዎቻችንን ስናካሂድበት ስለነበረውዞን 9 ነው፡፡
አቃቤ ህግ በክሱ እያለ ያለው የከሰስኳችሁ በመጻፋችሁ እና መብትን የሚጠይቁ ዘመቻዎችንበማድረጋችሁ (በአጠቃላይ ከዞን-9 ጋር በተያያዘ) ሳይሆን ሌላ የህቡዕ ቡድን መስርታችሁ ለሽብር ዓላማ ስትንቀሳቀሱ ስለነበር ነው፡፡የሰጠነው ቃል እና ክሱን ለመደገፍ የቀረቡት ማስረጃዎች ግን ስለ ዞን-9 አውርተው አይጠግቡም፡፡ በመጀመሪያዎቹ ቀናት የሚነግረውን‹‹ተቋሙ ገለልተኛ ነው፣ ሰዎችን ወንጀለኛ ለማድረግ ሳይሆን እውነትን ፈልፍሎ አግኝቶ ነጻ ሰውን ወደቤቱ ይሸኛል›› የሚለውን ዕምነትበቀላሉ ማስረጽ ከቻሉ የሚቀጥሉት ጥርጣሬ ወደመዝራት ይመስለኛል፡፡ በቀላሉ ያሉትን የማያምኑ ከሆነ ግን የተጠርጣሪውን በራስ መተማመንለመሸርሸር ህገ-ወጥ ተግባራቸውን ይቀጥላሉ፡፡
‹‹ምርመራ›› በጀመርኩ በአራተኛው ቀን የተከሰተው ይሄው ነው፡፡ ሚያዝያ 21/2006ዓ.ም ምሽት ድረስ ‹‹በምርመራው›› ሂደት ውስጥ ስሳተፍ የነበረው በሙሉ የራስ መተማመን ነበር፡፡ ለምሳሌ ም/ሳጅን መኮንን፣ ም/ሳጅንእቴነሽ፣ እና ሳጅን ፈይሳ በነበሩበት ታስሬ ‹‹እየተመረመርኩ›› ያለሁት ሀሳቤን በነጻነት ለመግለጽ ባለመፍራት ነው፡፡ ያኔ ‹‹ፖሊስለህዝብ የሚሰራ ተቋም ነው የምትሉትንም አላምንም፡፡ በአሁኑ ሰዓት ፖሊስ እንደ ተቋም እየሰራ ያለው አገዛዙን ስልጣን ላይ ለማቆየትነው›› ብያቸዋለሁ፡፡
ከላይ በጠቀስኩት ቀን ማታ ግን ሌላ ሊከሰት እንደሚችል የማውቀው፣ ግን ከምር ያልተዘጋጀሁበትነገር ተከሰተ፡፡ ምሽት 1፡00 አካባቢ የተጀመረው ‹‹ምርመራ›› ቶሎ ኃይለ ቃል ወደመሰንዘር እና ዛቻ ተለወጠ፡፡ በወቅቱ ም/ሳጅንመኮንን፣ የመጀመሪያ ቀን ፍርድ ቤት የወሰደን እና በየመተላለፊያው ሳገኘው ጭምር ቤተሰብ እንዲያገኘን መብት አለን፣ ፍርድ ቤትአዝዞልን ሳለ ለምንድነው የማታገናኙን እያልኩ ስጠይቀው የቆየሁት ሳጅን ምንላርግልህ እና ማዕረጉን የማላስታውሰው ፀጋየ (በቅጽልስሙ ጥጋቡ) የሚባል መርማሪ ነበሩ፡፡ የ‹‹ምርመራ››ውም ዋነኛ አጀንዳ የዞን 9 ድብቅ ግብ እና የውስጥ የስራ ክፍፍል (መዋቅር)በተመለከተ ነበር፡፡ በሁለቱ ጉዳይ ላይ እውነተኛው የማውቀው መልስ ‹‹መዋቅር የለውም›› የሚለው ነበር፡፡ ዞን 9 ድብቅ ግብምመዋቅርም ኖሮት አያውቅም፡፡ ሳጅን ምንላርግልህ መልሴ አላጠገበውም፡፡ ‹‹እኔ እንደሱ እንዳልመስልህ (የእኔን ጉዳይ በዋነኛነትወደያዘው ም/ሳጅን መኮንን እየጠቆመ) አለቅህም! ሽባ ነው ማደርግህ! ልብስህን አስወልቄ ሳልለጠልጥህ እውነቱን ብትነግረኝ ይሻልሃል!››የሚሉ ዛቻዎች ደረደረ፡፡ እኔ ግን መዋቅሩን በተመለከተ ስራ ለማቅናት ሲባል ምክረ ሀሳብ ቀርቦ እንደተወያየንበት፣ ነገር ግን ሀሳቡውድቅ እንደተደረገ ከማስረዳት በቀር የምጨምረው የማውቀው እውነት አልነበረም፡፡ ም/ሳጅን መኮንን እና ፀጋየ (ጥጋቡ) በየተራ ክፍሉንለቀው ከወጡ በኋላ ሳጅን ምንላርግልህ ከወንበሩ በመነሳት ምቾት በሚነሳ ሁኔታ ከተቀመጥኩበት ፊት ተጠግቶኝ ቆሞ ጥያቄዎችን ይደረድርጀመር፡፡
ጥያቄ፡- ‹‹ለምንድነው እነ ርዕዮትን ብቻ የምትጠይቁት?››
መልስ፡- ‹‹ኢትዮጵያውያን ስለሆኑ እና የታሰሩት በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት ነው ብለንስለምናምን፡፡››
ጥያቄ፡- ‹‹(በቁጣ) ባንክ የዘረፈውስ ኢትዮጵያዊ አይደለም? ለምንድነው ሌላውን ወንጀለኛየማትጠይቁት?››
በእውነት እዚህ ጋ ሳቄ መጥቶ ነበር፡፡ በርግጥ የታሰረን ሁሉ ከተቻለ መጠየቅ ለህሊናየሚያስደስት ስራ ነው፡፡ እግዜርም ይወደዋል፡፡ ግን ርዕዮትን ስጠይቅ እንዲሰማት የምፈልገው፣ ትግሏ ዋጋ እንዳላጣ እና እንዳልተረሳችነው፡፡ ይህም ትንሽም ቢሆን ብርታት ይጨምርላታል ከሚል ተስፋም ጭምር ነው፡፡ ተመሳሳይ ነገር የባንክ ዘራፊ እንዲሰማው በፍጹምአልፈልግም፡፡ ጥያቄው ቀጠለ፣
‹‹ዝዋይ ለምን ሄዳችሁ?››
‹‹እነ ውብሸትን ለመጠየቅ››
‹‹አትዋሽ! በቀለ ገርባን ለመጠየቅ ነበር?››
‹‹አዎ በቀለንም ለመጠየቅ ነበር፡፡››
‹‹በቀለ ምን እንደሚል ታውቃለህ? ለምን እንደታሰረ ታውቃለህ? ኦሮምኛ ትችላለህ?››
‹‹አልችልም››
‹‹በቀለ እኮ የሚለው ኦሮምኛ የማይችሉ ሰዎች በሙሉ ይታረዱ ነው፡፡››
ስለ በቀለ ገርባ የማውቀው ጥቂት ነገር ከሚለኝ ጋር ፍጹም የሚጣጣም ስላልነበር የፊቴንመለዋወጥ መቆጣጠር አልቻልኩም፡፡ ፊት ለፊቴ ተደንቅሮ የጥያቄ ዝናብ ሲያወርድ የነበረው ሳጅን ምንላርግልህ አሁን ማድረግ የሚፈልገውንለማድረግ በቂ ምክንያት አገኘ፡፡ የመጀመሪያዋን ጥፊ ሰነዘራት፡፡ መብቴን እየነካ እንደሆነ ስነግረው ‹‹ይህንን ነው አይደል ፈረንጆቹወስደው የሚያሰለጥኗችሁ?›› በማለት ስራውን ቀጠለ፡፡ ድብደባው እዚያ ቤት ከሚፈጽሙት ሰቆቃዎች (torture) አንጻር ትንሽ ቢሆንምአሸነፈኝ፡፡ አሁን የሚጸጽቱኝንም ቃላት ተናገረኝ፡፡ ከውጭ የነበሩት ሁለቱ መርማሪዎች ድብደባ ሲፈጸምብኝ በነበረበት ወቅት በመሐልመጥተው ገላጋይ ሆነው ነበር፡፡ ምንላርግልህ ግን ለያዥ ለገናዥ አስቸገረ፡፡
ማስታወሻ፡-2. መርማሪዎች አንድ አላማ ነው ያላቸው
ሁለትና ከዚያ በላይ ሆነው ሲመረምሩ የትኛውንም ማመን አያስፈልግም፡፡ በኋላ ላይ ከሌሎችተጠርጣሪዎች ጋር ሳወራ የተረዳሁት ይህ የተለመደ አሰራር መሆኑን ነው፡፡
ሌላ ተጠርጣሪ ሲመረመር ሳጅን ምንላርግልህ ገላጋይ ሌላኛው ደግሞ እምቡር እምቡር ይላል፡፡ከዚያም ፀጋየ (ጥጋቡ) እኔ ላይ ሲያደርግ እንደነበረው ገላጋይ የሚሆነው መርማሪ ‹‹እኔ ችግር ውስጥ እንድትገባ አልፈልግም፤ ለምንእውነቱን አትነግረንምና ራስህን አትጠብቅም? ደግሞ ዘጠኝ ሆናችሁ ለሰራችሁት ስራ አንተ ብቻህን ለምን ትጎዳለህ? ሌሎቹ እኮ እየተናገሩነው፤ አይደለም ዘጠኝ ሰው የሚያውቀው ነገር ይቅርና ለሌላ አንድ ሰው የነገርከው ነገር እኮ ሚስጥር መሆኑ ያበቃል›› የሚሉ ማግባቢያዎችበመደርደር ምስኪን ምስኪን ሊጫወት ይሞክራል፡፡
የዛን ምሽት ምርመራ ሲጠናቀቅ የሁለት ሰዓት ማሰቢያ ጊዜ ተሰጥቶኝ የዞን 9 ግብ ምንእንደሆነ እና የመዋቅራችንን እያንዳንዱን የስራ ዘርፍ እንዳስታውስ የቤት ስራ ተሰጥቶኝ ከሌሊቱ አምስት ሰዓት ተመልሼ እንደምጠራተነግሮኝ ነበር ወደ ማረፊያ ቤት ውስጥ የተመለስኩት፡፡
በተለምዶ ሳይቤሪያ የሚባለው ማረፊያ ቤት ባለአንድ ፎቅ ህንጻ ሲሆን የታችኛው ወለል በኮሪደርተከፍሎ በግራና በቀኝ አምስት አምስት ክፍሎች አሉት፡፡ ኮሪደሩ መሀል ላይ አንዱ የግድግዳ ሰዓት ተሰቅሏል፡፡ የመጀመሪያ ሰሞንልብ ስላልኩት ሰዓት የማውቀው ምርመራ ክፍል ካሉት ሰዓቶች በመነሳት በግምት ነበር፡፡ ከሳጅን ምንላርግልህ በተሰጠኝ የቤት ስራመሰረት ከምሽቱ አምስት ሰዓት ሲል ተመልሼ ወደምርመራ እጠራለሁ፡፡ ከምርመራ ከተመለስኩ ጀምሮ በአዕምሮዬ ሲመላለስ የነበረው ነገርተጨማሪ መልስ ልሰጣቸው እንደማልችል እና በዚህ ምክንያት ተመልሼ ከሄድኩ በኋላ የሚደርስብኝ ሰቆቃ ማብቂያ ምን እንደሚሆን ማሰብነበር፡፡ ቀኑን ሙሉ በምርመራ በማሳለፌ ድካም የነበረብኝ ቢሆንም እንቅልፍ ሊወስደኝ ግን አልቻለም፡፡ ራሴን አረጋግቼ በተሰጠኝሁለት ሰዓት እረፍት መውሰድ ብፈልግም ምንም ዓይነት ድምጽ በሰማሁ ቁጥር አምስት ሰዓት የሆነ እየመሰለኝ እባንን ነበር፡፡ እነምንላርግልህ ግን አልፈለጉኝም፡፡ አይነጋ የለም ሌሊቱም ነጋ፡፡ ጠርተው ቢደበድቡኝ ይሻል ይሆን እንደነበር እንጃ!
ማስታወሻ፡- 3. እራስን አረጋግቶ በቂ እረፍት መውሰድ
መርማሪዎቹ መቼም ቢሆን ምርመራ ጨርሰናል ደህና እደሩ ብለው አይሸኙም፡፡ ሁል ጊዜ‹‹በኋላ እንገናኛለን፤ አስብበት›› ብለው ነው የሚጨርሱት፡፡ አንዳንድ ጊዜ በቀጠሮ መሰረት ምርመራው ይቀጥላል፡፡ አንዳንድ ጊዜደግሞ የውሃ ሽታ ይሆናሉ፡፡ በቀጠሮ መሰረት ብጠራም ባልጠራም ያለችውን ጊዜ በቂ እረፍት ለማድረግ መጠቀሚያ ማድረግ የሚያዋጣውአማራጭ ነው፡፡ ከድብደባው በባሰ የሚጎዳው የማያቋርጥ ጭንቀት እና የእረፍት እጦት ነው፡፡ ከአሁን አሁን ወደምርመራ ተጠራሁ ብሎመጨነቅ ጥሪውን የማዘግየትም የማስቀረትም አቅም የለውም፡፡ ‹በኋላ እንገናኝ› የምትለዋ ቀጠሮ እረፍት መንሻ ዘዴ ናት፡፡
በመቀጠል የምርመራው ዓላማ የነበረው ከጓደኞቼ ያገኟቸውን መረጃዎች በመጠቀም ብዙ እንደሚያውቁጥያቄ የሚጠይቁትም ከኔ ይምጣ ብለው እንጂ ሁሉ ነገር ላይ መረጃ እነዳላቸው ለማሳመን መጣር ነበር፡፡ በወቅቱ የእኔ ምላሽ የነበረውሁሉንም የሚያውቁ ከሆነ ለኔ ጥሩ እንደሆነ እና ምንም ጥፋት እንደሌለብኝ ከዛ በላይ ማስረጃ እንደሌለ የሚያስረዳ ነበር፡፡
ማስታወሻ፡-4. አብረው የሚሰሩ ጓደኛሞች ወጥ መልስ ለመስጠት አስቀድመው ስምምነት ላይ መድረስ
ስለ አንድ ጉዳይ ሁለት ጓደኛሞች የተለያየ መልስ ከሰጡ ሰቆቃው ሁለቱም ላይ የጠና ነው፡፡አንደኛው ወደሌላኛው መልስ የሚጠጋ ነገር እስካልተናገረ ድረስ ሁለቱም ይሰቃያሉ፡፡ በኛ ምርመራ ወቅት አስቀድመን ምንም የምንደብቀውወይንም የምንዋሸው ነገር እንዳይኖር ስንነጋገር ስለከረምን በተነጋገርነው መሰረት የአንዳችን ቃል ከሌላችን የጎላ ልዩነት አልነበረውም፡፡
በጓደኞች መሀከል ክፍተት ለመፍጠር ሙከራ ያደርጋሉ፡፡ ለምሳሌ ለበፍቄ ‹‹ናትናኤል እኮእውነቱን ነግሮናል፡፡ በፍቃዱ ነው አብዮት እና አመጽ እንድንጠራ የሚገፋፋን ብሏል፡፡ አንተ ለምንድነው እንዲህ የምትደብቅላቸውእነሱ እውነቱን እየተናገሩ›› ብለውታል፡፡ ቀዳዳ ካገኙ ቅያሜ በመፍጠር ከጓደኛሞች መሀል አንዱን መስካሪ ለማድረግ ይጥራሉ፡፡ ማስፈራሪያዎችበታጨቁበት ምርመራ መሀል እራሴን ነጻ ማውጣት ቀላሉ አማራጭ እንደሆነ ደጋግመው ይነግሩኝ ነበር፡፡ ፀጋዬ (ጥጋቡ)፣ ም/ሳጅን መኮንንእና ኢንስፔክተር አሰፋ እየመረመሩኝ በነበሩበት ወቅት ፀጋዬ ተራ ስድቦችን እና ዛቻዎችን ከሰነዘረ በኋላ በዛው አፉ እኔን ማቆየትእንደማይፈልጉ እና የሚፈልጉትን ካልኩላቸው ወዲያውኑ ወደቤቴ እንደሚሸኙኝ አባቴንም መንከባከብ እንደሚሻለኝ ሲነግረኝ ነበር፡፡ የአባቴጤንነት እንዳሳሰበኝ ስለገባቸው ባገኙት አጋጣሚ ለምርመራው ግብአትነት ይጠቀሙበት ነበር፡፡
አብዛኛው የምርመራ ጊዜ በተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና ተደጋጋሚ መልሶች የሚያልፍ ነው፡፡ ይህምምርመራዎችን እጅግ አድካሚ እና አሰልቺ ያደርጋቸዋል፡፡ ዝርዝር ጉዳዮችን በተደጋጋሚ በመጠየቅ ከምሰጠው መልስ ላይ ልዩነት ለማግኘትይህንንም ተጠቅሞ ሌላ አዲስ ነገር ለማውጣጣት ይጥሩ ነበር፡፡ የተሳካላቸው ግን አይመስለኝም፡፡ በተቻለኝ አቅም ቀዳዳ ሳገኝ የማምንበትንአቋም ከመናገር ወደኋላ አላልኩም፡፡ የማውቀውን ለማካፈልም እንደዚያው፡፡ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 39ን የሚቃወም መርማሪአግኝቼ ለምን ልክ ነው ብዬ እንደማምን አስረዳኋቸው፡፡ በተለያየ ጊዜ የወሰድኳቸው የበይነ መረብ ደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎችንምበተመለከተ ያብራራሁለትም መርማሪ ነበር፡፡
ማስታወሻ፡-5. በተገኘው አጋጣሚ አቋምን ማስረዳት
መርማሪዎቹ በተደጋጋሚ ስለተነገራቸው ብቻ የሚያምኑት ብዙ ነገር አለ፡፡ ኢህአዴግ ትግልላይ በነበረበት ወቅት ጭራቅ ተደርጎ ይሳል እንደነበረው አሁንም የነጻነት ትግል እያደረጉ ያሉትን ሰዎች እንደ ሰው በላዎች የሚቆጥሯቸውመርማሪዎች ብዙ ናቸው፡፡ በነዚህ መርማሪዎች ይህን ከተማ (አ.አ) ተወልዶ ያደገ ሰው ፖለቲካ ውስጥ ቦታ የለውም፡፡ ተደጋግሞ ሲነሱልኝከነበሩት ጥያቄዎች መሀል ይህ መንግስት ምን በድሎሃል (በግል) እንዴት እንደዚህ አይነት አቋም ልትይዝ ቻልክ? የሚለው እንደነበርአስታውሳለሁ፡፡ መልሴ ግን አጭር ነበር፡፡ ነጻነቴን ዋጋ እሰጠዋለሁ!!
ከምክትል ሳጅን መኮንን ጋር በነበረን ጊዜ የተረዳሁት ስለ አቋሞቼ በጥልቀት ማወቅ ቢፈልግምእንደ ጦር እንደሚፈራቸው ነው፡፡ ገና ማስረዳት ስጀምር ቶሎ ብሎ ‹ወደጉዳያችን እንመለስ፣ ዳግም ወደ አንተ ልትስበኝ ነው?› ይለኝነበር፡፡ ሌሎችም መርማሪዎች ተመሳሳይ ፍላጎት አይቸባቸዋለሁ፡፡ አንድ የማይረሳኝ ምሳሌ ከኢሜሌ ላይ የተገኘውን የዜና መጽሔት በተመስጦሲያነብ የነበር አንድ መርማሪ አለቃቸው ድንገት ቢሮውን ከፍቶ ሲገባ ወረቀቱን በድንጋጤ ወርውሮታል፡፡ ከዚህ መገንዘብ የቻልኩት እነዚህን በአንድ በኩል መረጃ የተደፈኑ ሰዎች ሌላኛውን ጎን ማሳየት በሌላ አማራጭ የማያገኙት መረጃ ምንጭ መሆን ስለሆነ በምርመራወቅት እንደ አንድ ዓላማ ሊወሰድ እንደሚገባ ነው፡፡
አልፎ አልፎ ከሌላ ቦታ የሚመጡ (ከደህንነት መስሪያ ቤት) መርማሪዎች ለመመለስ አደጋችየሆኑ ውስብስብ ጥያቄዎችን ከመጠየቃቸው ውጭ የሚጠየቁት ጥያቄዎች እዚህ ግባ የሚባሉ አይደሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ መርማሪዎች የሚጠይቋቸውጥያቄዎች ለራሳቸውም ግልጽ አይደሉም፡፡ ጥያቄዎችን የሚያበጁት ከጀርባ ሆነው ምርመራውን የሚመሩት አለቆቻቸው ናቸው፡፡ አልፎ አልፎለመመለስ አደጋች የሚመስሉ ጥያቄዎች ይነሳሉ፡፡ ለምሳሌ ሚያዝያ 27 ቀን (የአርበኞች ድል ቀን) ኢንስፔክተር አሰፋ እና አንድየደህንነት ባልደረባ ሆነው ባካሄዱብኝ ምርመራ ወቅት አንድ አስቸጋሪ ጥያቄ ተነስቶ ነበር፡-
የደህንነት ባልደረባው፡- ‹‹ዞን 9 ምን ማለት ነው?››
መልስ ፡- ‹‹ዞን 9 ማለት ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውጭ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን የተነጠቀ ታሳሪ ነው ለማለት የተጠቀምንበት ስም ነው፡፡››
‹‹እኔም የዞን 9 አባል (ነዋሪ) ነኝ ማለት ነው?››
‹‹አዎ!››
‹‹ጥሩ! ስለዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን የተነጠቀ ከሆነ መቼ እና እንዴት ነው ዞን9 ነጻ የሚወጣው?››
ይህ ጥያቄ ትንሽ ለመመለስ አስቸጋሪ ነበር፡፡ በርግጥ እንደማነኛውም ግለሰብ የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነቱን መቼ ያገኛል ለሚለው ጥያቄ የራሴ አስተያየት ቢኖረኝም በዚህ ምርመራ ወቅት ሀሳቤን በነጻነት ብናገር የሚያመዝነውአደጋው ነበር፡፡ ስለዚህ ማለት የቻልኩት ዞን 9 የሚለውን ተምሳሌታዊ ስያሜ አምነንበት ብንጠቀምም የዞን 9 ነዋሪዎችን ነጻ ማውጣትግን እንደ ግብ ያስቀመጥነው እና እንዲሳካም ኃላፊነት ወስደን የሰራንበት ጉዳይ እንዳልነበር ነው፡፡
አጠቃላይ የእስር ቤቱ የአያያዝ ሁኔታና የምርመራው አሰልቺነት በየዕለቱ መርማሪዎቹ ከሚነግሩኝየራሳቸው እውነት ጋር ተደማምሮ ሊያሸንፈኝ ዳር ዳር ብሎ ነበር፡፡ ነገር ግን በተባራሪየምንሰማቸው ጓደኞቻችን እና መታሰራችን የሚቆረቁራቸው ሰዎች የሚያደርጉት ሰላማዊ ሰልፍ እና የበይነ መረብ ዘመቻ ተጨማሪ የጥንካሬምንጭ ሆነውኛል፡፡ የማታዎቹ ምርመራዎች ለዚህ ምቹ ናቸው፡፡ ካስተዋልኩት የተረዳሁት የማታውን (የሌሊቱን) የምርመራ ጊዜ መርማሪዎቹለሚከፈላቸው ተጨማሪ ገንዘብ እና ስላመሹ መ/ቤቱ ለሚያቀርብላቸው ቆሎ እና ውሃ ካልሆነ በስተቀር አይፈልጉትም፡፡
በማታው ምርመራ ወቅት ቶሎ የመሰላቸት እና የኃይል እርምጃ ወደመውሰድ ይሄዳሉ፡፡ ብዙ ማውራት አይፈልጉም፡፡ ስለዚህአለቆቻቸው የሰጧቸው ጥያቄዎች ሲያልቁባቸው የተለያዩ ስፖርታዊ ቅጣቶች በማዘዝ በተንቀሳቃሽ ስልካቸው አማካኝነት ጨዋታ(game) ይይዛሉ፡፡ ወይንም ሌላ ክፍል ምርመራ ላይ ካለ ጓደኛቸው ጋር በኢንተር ኮም ወግ ይይዛሉ፡፡ በተመርማሪዎች ላይ ያላግጣሉ፡፡በማታዎቹ ምርመራዎች ወቅት ለሚነሱ ጥያቄዎች ረዘም ያሉ መልሶችን መምረጥ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ መልሶችንም በህገ-መንግስቱ ስለተፈቀዱመብቶች፣ ስለ ተቋማት ነጻነት አስፈላጊነት፣ እና መሰል ፖለቲካዊ ጉዳዮች ወደማብራራት ማጠጋጋት፣ ከተቻለ የመርማሪዎቹን ቀልብ ለመሳብእና ከሚወስዷቸው አላስፈላጊ የኃይል እርምጃዎች መከላከል ይቻላል፡፡
ማስታወሻ፡-6. አቤቱታ ማሰማት
የጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያ ፍርድ ቤት በሚወሰዱበት ጊዜ ያለውን አጋጣሚ በሚገባ መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ በተለምዶ ፍርድቤት በፖሊስ የአያያዝ በደል ተፈጽሞብኛል ብሎ የሚያመለክት ሰው ከፍርድ ቤቱ መልስ ተመልሶ ማዕከላዊ እንደሚገባ ስለሚያውቅ የባሰአደጋ ለመቀነስ በሚል አቤቱታ ከማቅረብ ሊቆጠብ ይችላል፡፡ ነገር ግን አቤቱታውን አቀረበም አላቀረበም ሰብዓዊ መብቱን ከመረገጥአይድንም፡፡ ልዩነቱ የሚሆነው የፍርድ ቤቱ መዝገብ ላይ የመብት ጥሰቱ ተመዝግቧል ወይስ አልተመዘገበም የሚለው ነው፡፡
እዚህ ላይ የምመክራቸውን ነገሮች ያለማድረግ ቁጭት በእኔ ብቻ ሳይሆን ብዙ ታሳሪዎች ላይ ያስተዋልኩት ነው፡፡ ያላደረግሁትንአድርጉ ብሎ የመጠየቅ ይሉኝታም ጽሁፉን ልጻፍ ወይስ ይቅርብኝ ብዬ እንዳንገራግር አድርጎኝ ነበር፡፡ ውስጤ ከሚብላላ ግን ጽፌውአንብቦ ቢያንስ አንድ ሰው የተለየ መንገድ ተከትሎ ጉዳት ቢቀንስ የተሻለ ነው የሚለው ሀሳብ የተሻለ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ ሌሎቹምጓደኞቼ ተመሳሳይ መንገድ አልፈዋል፡፡ የነሱንም የምርመራ ሂደት ይጽፉታል የሚል እምነት አለኝ፡፡ እስከዛው ድረስ መታገስ ያልቻለየሀገር ውስጥ ነዋሪ ግን ወደ ቂሊንጦ ጎራ ብሎ ከራሳቸው አፍ ጠይቆ መረዳት ይችላል፡፡ እኔ ቀረኝ የምለው ነገር ካለኝ በሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ፡፡
ማስታወሻ፡-7. የማዕከላዊ ቤቶችን (ክፍሎች) ይተዋወቁ
ማዕከላዊማዕከላዊ
በግቢው ውስጥ ሶስት የእስረኛ ማቆያ ቦታዎች አሉ፡፡ በተለምዶ ጣውላ ቤት፣ ሳይቤሪያ እና ሸራተን በመባል ይታወቃሉ፡፡ጣውላ ቤት አምስት ክፍሎችን በተርታ የያዘ ሲሆን የምርመራ ቢሮዎች ያሉበት ህንጻ ጀርባ ምድር ላይ ያሉ ክፍሎች ናቸው፡፡ እኛ ማዕከላዊታስረን በነበርንበት ወቅት ሶስቱ ክፍሎች ለሴት ተጠርጣሪዎች ማቆያ ሲሆኑ ቆርቆሮ መከለያ ተደርጎለት፣ ደግሞ የተቀሩት ሁለቱ ምስክርለመሆን የተስማሙ ወንድ ተመርማሪዎች ማቆያ ነው፡፡ ማሂ እና ኤዶም ከሶስቱ ክፍሎች በአንደኛው ከሌላ ሴት ታሳሪዎች ጋር እንዳይገናኙሁለቱ ብቻ ተለይተው ነበር፡፡ ጣውላ ቤት ፊት ለፊት የክፍሎቹ ወለል ጣውላ መሆኑ ነው ጣውላ ቤት የሚል ስያሜ ያሰጠው፡፡ ይህንንማቆያ ቤት አልፎ አልፎ ሂልተን በማለት የሚጠሩት ሰዎች ገጥመውኛል፡፡
ሳይቤሪያ የሚባለው የእስረኛ ማቆያ በቅዝቃዜው ምክንያት ነው ስሙን ያገኘው፡፡ ይህ ባለአንድ ፎቅ ህንጻ ምድር ላይየሚገኘው ማቆያ ቦታ በረጅም ኮሪደር የተከፈለ ሲሆን በግራና በቀኝ ከ2 ቁጥር እስከ 10 ቁጥር የተለጠፈባቸው አምስት አምስት ክፍሎችአሉት፡፡ 8 ቁጥር ከተለጠፈበት ውጭ ሌሎቹ ወጥ ክፍሎች ሲሆኑ 8 ቁጥር የተለጠፈበትን በር ተከፍቶ ሲገባ ግን ሌሎች ራሳቸውን የቻሉአራት ክፍሎች አሉት፡፡ የበለጠ ቅጣት እንዲቀጣ የሚፈልጉት ተመርማሪ እነዚህ ሁለት ሜትር በሁለት ሜትር የሆነ ጨለማ ክፍል ውስጥያስሯቸዋል፡፡ ሳይቤሪያ የምርመራ ግለቱ እስኪሰክን ድረስ ተመርማሪዎች የሚቆዩበት ቦታ ሲሆን ሁሉም ክፍሎች ከኤሌክትሪክ መብራትውጭ ምንም አይነት ብርሃን አይደርሳቸውም፡፡ የክፍሎቹ ግድግዳዎች ወለሉና ጣራው ከኮንክሪት የተሰራ ነው፡፡ ቀኑን ሙሉ ከውጭ ተዘግቶየሚውለው ክፍል በቀን ለሶስት ጊዜ ያክል ይከፈታል፡፡
ሳይቤሪያ ውስጥ ያሉ ክፍሎች ጠዋትና ማታ በተራ በተራ እየተከፈቱ ተመርማሪዎች በጋራ ወደሚጠቀሙት ባለስድስት ክፍልሽንት ቤት እና መታጠቢያ ቤት እንዲሄዱና ተጠቅመው እንዲመለሱ ለደቂቃዎች ፈቃድ ያገኛሉ፡፡ ለሌሎች ጥቂት ደቂቃዎች ደግሞ የፀሐይብርሃን ለማግኘት ይፈቀድልን ነበር፡፡ ፀሐይ የምናገኘው በጣውላ ቤት እና በህክምና ክሊኒኩ መሐከል ባለ ክፍት ቦታ ላይ ነበር፡፡ጣውላ ቤት ያሉት ክፍሎች በር ክፍት ስለሚሆን ከማሂ እና ኤዶም ጋር በዓይን እና በምልክት ብቻ እናወራ ነበር፡፡ የሳይቤሪያ ክፍሎችበየተራ በሳምንት አንድ ቀን የሚጸዱ ሲሆን ባለችን መታጠቢያ ጊዜም የምናገኘው በነዚህ ቀናት ብቻ በሳምንት አንዴ ነው፡፡
ሸራተን ለ12 ሰዓት ፀሐይ የሚገኝበት፣ ቲቪ የሚታይበት እና የሽንት ቤት እና የመታጠብ ፍላጎት ያለው ሰው የፈለገውንማድረግ የሚችልበት ቦታ ነው፡፡ የምርመራው ሂደት ሲጠናቀቅ ቀለል ባለ ጉዳይ የሚመረመር ሰው ወይንም ደህና ባለስልጣን ዘመድ ያለውሰው ሸራተን ሆኖ የማዕከላዊ ቆይታውን ያጠናቅቃል፡፡
በመጨረሻም አንድ እብሪተኛ መርማሪ በተናገረኝ ንግግር ማስታወሻየን ላጠናቅቅ፡፡ እንዲህ ነበር ያለኝ፣ ‹‹መንግስትብዙ ዓይኖች እና ጆሮዎች አሉት፡፡ እናንተ ደግሞ ስታወሩ የነበረው በእኛው ስልክ፣ ከሀገር ስትወጡ የነበረው በእኛው በሀገራችን አየር መንገድ እና በቦሌ በኩል ነበር፡፡ እያንዳንዱ እንቅስቃሴያችሁን መረጃ አለን፡፡ አንተ አሁን እየደበቅህን ነው፡፡ ይህ ደግሞ ለአንተ አይጠቅምም፡፡ እኛ ምርጫ እንሰጥሃለን፡፡ ሕይወትህን ወደብርሃን መውሰድ የምትፈልግ ከሆነ ወደዚያው እንመራሃለን፡፡ አይ አልፈልግም የምትል ከሆነ ደግሞ መውጣት ወደማትችለው ድቅድቅ ጨለማ እንከትሃለን፡፡ ምርጫው የአንተ ነው፡፡››


Leave a Reply

Your email address will not be published.

9 + 2 =