ዓርብ 18 ዲሴምበር 2015

ልጆች በጥይት አይቀጡም፣ የትኛው መንግስት ዛሬ ተማሪዎችን በጥይት ይደበድባል?

ልጆች በጥይት አይቀጡም፣ የትኛው መንግስት ዛሬ ተማሪዎችን በጥይት ይደበድባል?

ዛሬ የዓለም መሪዎች በፓሪ ፈረንሳይ ስለ ዓለማችን ያየር ንብረት ችግሮች እየመከሩ ነው።ችግሩ ደግሞ ቀድሞ ሰለባ ያደረገው ደሃ አገሮችን መሆኑ ግልጽ ነው።ኢትዮጵያም አንድዋ ናት።ከኢትዮጵያ ህዝብ አስራ አምስት ሚሊዮን ለራብ መጋለጡ መደበቅ የማይቻል እውነት ነው።ወያኔ ሃላፊነት ያለው መንግስት ቢሆን እዲህ ጊዜ የማይሰጥ ችግር ላይ ያተኩር ነበር።የአስራ አምስት ሚሊዮን ህዝብ ለራብ መጋለጡን የአውሮፓ ህብረት ጉዳዬ ብሎ ሲመክርበት ህወሃት ይህን ችግር ከፖለቲካ ተቃውሞ መለየት ተስኖት ከውይይቱ እንኳን ለመሳተፍ አልመረጠም።ካአየር ንብረት ችግሩ እጅግ የከፋው የአስተዳደር ጉድለቱ የሚፈጸመው ግፍ ነው በኢትዮጵያችን።ኢትዮጵያ መንግስትዋ ሽብርተኛ ያየር ንብረት ችግሯ በጣም ፈታኝ የሆነበት ዘመን ዛሬ ነው።ያየር ንብረት ችግር ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ልጆችዋን እየገበረች ነው።ልጆች በጥይት ይቀጣሉ።የህወሃት ግፍ ይህ ነው።TPLF killing Oromo students
ህወሃት የዛሬውን አይበለውና የትግራይ ህዝብን አታግልለታለሁ ሲል “ሃረሽታይ ሸቃላይ” ወይም አርሶአደር ላብአደር ይል ነበር። ለህዝብ እንደቆመ ሁሉ።ዛሬ “መሬት ላራሹ”ን ተረተረት አድርጎ የኢትዮጵያን አርሶ አደር መሬት ንብረቱን ቀምቶ እያራቆተው ይገኛል። ከአርሶ አደሩ አብራክ የወጡትን ልጆቹን ለአርሶ አደሩ በደል ቢነሱ በጥይት ይደበድባቸዋል። የዓለም ዜና ይህን ባያተኩርበትም ዛሬ የኢትዮጵያ ሁኔታ በከፋ መጠን እየተናጋ መሆኑን ማንም ሊክድው አይችልም።በዓለም ተበትነን ያለነው ዜጎች በየሰዓቱ የምንከታተለው ይህንኑ ነው።
ማንም ህብረተሰብ ቀጣዮን ትውልድ ያስተምራል።ፈደል ተቆጥሮ፤ሂሳብ ተምሮ፤ ቋንቋ ሰዋስው አጥንቶ፤ሳይንስን ተቃምሶ የህብረተሰብ ጥናት ታሪክንም ለካክፎ ወደከፍተኛ ትምህርት ማምራት አለ።ከፍተኛ ትምህርት አንድ ህብረተሰብ ለወጣት ዜጋው የሚያቀርበው ትልቁ የውቀት ገበታ ነው።አላፊነት የሚሰማው አገሩን የሚወድ ትውልድ የሚዘጋጅበት፤ራስንም ዓለምን ለማወቅ የሚሞከርበት የድሜ ዘመን የሚልፍበት ነው ማለት ስተት አይሆንም።በከፍተኛ ትምህርት ቅጥር ውስጥ እማይጠየቅ የለም።እማይፈተን የለም። ሁሉም በነጻነት ይፈተሻል።ይሞከራል።ጉልበት፤ ስልጣን አለው ተብሎ የሚፈራ የለም።በከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሁሉም ይተቻል።ይጠናል።ይተነተናል።የበደለም ይኮነናል።ለውነት ለፍትህም ቆምን ይባላል።ዛሬ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለተቃውሞ ቢወጡ ለአገር ለወገን ብለው ነው።ተቃወሞ ወግ ነው።ልጆች ስለተቃወሙ በጥይት አይቀጡም።የትኛው መንግስት ዛሬ ተማሪዎችን በጥይት ይደበድባል ? ፈሪው ህወሃት ብቻ!ጨካኙ ህወሃት ብቻ!ከፖለቲካ ድርጅትነት ዘቅጦ የእጽ ሻጭ ካርቴል የነብሰገዳይ ጥርቅም ዓይነት የሆነው ህወሃት ብቻ!
ህወሃት መሩ መንግስት ከፍተኛ ትምህርት ቅጥር ግቢን የሞት አውድማ ያደረገው ገና ድሮ ነው። የመለስ ዜናዊም “ሌጋሲ” “ትሩፋት” አንዱ ይህ ነው። ሰሞኑን በሀረር ሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የሆነው ዘግናኝ ነው። በሌሎቹም ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁ። የህወሃት አገዛዝ ከጅምር አካሄዱ ይሄው ጥፋት ነበር።በዘውዱ ስርዓት ፖሊስ ዩንቨርሲቲ ቅጥር ሲገባ እጅግ ይኮነን ነበር።ወታደራዊ ደርግም ወጣቱን በቀይ ሽብር ቢጨፈጭፍም እዲህ እንደ ህወያት መሩ መንግሰት ዩንቨርሲቲውን የጦር ቀጠና አላደረገውም ነበር።ህወያት መሩ መንግሰት ቁንጮ ላይ ያሉት ጥራዝ ነጠቅ የዛሬ ተራ ቀማኞች “መሬት ላራሹ” ካለው ትውድ እንደመር ይሉ ይሆን ?ያትውልድ ህወያት የሚባል ጉድ ትቶ አለፏል።ግን የኢትዮጵያ ተማሪዎችን አኩሪ የትግል ታሪክን ህወሃት አይሽረውም።እዚህ ቀጣይ የሞት ሂደት ውስጥ የከተተው የቀማኛ ቡድንን አስወግዶ የዜግነት ክብር የነገሰባትን፤እኩልነት የሰፈነባትን ነጻ ኢትዮጵያ ከህዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሀይሎች ጋር በመሆን ይመሰርታል።እልሙ ኢትዮጵያ! ናት።ድል የሚገኘው በህብረት ትግል እንደሆነ ይገነዘባል።
የኢትዮጵያ ተማሪዎች ቀድሞ ሲነሱ ኢትዮጵያ! ነው ያሉት።”መሬት ላራሹ” የተባለው ለትግራዩ፤ለኦሮሞው፤አማራው፡ለአፋሩ፤ለሱማሌው ለደቡቡ ለሁሉም ነው፤የህወሃት የአዲሱ አገዛዝ አናት ላይ መሆን እንጂ ”መሬት ላራሹ” ዛሬም ፍቺ ያላገኘ የዴሞክራሲ ጥያቄ ነው።የምናየውን እልቂትን የሚገፋው ምክንያት ይሄው ነው።”አዲስ ንጉስ እንጂ ለውጥ መቼ መጣ?” ቴዲ አፍሮ ጨርሶታል። እኩይ ንጉስ ነው የመጣ!
በኦሮሚያ ክልሎች የሆነው ከላይ ያልኩት ነው። የከፍተኛ የትምህርት ገበታን የሞት አውድማ ማድረግ ነው ።ተማሪዎች ልክ ድሮ የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንደታገሉት ሁሉ “መሬት ላራሹ” ብለው ዛሬም እየታገሉ ነው።የወገንን መሬት “ኢንጉርጉረምቱ!” አይሸጥም ! ነው ያሉት።ጥያቄው የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ሁሉ ጥያቄ ነው።በተለይ የኦሮሚያ ክልል ብቻ ብሎ የሚፈረጅ አይደለም።የአፋሩ፤የጋምቤላው በደል ከአማራውና ከኦሮሞው የሚለይ አይደለም።
የገጠመንን ችግር የከልል ማድረግ የኢትዮጵያን ሁኔታ ጠንቅቆ አለመረዳት ነው።የልጆቻችን ተስፋም እመረቃለሁ፤ ለማዕረግ እበቃለሁ እንጂ እሞታለሁ መሆን አይገባውም። የልጆቻችን ሞት የኢትዮጵያዊ ወገናችንም ሁሉ ሞት ሊያገሸግሸን ይገባል።ኢትዮጵያ ተበደለች። ልጆችዋን ገበረች።ተምሬ ወግ ማእረግ አይባታለሁ የምትባለዋን ኢትዮጵያን የምናይበት ጊዜው እሩቅ አይሆንም።የሚጠይቀው ህብረታችንን ብቻ ነው። ህወሃት መሩን መንግስት ተባብረን እንሸኝ።ከዚህ ወዲያ ድርድር የለም።
የኦሮሚያ ክልልን መዝረፍና ማስዘረፍ የአማራውን ክልል የሞት፤የቃጠሎ የእስራት ቀዬ ማድረግ በሁለቱም የኢትዮጵያ አካሎች ላይ የዘር ማጥፋት ወጀልን ወደ መፈጸም የሚቀርብ ክፋት ነው።የጎንደር ህዝብ በደል የኢትዮጵያ በደል ነው።በተለይ አጠገቡ ለሆኑት የትግራይና የወሎ ህዝቦች በደል ነው።ጎንደርን መሸንሸን እንደምን ይሆናል ? የኢትዮጵያ አንድነት ምንጭ መሰረቱን ?! የወልቃት አልበቃ ብሎ ቅማንትን! ከወንድም እቶቹ ማጋጨት ?ወሰን ድንበር ለባዕድ ለመለገስ ሸር ጉድ? አዲሳባን እናስፋ በማለት ዝርፊያ አሁን ይቁም! ራብም እየፈጀን ልጆቻችንም እየሞቱ እየተቃጠልን እየደማን እስከ መቼ? ወገኖቼ።ዘረፋው እስከመቼ? ምን እንጠብቃለን።
ለደሃው የኢትዮጵያ አርሶ አደር አለኝቶቹ ዛሬ በዳያስፖራ የምንገኝ ነን!
በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የህወሃት ገዳዮች የሚፈጽሙትን በህብረት እናውግዝ!
ኢትዮጵያን ከክፉ መከራ አላህ የሰውራት! ሁላችንም እየጸለይን እንታገል!

ለወያኔ ድርጊት፣ ምን ስም እናውጣለት (ይገረም ዓለሙ)

ለወያኔ ድርጊት፣ ምን ስም እናውጣለት (ይገረም ዓለሙ)

ይገረም ዓለሙ
ወገንን ጨፍጫፊ ቆዳው የነጣ ነው
በአበሻ የሚጨክን ፈረንጅ ብቻ ነው፤
እያለ የሚያስብ የዋህ ፍጡር ማነው
ጨፈጫፊ ከሆነ አበሻም ጣሊያን ነው
እንቶኔም በተግባር ሲኞር እንቶኔ ነው፤
Police brutality in Ethiopia
በየግዜው እየከፋ የሄደውን የወያኔ አረመኔነትና የሀገራችንን ጉዞ ወዴትነት ሳስብ ትውስ ያለችኝን ይህችን ስንኝ ወደ ማስታወሻየ ገልብጬ ያኖርኳት በ1980ዎቹ መጨረሻ ግድም ለንባብ ይበቁ ከነበሩት መጽሄቶች ከአንዱ ነው፡፡ ወያኔ ዴሞክራት መስሎ ለመታየት በሞከረበትና ትክክለኛ ማንነቱ ገሀድ ወጥቶ ብዕርን ከጠመንጃ አስበልጦ መፍራት ባልጀመረበት በዛ ወቅት እንዲህ የጻፉት ሰው ዛሬ በህይወት ካሉ ምን ሊሉ እንደሚችሉ መገመት ይቸግራል፡፡
ወያኔዎች ደርግን በጨፍጫፊነት በማውገዝ ዛሬም ድረስ ፈሺስት ናዚ ወዘተ በማለት ይገልጹታል፡፡ በዘመነ ደርግ የተፈጸመውን ቀይ ሽብርም ለአንድ ሰሞን የፖለቲካ ፍጆታ ሊጠቀሙበት ሞክረዋል፡፡ ግን ካወገዙት ተግባር ተምረው ከተጸየፉት ድርጊት ርቀው ሊገኙ አልቻሉም፡፡ በርግጥም ከጅምሩ ስለ ቀይ ሽብር የነበራቸው አያያዝ ሊማሩበት ሳይሆን ሊያደናግሩበት፤ ለተበዳዮች ፍትህ ሊያስገኙበት ሳይሆን ጥላቻን ሊያነግሱበት እንደነበረ መለስ ብሎ በማስታወስ ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ከቀይ ሽብር ቢማሩ ኖሮ ራሳቸው ያቋቋሙት የቀይ ሽብር ኮሚቴ ይዞት የነበረውን “ያለመቻቻል ፖለቲካ ሰማዕታት፣መቼም እንዳይደገም” የሚለውን መርህ ተግባራዊ ባደረጉና እንዲህ የለየላቸው ጨፍጫፊ ባልሆኑ ነበር፡፡
የቀይ ሽብር ነገር ለወያኔ የፖለቲካ ካርድ በነረበት ወቅት የቀይ ሽብር ኮሚቴ ባዘጋጀው አንድ የውይይት መድረክ ላይ የጥናት ወረቀት ያቀረቡት ፕ/ር ባህሩ ዘውዴ “…የፖለቲካ ልዩነቶችንም በተመለከተ አንዱ ወገን ምንግዜም ቢሆን ፍጹማዊ እውነትን ሊታደል እንደማይችል ተገንዝቦ የሌላውን ወገን ሀሳብ እህ ብሎ ማዳመጥ መቻል ይኖርበታል፡፡ የተቀዋሚ ወገን አየለ ብሎ ቃታ ለመሳብ መጣደፍ ዞሮ ዞሮ ሀገርን በብርቱ የሚጎዳ መሆኑን ከ « ቀይ» ሽብር ያተረፍነው ትልቁ ትምህርት ነው” ብለው ነበር፡፡ ነገር ግን ወያኔዎች ቀይ ሽብርን ያራገቡት ፖለቲካ ሊቆምሩበት እንጂ ሊማሩበት ያለመሆኑን ውለው ሳያድሩ በጀመሩት የሁሉም ነገር መፍትሄ ከጠመንጃ ይመነጫል አይነት ተግባራቸው አሳይተውናል፡፡
ሌላው ተናጋሪ የነበሩት ዶ/ር የራስ ወርቅ አድማሴ ባቀረቡት ጽሁፍ ደግሞ “ከኛ ትውልድ ስህተት በመማር የልጆቻችንን ትውልድ ከፖለቲካ ግድያ፣ከዘር ማጥፋት ፍጅትና ከስጋትም ጭምር ነጻ በሆነችና ፍትህ በነገሰባት ኢትዮጵያ እንዲኖሩ እንመኛለን፡፡ ይህን ምኞታችንን እውን ካደረግን ደግሞ እሱ ጊዜ የማይሽረውና የማያደበዝዘው ዕውነተኛው የሰማዕታት መታሰቢያ ይሆንልናል፡፡”» በማለት ዋናው ቁም ነገር የድንጋይ ሀውልት ማቆሙ ሳይሆን ካለፈው ተምሮ መሰል ጥፋት እንዳይደገም ማድረጉ እንደሆነ ነበር የገለጹት ፡፡ግና አንደ አለመታደልም ሆነና ወያኔን ሀይ የሚለውም ጠፋና ይሄው ዛሬ ድረስ ስጋቱም ፍጅቱም እንዳለ አለ፡፡
ባለፉት ሀያ አራት ዓመታት ወያኔ ከምንይልህ ቤተ መንግሥት ሆኖ የፈጸማቸው ኢ- ሰብአዊ ተግባሮቹን ለታሪክና ለትውልድ ፍርድ ትተን ዛሬም በእብሪትና በማን አለብኝነት የሚፈጽማቸውን ተግባራት ስናስተውል ጨፍጫፊ ከሆነ ሀበሻም ጣሊያን ነው የሚያሰኙ ናቸው፡፡ታዲያ እኒህን ከእለት እለት እየባሱ የመጡ አረመኔያዊ ድርጊቶቹን ምን ስም አንስጣቸው፡፡ ይመጥ አይመጥነው ባይታወቅም አንድ ሰሞን አንዳንድ ሰዎች ጥቁር ሽብር ማለት ጀምረው ነበር፡፡
ከወራት በፊት አቶ ኤፍሬም ማዴቦ “አይኔ እያየስ እዚህ ውስጥ አልገባም, መሠረት ሙሴ” በሚል ርዕስ ባስነበቡን ጽሁፍ ስሙ የተጠቀሰው ወጣት ከሌሎች ሁለት ወጣቶች ጋር ጎነደር መተማ ላይ ተያዘ፡፡ ሁመራ ተወስደው ጫካ ውስጥ ሊረሸኑ ጉድጓድ አፍ ላይ ቆመው ገዳዮቹ አንደኛውን ወጣት በጥይት መትተው ወደ ጉድጓድ ሲከቱት አይኔ እያየስ እዚህ ውስጥ አልገባም ያለው መሰረት እግሬ አውጪኝ ብሎ ሮጦ አካሉ በጥይት ቢነዳደልም አምልጦ በሻዕቢያ ወታደሮች እጅ መውደቁንና ታክሞ ድኖ ግንቦት ሰባትን መቀላቀሉን ነግረውናል፡፡( ይህን አንብበን ዝም ማለታችን ራሱ አስገራሚ ነው)
ወጣቱ በፈጣሪ ቸርነት በማምለጡና አቶ ኤፍሬምንም በማግኘቱ የአይን ምስክርነቱን ሊሰጥ ቻለ፡፡ ባይሆን ኖሮ ይኑሩ ይሙቱ ሳይታወቅ ቤተሰብም እርሙን ሳያወጣ ጫካ እንደተጣሉ ይቀሩ ነበር፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በየደረጃው ባሉ ዘመንኞች እየተረሸኑ በጅምላ የተቀበሩና በየጫካው የተጣሉ ዜጎችን ቤት ይቁጠራቸው ማለት ይቻላል፡፡ አንድ ቀን ግን መጋለጡ አይቀርም፡፡
እዛው ጎንደር ውስጥ የወንድሞቹ በረሀ መግባት በሰላም ለሚኖረው ክብሩ አሰፋ ወንጀል ሆኖ 18 ዓመታት አስፈርዶበት በጎንደር ወህኒ ቤት ስድስት ኣመታትን ካሳለፈ በኋላ ከእስር ቤት ተወስዶ መረሸኑን ከአርበኞች ግንቦት ሰባት መግለጫ አንብበናል፡፡ይህም ወያኔዎች ጠላታችን የሚሉትን ሰው አስረው እንኳን እንቅልፍ የማይወስዳቸውና ካልገደሉ የማይረኩ መሆናቸውን የሳየ ነው፡፡ በዚህ መልክ የተረሸኑ ወገኖቻችንስ ምን ያህል ይሆኑ?
ከሁለት ዓመት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ ከስድስት ኪሎ ወደ ፈረንሳይ የሚሄደው መንገድ ሲሰራ ሶስተኛ ሻለቃ በመባል ይታወቅ የነበረውና ወያኔ ስሙን እየቀያየረ የሚጠቀምበት የጦር ሰፈር ጫፉ ላይ አጥሩ ፈርሶ ሲቆፈር የቅርብ ግዜ አስክሬን ከነተጠቀለለበት ብርድ ልብስ መገኘቱ ይታወሳል፡፡ በማህበራዊ ድረ ገጽም ምስሉ ተለቆ ለአንድ ሳምንት መነጋገሪያም ሆኖ ነበር፡፡ (ንዴት ቁጣችን፣ ተቃውሞ ፉከራችን ከአንድ ሳምንት አይዘል አይደል!) ሳይታሰብ በመንገድ ስራ ቁፋሮ ምክንያት ለእይታ የበቃው ያ የወገን አጽም የወያኔ የጦር ካምፖች ለወታደራዊ ተግባር ብቻ ሳይሆን ታፍነው ለሚሰወሩ ዜጎች ማሰቃያ መግደያና መቀበሪያነትም የሚያገለግሉ መሆናቸውን ያጋለጠ ነው፡፡ በዚህ መልክስ ስንት ወገኖቻችን በአረመኔዎች እየተገደሉ በየቦታው ተቀብረው ይሆን; ጠያቂ ጠፍቶ ጯሂ አልተገኝቶ ሆኖ እንጂ ቁፈራው ሰፋ ተደርጎ ቢቀጥል ብዙ ጉድ በተጋለጠ ነበር፡፡
የፖለቲካ ትርፍ አገኛለሁ ብሎ በደርግ እየተገደሉ በየቦታው የተቀበሩ ወገኖቻችንን አጽም እያወጣና በቴሌቭዥን እያሳየ ሲያስለቅሰንና ሲያላቅሰን የነበረው ወያኔ እሱ በተራው ሀያ አራት ዓመት ሙሉ አስሮ አሳቃይቶና ገድሎ ሊረካ አልቻለም፡፡ መታሰር መሰቃየትና መገደል በቃን ብለን ካላመረርንና ካልተባበርን አለበለዚያም ለወያኔ ሰጥ ለጥ ብለን ካላደርን በስተቀር ወያኔ ከዚህ አድራጎቱ መቼም የሚገታ አይመስልም፡፡ ግና ዘላለማዊ ምድራዊ ኃይል የለምና አንድ ቀን የጨለመው ሲበራ ህሊናቸው ፋታ ነስቶአቸው ወይንም ህግ አስገድዷቸው ወያኔ በዘመነ ሥልጣኑ እየገደለ በየቦታው ስለቀበራቸው ኢትዮጵያውያን የአይን እማኝነታቸውን የሚሰጡ ሰዎች መኖራቸው አይቀርም፡፡
ይሄው ሰሞኑን ደግሞ በየመድረኩ ስለፍትህ ስለ መልካም አስተዳደር ተቃውሞን በሰላማዊ መንገድ መግለጽ ስለመቻል ወዘተ እየደሰኮሩ በተግባር ግን በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ባቀረቡና ተቃውሞ ባሰሙ ወጣቶች ላይ ነብሰ ገዳይ ወታደሮቻቸውን አሰማርተው እያስደበደቡ እያሳሰሩና እያስገደሉ ነው፡፡ ለሀያ አራት አመታት በስልጣን ለመቆየት የቻሉት በማናቸውም ወገን የሚነሳን ማናቸውንም ጥያቄና ተቃውሞ በእስር በድብደባና በግድያ ጸጥ በማሰኘት በመሆኑ ሌላ ለጥያቄ መልስ መስጫ ዘዴም ሆነ ተቃውሞን ማስተናገጃ መንገድ አያውቁም፡፡
የአረመኔነታቸው ክፋት ጎንደር እስር ቤት ተቃጥሎ እስረኞች ህይወታቸውን ለማትረፍ ሲሮጡ እየተኮሱ ገድለዋል፡፡ ያለህበት ቤት ሲቃጠል አይንህ እያየ ዝም ብለህ ተቃጠል የሚሉ ነው የሚመስለው፡፡ እንደው እነዚህ ከእሳት የሚያመልጥን ዜጋ ተኩሰው የሚገድሉ ነብሰ በላዎች ከምን አይነት ማህጸን የተፈጠሩ ይሆኑ! ወይስ ወያኔዎች ሲያሰለጥኑዋቸው ከምግብ ወይንም ከሚጠጣ ነገር ጋር ቀላቅለው የሚሰጡዋቸው ከሰውነት ወደ አንስሳነት የሚቀይር፣ ሰዋዊ አስተሳሰብን አደድቦ ህሊና ቢስ የሚያደርግ ነገር ይኖር ይሆን፡፡
ወያኔዎች የአረመኔነታው ክፋትና የንቀታቸው ብዛት አንድም ገደሉ መቶ ለአፋቸው ይህል እንኳን በተፈጠረው ነገር እናዝናለን አይሉም፡፡ እነርሱ የሚያውቁት በሟች ቁጥር ላይ መሟገት ነው፡፡ ሰሞኑን የምንሰማውም ይህንኑ ነው፡፡
በሰላም ተቃውሞ በሚያሰሙ ( ቢቢስ ድንጋይ ይወረውሩ ይሆናል) ወጣቶች ላይ እንዲህ በየግዜው ግድያ የሚፈጽሙት ወያኔዎች ደርጎች ላይ እንደሆነው በአዲስ አበባ ከተማ በትላልቆቹ ባለሥልጣኖች ላይ ቢተኮስባቸው፣ ከመካከላቸው ቢቆስልና ቢሞትባቸው ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ መገመት አይከብድም፡፡ አብርሀ ደቦጭና ሞገስ አስግዶም የጣሊያኑን ጀነራል በቦምብ ካቆሰሉ በኋላ ጣሊያኖች በአዲስ አበባ የፈጸሙት ጅምላ ፍጅት መቼም የሚረሳ አይደለም፡፡ ወያኔዎች ከእስከዛሬ ተግባራቸው እንዳወቅናቸው ከመካከላቸው አንድ ሰው ቢገደል ወይንም ቢቆስል ተመሳሳይ ተግባር ከመፈጸም ወደ ኋላ እንደማይሉ ፡፡ ታዲያ ይህን በቀይ ሽብር ለተጨፈጨፉ ወገኖች ሀውልት አቁሞ ጭፍጨፋ የሚፈጽም አረመኔ ቡድን ለእሱም ሆነ ለድርጊቱ ምን ስም እናውጣለት፡፡

የኦሮሞ ህዝብ ብሶት፥ ወደ የጋራ ነጻነት

የኦሮሞ ህዝብ ብሶት፥ ወደ የጋራ ነጻነት


“ከአዲስ አበባዉ የእርሻ መሬት እስከ አሜሪካዊ ቤተ መንግስት፥መብትን የማስከበር ጣምራ ሒደት!”
በአሜሪካዉ ቤተ መንግስት እና በዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የኢትዮጵያ መንግስት በሰላማዊ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ የሚያደርገዉን ግድያ፣ድብደባ፣ እስር፣ወከባና ማፈናቀልን በመቃወም በተደረገዉ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በመገኘት ሳዲቅ አህመድ ያዘጋጀዉ ልዩ ፕሮግራም።

Washington DC protest against the killing of Oromo students

ረቡዕ 11 ኖቬምበር 2015

ረሃቡና እድገታችን፡ ተጠያቂው ማን ነው? (በአብዱረዛቅ ሑሴን)

ክፍል አንድ፡ እድገቱን የጎሪጥ!
ምስራቅ አፍሪካ ላይ በዚህ አመት 22 ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች በረሃብ እንደሚጠቁና ከዚያም ውስጥ 68% (15 ሚሊየኑ) ከኢትዮጵያ እንደሚሆን የተባበሩት መንግስታት እየተናገረ ይገኛል፡፡ መጀመሪያ ምንም አይነት ስጋት እንደሌለ፣ ከዚያም 4 ሚሊየን ቆየት ብሎ ደግሞ 8 ሚሊየን ህዝብ ተጠቂ እንደሆነ ዘግይተው ላመኑት ሹማምንቶቻችን ከፍተኛ ዱብ እዳ እንደሚሆንባቸው አያጠያይቅም፡፡ የሀገርም ውስጥ ይሆን አለም አቀፉ ህብረተሰብ አንድ ተመሳሳይ ጥያቄ እንደሚጠይቅ ይጠበቃል፡- ‪ላለፉት‬ አስር አመታት በሁለት ዲጅት ያደገ ኢኮኖሚ እንዴት የህዝቡ 15% በረገብ ሊጠቃ ቻለ?15 million people in need of food aid
ለዚህ ጥያቄ የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትራችን ያላቸውን የኢኮኖሚክስ እውቀት ተጠቅመው ቢያንስ መልስ ሚመስል ነገር ይሰጡን እንደነበረ እርግጠኛ መሆን ይቻላል፡፡ እሳቸው ከነጎዱ ወዲህ ግን ‪‎ወይ‬ አያውቁ፣ ወይ የሚያውቁትን አያመጡ፣ ወይ አይወጡ; ሆኖብን እንጨት እንጨት የሚል የወረዱ ትንታኔዎቻችን የሚሰጡን ከጠቅላይ ሚንስተሩ እስከ ኮሚኒኬሽን ሚንስትሮቻቸው ድረስ ያሉ ባለስልጣናት ግራ አጋብተውናል፡፡ የዋጋ ግሽበት ፣የኑሮ ውድነቶችን እና የመሰረታዊ አገልግሎት አቅርቦት እጥረትን የመሳሰሉ ችግሮች ሲነሱ አቶ መለስ በተደጋጋሚ የእድገታችን ውጤት እንደሆነ ለኛም ለተተኪዎቻቸውም ሲነግሩን ነበር፡፡ ይህ ምላሽ መንግስትን ከተጠያቂነት ባያስመልጥም በከፊልም ቢሆን ኢኮኖሚክሲያዊ መሰረት ያለው ምሁራዊ ትንተና ሊባል የሚችል ነው፡፡ ከሳቸው መሞት በኋላ የመጡ መሪዎቻችን ለተመሳሳይ ጥያቄዎች ተመሳሳይ መልስን ሲሰጡን ቆይተዋል፡፡ ራእያቸውንም ብቻ ሳይሆን ለጥያቄዎች የሰጡትንም መልሶቻቸውን እያስቀጠሉም ይገኛሉ፡፡ ረሃብ ሀገራችንን ተለይቷት ባያውቅም በዚህ መጠን ግን የሁለት ዲጅት እድገት ትርክት ከተጀመረ ወዲህ ስላልተከሰተ የቀድሞውም ጠቅላይ ሚንስትር አልተጠየቁምም ለወራሾቻቸውም መልሱን አላስቀመጡም፡፡ በተወሰኑ አጋጣሚዎች ወደ ሚዲያ ብቅ ያሉትም ባለስልጣናት ችግሩን ከመካድ፣ መጠኑን ከማስተባበልም አልፎ የወረዱ ምክንያቶችን ሲደረድሩ ታዝበናቸዋል፡፡ መልሽ ያጣውን ጥያቄ ዛሬ በከፊልም ቢሆን ለመመለስ እንሞክር፡፡
ረሃብ! ድሮና ዘንድሮ
የሰባ ሰባቱ ድርቅና ረሃብ ሀገራችንን አለም ፊት አንገት ያስደፋ አሳዛኝ ክስተት ነበር፡፡ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተከሰተው ድርቅ ከፍተኛ የሆነን ረሃብና እልቂት አስከትሎ ነበር፡፡ ዶክተር እሌኒን የመሰሉ ምሁራን እንደሚሞግቱት በወቅቱ የሰሜኑ ክፍል በድርቅ ቢጠቃም በሌላው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ግን በቂ ምርት እንደነበረ ይገልፃሉ፡፡ ሀገሪቱ በዛ ወቅት ምርት ከተትረፈረፈበት ደቡብ እጥረት ወደተከሰተበት ሰሜን እንዲሄድ የሚያስችል በቂ የኢንፍራስትራክቸርና በተለይም የገበያ ተቅዋም አለመኖሩን ለችግሩ መባባስ እንደ ዋና ምክንያትም ያቀርባሉ፡፡ በሌላ አባባል በቂ የኢንፍራስትራክቸር ዝርጋታ ኖሮ በነበረና ምርትን ከፍላጎት ጋር ለማገናኘት የሚያስችል የገበያ መረብ ኖሮ በነበረ ድርቁ ያስከተለውን እልቂት መቀነስ ይቻል ነበር፡፡ ይህ ምልከታም በዶክተር እሌኒ መሪነት የተቋቋመውን የEthiopia Commodity Exchangeን ለመመስረት እንደ ዋነኛ መከራከሪያ ሆኖ በተለያዩ የጥናት ፅሁፎቻቸው ውስጥ ተካቶ እናየዋለን፡፡
አስከፊው የሰባ ሰባቱ እልቂት ከተከሰተ ከሰላሳ አመት በኋላም ይኸው ድርቅ አገሪቱን እያሳሰበ ይገኛል፡፡ እነ ዶክተር እሌኒ የሞገቱለት የኢንፍራስትራክቸርና የገበያ ተቋማት አለመኖር በፊት ከነበረው በእጅጉ የተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጥርጥር የለውም፡፡ የመንገዶችም ሆነ የኮሚኒኬሽን ኢንፍራስትራችቸሩ ከድሮው ጋር ሊወዳደር በማይችል መልኩ አድጓል፡፡ በሀገሪቱ በየትኛውም ቦታ የአቅርቦት እጥረት እናዳለና ተመጣጣኝ ትርፍ ሊገኝ እንደሚችል የሚያውቅ ነጋዴ ወሬውን ሰምቶ ተኝቶ ያድራል ብሎ ማሰብ ይከብዳል፡፡ ወሬውን ለመስማት የሚያስችለው የኮሚኒኬሽን ኢንፍራስትራችቸርም ይሁን ምርቱን እጥረት ወደ አለበት ቦታ ወስዶ ለማትረፍ የሚያስችለው የትራስፖርት አማራጮች በብዙ እጥፍ ተሻሽለውለታል፡፡ ይህ ባለበት ሁኔታ ረሃቡ በድጋሚ መከሰቱ እነ ዶክተር እሌኒ የዘነጉት ወይም ትኩረት ያልሰጡት ሌላ ተጨማሪ የረሃብ መንስኤ እንዳለ ያሳየናል፡፡ ይህም የህዝብ ወይም የመንግስት የመግዛት አቅምን ይመለከታል፡፡
ነጋዴው ያማሩ መንገዶችን ተጠቅሞ ትርፍ ምርት ካለበት ወደ እጥረት ወደተከሰተበት የሀገሪቱ ክፍል ምርቱን ቢያቀርብ ለረሃቡ መፍትሄ ሊሆን አይችልም፡፡ በችግሩ የተጠቃው የህብረተሰብ ክፍል የምርት አቅርቦት ብቻም ሳይሆን የመግዛት አቅሙም ሊኖረው ይገባል፡፡ ምርቱ በድርቅ የረገፈበት ገበሬ በደህናው ጊዜ ተቀማጭ ሀብት እስካላፈራ ድረስ የምርት አቅርቦትን ማሻሻልና ማቀላጠፍ ብቻ በራሱ ችግሩን አይፈታውም፡፡ ኑሮው ከእጅ ወደ አፍ ስለሆነና የመግዛት አቅሙም ስለማይኖረው ከመንግስት እርዳታን መከጀል ብቸኛ ምርጫው ይሆናል፡፡ መንግስት ፈርጣማ አቅሙን በመጠቀም ትርፍ ምርት ካለባቸው አካባቢዎችም ካልሆነም የውጭ ሀገራት ገዝቶ ተጠቂውን ህዝብ የመድረስ ግዴታ ይወድቅበታል፡፡ አሁን እንደሚታየው ከሆነ ግን ገበሬውም ለነገዬ ብሉ ያስቀመጠው ቅሪት ሳይኖረው በረሃብ አለንጋ እየተጠበሰ፤ መንግስትም ሲፎክርበት የነበረው ፈርጣማ አቅሙ በሞት አፋፍ ላይ ላሉት 15% ህዝቡ የቁርጥ ቀን ደራሽ መሆን ያዳገተው ይመስላል፡፡ ላለፉት አስርት አመታት ተኣምራዊ እድገትን ስታድግ የነበረችው ኢትዮጵያ፤‪‎ግብርናን‬ መሰረት ያደረገ; የእድገት ስትራቴጂ እየተከተለች እንዳለች የምትነግረን ኢትዮጵያ፤ ገበሬዋ እራሱን መመገብ ሲያቅተውና መንግስቷም የክፉ ቀን ደራሽ መሆን ሲሳነው እድገቱን የጎሪጥ ብናየው ይፈረድብን ይሆን?

ቅዳሜ 7 ኖቬምበር 2015

ድል ለመቀዳጀት በአንድ ማሊያ መጫወት (ይገረም ዓለሙ)

ይገረም ዓለሙ

የላቀ የኳሽ ችሎታ ያላቸው ተጨዋቾች በሀገራቸውም ሆነ ከሀገራቸው ውጪ በከፍተኛ ገንዘብ እየተሸጡ ይጫወታሉ፡፡ እነዚህ ዘር፣ቀለም ፤ኃይማኖትም ሆነ ቋንቋ ሳይገድባቸው በችሎታቸው ተመርጠው በየትኛውም የአለም ክፍል የሚጫወቱ ተጨዋቾች ገንዘብ የሚከፍላቸውን ቡድን የዋንጫ ባለድል ለማድረግ ለራሳቸውም ተዋቂነት ለማትረፍ በቁርጠኝነት ይጫወታሉ፡፡ የአንድ ሀገር ልጆች የተለያየ ማሊያ ለብሰው ለተለያዩ ቡድኖች ተሰልፈው ሲጫወቱ የተሰለፉለትን ቡድን ለአሸናፊነት ለማብቃት ይሻኮታሉ ይጎሻሸማሉ፡
አህጉራዊ ወይንም ዓለም አቀፋዊ ጨዋታ ሲኖር ግን ከየሄዱበት ተመልሰው ከተበታተኑበት ተሰባስበው በአንድ ማሊያ ለሀገራቸው ይሰለፋሉ፡፡ ለሀገራቸው ቡድን የመሰለፍ ምክንያታቸው በአሰልጣኙ መመረጣቸውና ሀገራቸው ችሎታቸውን መፈለጉ ብቻ ሳይሆን የእነርሱም ሀገራቸው አሸንፎ ባለ ድል አንዲሆን ከምር መፈለጋቸው ጭምር ነው፡፡ ባለፈው የዓለም ዋንጫ የእግር ኳስ ውድድር ላይ ከአሸናፊነት ክብር ብር በልጦባቸው ከሀገራቸው አልፎ አፍሪቃን መሳቂያ ያደረጉትን ተጨዋቾች ሳንጨምር ነው ታዲያ፡፡
በዚህ ተምሳሌት የሀገራችንን ፖለቲካ ብንመለከተው ወያኔ በዚህ መንገድ በሚገባ እየተጠቀመበት መሆኑን እናያለን፡፡ ተቀዋሚው ግን….. ፡፡ ወያኔ አባል አጋር ሌላም በውል ስም ያልወጣላቸው ቡድኖችን አቋቁሞ በተለያየ ማሊያ የክልል ጨዋታውን ያካሄዳል፤ አምስት ዓመት ጠብቆ ሀገራዊው ጨዋታ ሲካሄድ ደግሞ ሁሉንም በአንድ ማሊያ በኢህአዴግ ስም ያሰልፋል፡፡
ወያኔ ማሊያ እየቀያየረ መጫወት የጀመረው በህውኃት ማሊያ ወደ ጎነደርና ወሎ መሸጋገር እንደማይቻል በተረዳበት ግዜ ነው፡፡እናም የአማራ ክልል የሚል ስያሜ በሰጠው የኢትዮጵያ ክፍል ለመረማመድ እንዲቻለው ኢህዴን ይባል የነበረውን ሕብረ- ብሔራዊ ድርጅት ስሙንም ዓላማውን አስለውጦ ብአዴን በሚል መጠሪያ የአማራነት ማሊያ አለበሰው፡፡ወያኔ ይህን ሲያደርግ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ነው የመታው፡፡ አንዱ በአማራ ክልል ለመረማመድ የሚያስችለው ቡድን መፍጠር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የማይፈልገውንና ለእቅዱ አንቅፋት አድርጎ የሚያየውን ሕብረ ብሄር ፓርቲ ማክሰም፤ ሀገራዊ አስተሳሰብን ማጥፋትና ዘረኝነትን ማስፋፋት ነው፡፡ ወደ ሸዋ ሲጠጋ ደግሞ እሱም ጋር ሻዕቢያም ዘንድ የነበሩ ኦሮምኛ ተናጋሪ ምርኮኞችን ሰብስቦ በኦሮምያ ውስጥ ለመረማመድ የሚያስችለውን የኦሮሚያ ማሊያ ለብሶ የሚጫወት ቡድን ( ኦህዴድን) ፈጠረ፡፡አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ደግሞ የሱን ሥልጣን የሚያረጋጉና የሚያስጠብቁ ደኢህዴንና እና አጋር የሚባሉትን ቡድኖችን መፍጠሩን ሁሉም የሚያውቀው ነው፡፡
እነዚህ የተለያያ ማሊያ ለብሰው የተለያየ ቡድን ተመስለው የሚጫወቱ ቡድኖች የቡድን መሪያቸው አሰልጣኛቸው አስተዳዳሪያቸው ህወኃውት መሆኑን አሌ የሚል አይኖርም፡፡እናም ለዘወትሩ ጨዋታ በክልል ማሊያ እያሰለፈ በየአምስት ዓመት ለሚካሄደው ጨዋታ ደግሞ የኢህአዴግን ማሊያ እያሰለፈ ሀያ አራት አመት ሙሉ የዋንጫው ባለቤት እንደሆነ አለ፡፡
ይህን ጨዋታ ቅንጅትም ሞክሮት ውጤታማነቱን አሳይቷል፤ምርጫ 97 በአጃቢነት የምንገባበት፣ ለአድማቂነት የምንሰለፍበት ሳይሆን ከምር ተወዳድረን የምናሸንፍበት መሆን አለበት ያሉ ወገኖች ለማሸነፍ ደግሞ በተለያየ ስም ሆኖ የተለያያ ማሊያ ለብሶ ሳይሆን በአንድ ቡድን መደራጀት በአንድ ማሊያ መሰለፍ እንደሚስፈልግ ተናገሩ-ሰሩ፡፡ በዚህ ጥረትም አደረጃጀታው ሀገራዊ መገኛቸው ሀገር ቤት የሆኑ አራት ድርጅቶች ስማቸውን ቅንጅት ብለው ምልክታቸውን ሁለት ጣት አድርገው በአንድ ማሊያ ተሰልፈው መጫወት በመቻላቸው መቼም የማይረሳውንና መቼ ሊደገም እንደሚችል መተንበይ የማይቻለውን ውጤት አስገኙ፡፡
ይህ ከሆነ በኋላ ሁለት ምርጫዎች ተደርገው ተቀዋሚው እንደለመደው ጨዋታውን በተለያየ ማሊያ ማድረጉን በመቀጠሉ በአንዱ አንድ ወንበር ሲያገኝ በሁለተኛው ፓርላማውን ጨርሶ አስረክቧል፡፡ ሀገራዊ ውድድርን በአሸናፊነት ለመወጣት ካልሆነም ትንሽ ወንር ከፓርላማ ለማግኘት አንድ ቡድን መስርቶ በአንድ ማሊያ መጫወት ያለውን ጠቀሜታ ከወያኔ መማር ባይቻል ወይንም ባይፈለግ እንደምን ከቅንጅት መማር ይቸግራል፡፡
ለውጤታማነት በአንድ ማሊያ መጫወት የሚያስፈልገውና የሚጠቅመው በሀገር ቤት ለሚደረገው ትግል ብቻ አይደለም፡፡የትግሉ መነሻ ቦታ ኢትዮጵያም ይሁን አሜሪካ፣ ኤርትራም ይሁን በርበራ፣አሰብም ይሁን ሱዳን በሁሉም የሚፈለገው ውጤት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ማየት ከሆነ በአንድ ቡድን ተሰባስቦ አንድ ማሊያ ለብሶ አንድ ሀገራዊ ገዢ መርህ አንግቦ መጫወት የግድ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ ውጪ እስካሁን በተመጣበት ሁኔታ የሚካሄድ ውድድር(ትግል) ይህን ያህል ቡድን እዛና እዚህ አለ ከመባል ባለፈ ብሎም አንድ ቡድን ብቻውን ለጨዋታ ሜዳ አይገባምና የወያኔ አጨዋች ከመሆን የዘለለ የሚፈይደው ነገር የለም፣ አለ ከተባለ እገሌ የዚህ ቡድን መሪ እገሌ የዛኛው ቡድን ሊቀመንበር እየተባሉ መኖርን ትግልም ድልም ላደረጉ ሰዎች የሥልጣን ጥም ርካታ ማስገኘቱ ብቻ ነው፡፡ የፓርቲ መሪነት ሥልጣን ሆኖ፡፡
ሀያ አራት አመት እጅግ ብዙ ነው፡፡ስለሆነም ከዚህ በኋላ ሊመረን ይገባል፡፡በርግጥ ለውጥን ዓላማቸው አድርገው ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መሥረታ ከልብ አምነው ለዚህም ከምር ቆርጠው ለመታገል የወሰኑትና የፓርቲ ሊቀመንበር እየተባሉ መኖርን መነሻ ዓላማቸው መድረሻ ግባቸውም አድርገው የሚኖሩት ይለዩ፡፡ አንድ ቡድን መስርቶ በአንድ ማሊያ ተወዳደሮ የዋንጫ ባለቤት ላለመሆን ምክንያት ተደርጎ የሚቀርበው ቡድኖች ያላቸው የአደረጃጀት ፣ የጨዋት ስልት ፣የሚገኙበት ቦታ ወዘተ ልዩነት አሳማኝ አይደለም፡፡ ዋናው ምክንያት ሀገራዊ ለውጥ እንዲመጣ ያለመፈለግ ወይንም ቁርጠኝት ማጣት ነው፡፡ ለለውጥ በቁርጠኝነት የተሰለፈ ለለውጥ እንቅፋት ለሆኑ ችግሮች መፍትሄ ይፈልጋል እንቅፋት ሊሆኑ የሚችሉ ሰበቦችን ያስወግዳል እንጂ ልዩነትን ለማስፋት ሲማስን አያድርም፣በእያንዳንዱ ርምጃ ሰበብ እየፈለገ እንቅፋት አይፈጥርም፣ስለ ሀገራዊው ድል እንጂ ስለ እርሱ ቦታ አይጨነቅም፡፡
አንድ በግልጽ የሚታይ ነገር ላንሳ ጀነራል ከማል ገልቹና ጀነራል ሀይሉ ጎንፋ ሁለቱም ከወያኔ ከድተው አስመራ የገቡ የኦሮሞ ተወላጆች ናቸው፡፡እዛ ደርሰው ግን በአንድ ቡድን ተሰልፈው አንድ ማሊያ (ኢትዮጵያዊ ቢቀር ኦሮሚያዊ)ለብሰው መጫወት ተስኖአቸው ተለያይተው በኦሮሞ ስም የተለያየ ቡድን መስርተው እንደሚገኙ ነው የሚሰማው፡፡ ለያዙት ማእረግ የበቁት ውትድርናውን መቼ ጀምረውት እንደሆነ ማስረጃ ባይኖረኝም እዚህ ማዕረግ እስኪደርሱ በቃልም በተግባርም፤ በክፍልም በመስክም ወዘተ ሰፊ ወታደራዊ እውቀት እንደቀሰሙና ልምድ እንዳካበቱ እሙን ነው፡፡ ታዲያ በዚህ ወቅት ከሀገር ቤት ብቻ አይደለም ከአውሮፓና አሜሪካ ጭምር ከፕሮፌሰር እስከ ጳጳስ ከምር ቆርጠው ትግሉ ቦታ ሲወርዱ ጀነራሎቹ አሥመራ ተቀምጠው እንኳን ከሌላው መተባበር ርስ በርሳቸውም መነጋገር አቁመው አመታት መቁጠራቸውን መስማት እንቆቅልሽ አይሆንም!
ከምር ራሳቸውን ለትግሉ የሰጡና ለሥልጣን ሳይሆን ለነጻነት የሚታገሉ ስራቸው ምስክር ነውና በተግባራቸው እንለያቸው በምንችለውም አንደግፋቸው ይጠናከሩ፡ከውጤት አልባው የአመታት ጉዞአቸው ተምረው ለመለወጥ ያልፈቀዱትና ትግሉን ለስማቸው መጠሪያ ብቻ አድርገውት የሚኖሩት እንደዚሁ በተግባራቸው ይለዩ ፡፡ የእነዚህ መኖር ለሀገራዊው ትግል ከሚጠቅም ይልቅ ጉዳት ናቸውና ድጋፍ እንነሳቸው፤ከመኖራችሁ አለመኖራችሁ ይሻላል ብለን በግልጽ እንንገራቸው፡፡
ለነገሩ ሀገር ውስጥ ያሉት ብዙዎቹ ፓርቲዎች በወያኔ ዘንድ ነው እንጂ አሉ የሚባሉት ቆሞ ያልጠቀመ ሞቶ ምን ሊጎዳ ብሎ ሕዝቡ ከሸኛቸው አመታት ተቆጥረዋል፡፡ በውጪም በሚገኙት ላይ ይሄው መደገም አለበት፡፡ ሀገራዊውን ጨዋታ በአሸናፊነት ለመወጣት በአንድ ማሊያ መጫወት በምንልበት በዚህ ሰዐት እንወክለዋለን በሚሉት የአንድ አካባቢ ሕዝብ ስም የተደራጁ ሁለትም ስድስትም ድርጅቶች ስም እንሰማለን፡፡ የድርጅቶቹ መስራቾች ሁሉም ሊቀመንበር መባል በመፈለጋቸው ነው፡፡ ብዙም አባል አንደሌላቸው ይታወቃል፤ደጋፊው ግን ምን ይባላል፡፡ ትግሉን ከምር ያዙት አለያም ተዉት ማለት አያስፈልግም ትላላችሁ፡፡
በመጨረሻም ሎሬትን እንጋራ
Loret Tsegaye Gabre-Medhin

የፓርላማው ድራማ (ይገረም ዓለሙ)

ይገረም ዓለሙ
ሙሉ በሙሉ በአብዮታዊ ዴሞክራቶች በመያዙ የተለየ ሀሳብ የማይሰማበት ሙት የሆነውን ፓርላማ ህይወት ያለው ለማስመሰል የተዘጋጀው ድራማ ማክሰኞ ጥቅምት 16/2008 መታየት ጀምሯል፡፡ ይህ የፓርላማ ድራማ ቤቴሌቭዥን እንደምናያቸው ድራማዎች ሰሞነኛውን ትኩሳት እየተከተለ በየሳምንቱ የሚጻፍና የሚዘጋጅ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በዚህ የመጀመሪያ ቀን ትዕይንት መሪ ተዋናይ ሆነው የቀረቡት ጠቅላይ ምኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ከፓርላማው አባላት መካከል በተመረጡት ተዋንያን እየተጠየቁ በመመለስ ሲተውኑ ታይተዋል፡፡Hailemariam Desalegn in the TPLF parliament
ከቀደሙት ጠቅላይ ምኒስትር ጀምሮ ሲነገር እንጂ ሲተገበር የማይታየው ከተቀዋሚዎች ጋር አብሮ የመስራት ጉዳይ ለመጀመሪያው ቀን ድራማ ማድመቂያነት ከተመረጡት ጉዳዮች አንዱ ነበር፡፡ ተባብሮ መስራት ማለት እንደ ተቀዋሚዎች በመሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በመነጋገር ሀገራዊ መግባባት ከመፍጠር የሚጀምር እንደ ወያኔ ደግሞ እሱ በሚፈልገው ጉዳይ ሲፈልጋቸው ብቻ በመጥራት የሚገለጽ ነው፡፡ እንዲ ሆነናም በአምስት ዓመቱ ዕቅድ ላይ ለማወያየት ምርጫ ቦርድ መዝግቦ ለሚያውቃቸው ፓርቲዎች በሙሉ መንግጨሥታቸው ሰነድና ደብዳቤ መላኩን የገለጹት አቶ ኃይለማሪያም ብዙዎቹ በስብሰባው ላይ ሲገኙ ጥቂቶች ውኃ የማይቋጥር ምክንያት በመስጠት አልተገኙም አሉ፡፡ ያልተገኙት ፓርቲዎች ያቀረቡት ምክንያት ውኃ የማይቋጥር ነው ያሉበትን ምክንያትም ሲያረዱ በሕጋዊ መንግድ የተመረጠ መንግሥት ስላልሆነ ከእርሱ ጋር አንነጋርም ማለታቸው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ለመሆኑ ጥሪያችንን ተቀብለው ብዙዎቹ ተገኝተዋል የተባሉት ፓርቲዎች የትኞቹና እነማን ናቸው፡፡ዝቅ ብለን እናያቸዋለን፡፡
የመሳሪያ ትግል የሚያካሂዱትን ድርጅቶች አስመልክቶም ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ለራሱም መሆን ካልቻለው ሻዕቢያ ጋር ሆነው የሚያመጡት ውጤት ስለማይኖር ጊዜያቸውን በከንቱ ባያባክኑ በማለት ምክር ለመስጠት የዳዳቸው አቶ ኃይለማሪያም አንዳንዶቹ እኮ ጭራሽ የሌሉ ናቸው በማለት ኦነግን ኦብነግንና የጋምቤላ ህዝቦች ንቅናቄን ጠቀሱ፡፡ ይቺ ገለጻ የቀረበችው በደራሲውና አዘጋጁ ስህተት ይሁን ወይንም በርሳቸው የጥናት ጉደለት ባይታወቅም ሁለት መልእክት ታስተላልፋለች፡፡ አንደኛ እነዚህ የተጠቀሱት ድርጅቶች ሰሞኑን ተባብረው ለመስራት የደረሱበት ስምምነት እነ አቶ ኃይለማያም ሰፈር የፈጠረው ነገር መኖሩን እንድንጠረጥር ያሚያደርግ ፣ ሁለተኛ ደግሞ በሰሜን በኩል ድምጻቸው የሚሰማው ድርጅቶች እነዚህ ብቻ አይደሉምና ለሌሎቹ መኖሮና ጠንካራ መሆን በዘወርዋራ እውቅና የሰጠ ነው፡፡
አቶ ኃይለማሪያም የአቶ መለስ ሌጋስ አስቀጣይ እንደመሆናቸው ስለ ድርጅቶቹ የተናገሩት ከርሳቸው የወሰዱትን ነው፡፡ አቶ መለስ ብረት አንስተው መንግሥታቸውን የሚታገሉ ድርጅቶችን አስመልክቶ ሲላቸው አጥፍተናቸዋል የሉም ሲሉ ሌላ ግዜ ደግሞ በግላቸው ብዙ ርቀት ሄደው ከድርጅቶቹ መሪዎች ጋር ለመገናኘትና ለመደራደር እንደጣሩ ሲናገሩ ሰምተናል፡፡ ሌላ ግዜ ደግሞ ወድመዋል ተደምስሰዋል የተባሉት ደርጅቶች በዚህ ቦታ እንዲህ አደረጉ ጥፋት አደረሱ የሚል ዜና ስንሰማ ኖረናል፡፡ የሉም በተባሉ ድርጅቶች ስምም ዜጎች እየተወነጀሉ ታስረዋል እየታሰሩም ነው፡፡ አቶ መለስ አይደለም የሀገር ውስጥ ተፋላሚዎችን ሶማሌ ተሻግረው አልሻባብን ድምጥማጡን አጥፍተነዋል ብለውንም ነበር፡፡
አቶ ኃይለማሪያም ባያስታውሱም እኛ አንረሳውም፡፡ አቶ መለስ ከርሳቸው ፍላጎት ውጪ ስንዝር መሄድ የማይችለውን ፓርላማ አስፍቅደው(ነግረው) እንዲህ አስታዋሽ አጥቶ የቀረውን ሰራዊት ሶማሊያ በላኩበት ወቅት የገጠማቸውን ተቃውሞ ዝም ለማሰኘት ሰራዊታችን አልሻባብን ደምስሶ አሁን የቀረው ቃርሚያ ብቻ ነው፣ ያንን አጠናቆ በቅርብ ቀን ይመለሳል ብለውን ነበር፡፡ ነገር ግን ይኸው እስካሁን አልሻባብም አልጠፋ ሰራዊቱም አልተመለሰ፡፡ እንደውም በተቃራኒው ወንድሞቻችን የአልሻባብ ጥቃት ሰለባ እየሆኑ ነው፡፡ አቶ ኃለማሪያም እኔም አንደ መለስ ብለው በንቀት ስሜት የሉም ጠፍተዋል ስላሉዋቸው ድርጅቶች መረጃ ስለሌለኝ የምለው አይኖርም፤ የላችሁም የተባላችሁ መኖራችሁን አሳይዋቸውና አቶ ኃይለማሪም በዚህ አፋቸው ምን እንደሚሉ ለመስማት አብቁን የሚለው ግን መልእክቴ ነው፡፡
አቶ መለስ የሻዕቢያና ወያኔ ጸብና ፍቅር ለወላይታው ምኑ ነው ብለው ለአቶ ኃይለማሪያም አለነገሯቸው እንደሁ እንጂ ወያኔን አዲስ አበባ ያደረሰው ለራሱም የማይሆን ያሉት ሻዕቢያ ነው፡፡ ይህም ብቻ አይደለም ሌላው ኢትዮጵያዊ (የወያኔ ታጋይ ጭምር ) የማይታመን ሆኖ እስከ ተጣሉበት ግዜ ድረስ ቤተ መንግሥቱ ይጠበቅ የነበረው በሻዕቢያ ሰራዊት እንደነበረ የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡ስለሆነም አቶ ኃይለማሪያም ወያኔዎች ስለ ሻዕቢያ ዛሬ የሚሉትን ብቻ እየተቀበሉ መናገር ሳይሆን ትናንት ምን ይሉ ምንስ ያደርጉ እንደነበር የተጻፈ አንብበው የነበረ ጠይቀው ቢናገሩ ቢያንስ ጠቅላይ ምኒስትር ለሚለው ማዕረጋቸው( ይስሙላም ቢሆን) የሚመጥን ይሆናል፡፡
ከላይ እንደተገለጸው አቶ ኃይለማሪያም ስለ አብሮ መስራት ሲናገሩ ምርጫ ቦርድ የመዘገባቸውን ፓርቲዎች በሙሉ ጠርተን አብዛኛዎቹ ተገኝተዋል ነው ያሉት፡፡ አብዛኛው የሚለው የጥቅል መጠሪያ ለወያኔም ለፓርቲዎቹም ለምርጫ ቦርድም እያገለገለ ነው፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች በቁጥር ሲገለጹ እንጂ በስም ሲጠሩ አይሰማም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ምርጫ ቦርድ መዝገብ ላይ ሰፍረው የሚገኙት አንዳንዶቹ የሌሉ ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ምርጫ ሲመጣ ብቻ ብቅ የሚሉና ለምርጫ የሚሰጣቸውን ገንዘብ ተቀብለው የአጃቢነት ሚናቸውን ተወጥተው ለአራት ዓመት የሚጠፉ ናቸው፡፡ ጥቂቶቹም ፓርቲ ለመባል የሚያበቃ ቁመና የሌላቸው አቶ በረከት የፓርቲዎቹ ጥቅማቸው አልታይ ብሉአቸው ይሁን ስሜት ገፋፍቶአቸው ወይንም እውነት ተናንቆአቸው ባይታወቅም በመጽሀፋቸው የቤተሰብ ፓርቲ ሲሉ የገለጹዋቸው ናቸው ፡፡ በርግጥ ለመናገር አንዳንዶቹ ሊቀመንበር ተብሎ ከሚጠራው ሰው ቀጥሎ የሚጠራ ሶስትና አራት ሰው የሌላቸው በመሆኑ የቤተሰብ ፓርቲ የሚለውንም አያሟሉም፡፡ ብዙዎቹ ከተባሉት ከእነዚህ ስመ ፓርቲዎች ውስጥ ብዙዎቹን እንኳን ህብረተሰቡ ምርጫ ቦርድም አያውቃቸው፡፡ ድረ ገጹን ብትጎበኙ ቦርዱ ስለማያውቃቸው የተመዘገቡበትን ቀን መሙላት አቅቶት ቦታው ክፍት ሆኖ ታገኙታላችሁ፡፡ ፤ብቻ ብዙዎች እየተባሉ ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ይውላሉ፡፡እነዚህን በስም እየጠቀሱ መሪ የሚባሉትን ሰዎች ምንነትና ማንነት እያሳዩ መግለጽ የሚቻል ቢሆንም የሚፈይደው ነገር የለም፡፡ የምርጫ ቦርድን ድረ ገጽ ከጎበኙ ሌላም ነገር ይታዘባሉ፣ ምርጫ የማስፈጸም ብቃት አለው ተብሎ ምስጋና የተዥጎደጎደለት ይህ ተቋም ድረ- ገጹን ወቅታዊ ማድረግ ተስኖት ከአስር ዓመት በፊት የነበረ መረጃ ነው የሚያገኙት፡፡
ፓርቲ ማለት በምርጫ ቦርድ ተመዝግቦ የህጋዊነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የተሰጠው ነው ካልተባለ በስተቀር ብዙዎች የሚባሉት ከወያኔ ዳረጎት እየተቀበሉ፤ በምርጫ ቦርድ መልካም ፈቃድ ፓርቲ እየተባሉ፤ በአዳማቂነትና በአጃቢነት የሚያገለግሉ፣ እንኳን አባል የተሟላ አመራር የሌላቸው ናቸውና ፓርቲ ሊባሉ የሚበቁ አይደሉም፡፡ መሪ ለሚባሉት ሰዎች ግን የእለት እንጀራም የሕይወት መንገድም ሆኖ እየጠቀማቸው ነው፡፡ በአንጻሩ ብዙም ባይሆን ለወያኔ ዕድሜ መርዘምም እየረዱ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግን ኖሩም አልኖሩ “ተለበሰ ቀረ የደበሎ ቅዳጅ ”እንደሚባለው ናቸውና ምንም ፋይዳ የላቸውም፡፡ እንደውም የማይቻል ሆኖ እንጂ አለመኖራቸው ይሻል ነበር፡፡
ሙቱን ፓርላማ ህይወት ያለው ለማስመሰል የተጀመረው ድራማ ደራሲና አዘጋጁ ሰልችቶአቸው እስካላቆሙት ድረስ በጀመረው መልኩ ወቅታዊ የትኩረት አቅጣጫዎችን እየተከተለ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ የእኛም ማየትና መስማት ብሎም ከምናይ ከምንሰማው ተነስተን ብዕር ከወረቀት ማገናኘት እንዲሁ ይቀጥላል፡፡እስካላቆሙት ድረስ ያልኩት አቅጣጫ ለማስቀየሻ እየተባሉ በዚህ መልኩ የሚጀመሩ ጉዳዮች ሲዘልቁ ስለማይታይ ነው፡፡ደግሞስ የማስመሰል ስራ መች ብዙ መንገድ ያስኬዳል፡፡ይህ የፓርላማ ድራማ ቀልቡን የሚስበው ሰው ኖር ይሆን!!

ለጥቅምት 22 ሰማዕታት የመታሰቢያ ፕሮግራም ተካሄደ (ነገረ ኢትዮጵያ) ለጥቅምት 22 ሰማዕታት የመታሰቢያ ፕሮግራም ተካሄደ (ነገረ ኢትዮጵያ)

http://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2015/11/semayawi-party-remembering.jpg?bd378dምርጫ 1997 ዓ.ምን ተከትሎ ጥቅምት 22/1998 ዓ.ም በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ቀጥታ ትዕዛዝ በ‹‹ፀጥታ ሀይሎች›› በጭቃኔ ለተገደሉት ሰማዕታት እና ለቆሰሉት ኢትዮጵያውያን በሰማያዊ ፓርቲ ፅ/ቤት መታሰቢያ ተደረገ፡፡ የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች ጥቅምት 22/1998 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የገጠማቸውን በተለይም ኢትዮጵያውያን ሲገደሉ ያዩትንና የራሳቸውን ገጠመኝም አካፍለዋል፡፡
የፕሮግራሙ ተሳታፊዎቹ የተገደሉትን በክብር መቅበር እንዳልቻሉ እና ታፍሰው በተለያዩ እስር ቤቶች መታሰራቸውን አስታውሰዋል፡፡ አዛውንቶችንና ህፃናትን በጭካኔ ተገድለው ባንክ ሊዘርፉ ነው የተባለበትና የሥርዓቱን የህግና ሞራል የማይገድበው መሆኑን ያሳየበት ነውም ብለዋል፡፡ ሥርዓቱ ካለፈው ስህተቱ ሳይማር ዛሬም ለመግደል ዝግጁ እንደሆነ መቀጠሉንም ገልፀዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ሥርዓቱ ወደ ባሰ አምባገነንነት በመግባቱም ትግሉን መቀላቀላቸውን ገልፀው፣ ዘላቂው አማራጭ የሰማዕታቱን የትግል መንፈስ ፅናት ይዞ መታገል ነው ብለዋል፡፡ እነሱ አላማ ያደረጉትን ተጉዘው በአንድነት የኢትዮጵያን እጣ ፋንታ መወሰን እንደሚገባቸውም ገልፀዋል፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በ1997 ዓ.ም በኋላ የሥርዓቱ ሁኔታ እየተባባሰ እንደመጣና ለዚህም ዋናው ምክንያት ኢትዮጵያውያን ሥርዓቱ የሚያደርስብንን በደል ችለን ወደ ውስጥ የምናለቅስ መሆናችን ነው ብለዋል፡፡ ሥርዓቱ ይቅር የማይደረግለት ሆኖ፣ ፖለቲካው በመነታረክ መቀጠሉን ትክክል እንዳልሆነም ገልፀዋል፡፡
‹‹ሥርዓቱ ታሪክና የጋራ ነገር የላችሁም ብሎናል፡፡ መናናቅንና ሀይማኖትን ማቃለልን በተግባር አሳይቶናል፡፡ የወደፊት ኢትዮጵያ በእኛ እጅ እንድትሆን ከፈለግን የነበረውን የሀገራችን እሴት ማናናቅ የለብንም፡፡›› ያሉት ኢ/ር ይልቃል ኢትዮጵያውያን የገነቧቸው እሴቶች ሁሉ በወጣቱ ልብ ውስጥ ማደር እንዳለባቸው፣ ሰማዕታቱ የሞቱለት አላማና ኢትዮጵያውያን የገነቡት እሴት መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡