እሑድ 28 ዲሴምበር 2014

ገዥው ፓርቲ ባህርዳር ላይ  የግዳጅ ሰልፍ ሊጠራ ነው።

ታኀሳስ ፲፯(አስራ ሰባትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ   ከቀናት በፊት በባህርዳር የተካሄደውንና  ምእመናን የተገደሉበትን የተቃውሞ ሰልፍ – የሚቃወም  ሌላ የግዳጅ ሰልፍ  ሊጠራ መሆኑን የከተማው ነዋሪዎች  ገለጹ።
እንደ ምንጮች ገለጻ በግዳጁ ሰልፍ የማይገኝ የባህርዳር ነዋሪ ቅጣት ይጣልበታል ተብሏል።
ገዥው ፓርቲ በአማራ ክልል አስተዳደር ባህር ዳር ከተማ የቤተ ክርስቲያን ንብረት የሆነውን የታቦት ማደሪያ ለመንገድና ለጥቃቅንና አነስተኛ ሱቆች መስሪያ እንዲነጠቅ ማዘዙን ተከትሎ የባህር ዳር  ህዝበ-ክርስቲያን የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው ይታወቃል።
በሰልፉ ሰላማዊ ሰዎች ከመገደላቸውም ባሻገር በርካቶች መጎዳታቸው በምእመናኑ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣና ቅሬታ  በቀሰቀሰበት በአሁኑ ወቅት ገዥው ፓርቲ ቀደም ሲል የተካሄደውን ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ የሚቃወም  ሌላ የድጋፍ ሰልፍ ሊጠራ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ዘገባ ያመለክታል።
መንግስት ታህሳስ 9/2007 ዓ.ም የተደረገውን ህዝባዊ ተቃውሞ የ‹‹ፀረ ሰላም ኃይሎች እጅ እንዳለበት›› በመግለጽ ‹‹ህገ-ወጥ ሰልፍ›› ማለቱ  ይታወሳል።
በአሁኑ ወቅት  ባህር ዳር ከተማ የሚገኙት የቀበሌ ካድሬዎች የኢህአዴግን የግዳጅ ሰልፍ ለማሳካት   እያስተባበሩ እንደሚገኙ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቀበሌ ካድሬዎች በየ ቤቱ እየሄዱ የነዋሪዎችን ስም በመመዝገብ በሰልፉ የማይሳተፍ ሰው ቅጣት እንደሚጠብቀው እያስጠነቀቁ  እንደሆነ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
የግዳጅ ሰልፉ ታህሳስ 21 ወይንም 22 ቀን 2007 ዓ.ም ይደረጋል ተብሎ ይታሰባል፡፡

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር በ15 ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎችን ሊያደርግ ነው

ታኀሳስ ፲፯(አስራ ሰባትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-የ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ያወጣውን ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩን ታህሳስ 17 ቀን 2007 ዓ.ም ይፋ ሲያደርግ፣ ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩም ለ2 ወራት የሚቆይ እንደሚሆን አስታውቋል።
የትብብሩ አመራሮች በሰማያዊ ጽ/ቤት የሰጡትን  መግለጫ ተንተርሶ ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው በሁለተኛ ዙር የትብብሩ መርሃ ግብር መሰረት የካቲት 15 ቀን 2007 ዓ.ም በተመሳሳይ ሰዓት በ15 የሀገሪቱ ትላልቅ ከተሞች ላይ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፎች ይደረጋሉ።  በአዲስ አበባ፣ በሀዋሳ፣ በባህር ዳርና በአዳማ ደግሞ ህዝባዊ ስብሰባዎች እንደሚደረጉ የትብብሩና የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ይልቃል ጌትነት (ኢ/ር) በመግለጫው ወቅት ተናግረዋል፡፡
ይህን የሁለተኛ ዙር የሁለት ወር ዕቅድ ከታህሳስ 16 እስከ የካቲት 15 /2007 አውጥቶ በቀዳሚነት ለዋነኛ ባለቤቶቹና ፈጻሚዎቹ ኢትዮጵያዊያን ሲያቀርብ እንደመጀመሪያው ዙር ከጎኑ እንደሚቆሙ ሙሉ እምነት በማሳደር ነው›› ያለው መግለጫው፣ በትብብሩ በኩል በአመራር ከፊት ቆመው ትግሉን ለመምራት ዝግጁነትና ቁርጠኝነት መኖሩን ሊቀመንበሩ አስረድተዋል።
የትብብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ለእንቅስቃሴው ማስፈጸሚያ 1 ሚሊየን 200 መቶ 15 ሺህ  ብር በጀት አጽድቋል። በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከጎኑ እንዲቆሙ ትብብሩ ጥሪውን  አስተላልፏል፡፡

ዓርብ 26 ዲሴምበር 2014

ምርጫ ቦርድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ሊያካሂድ ላቀደው ብሔራዊ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች ምዝገባ በዛሬው ዕለት ጀመረ፡፡

ታኀሳስ ፲፮(አስራ ስድስትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-ቦርዱ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በየምርጫ ክልሉ ጽሕፈት ቤቶች ከታህሳስ 16 እስከ ጥር 27 ቀን 2007 ዓ.ም ምዝገባ እንደሚካሄድ የሚታወቅ ቢሆንም አንድነትና መኢአድ ፓርቲዎች ከምርጫ ቦርድ ጋር ከገቡት አሰጥ አገባ ጋር ተያዞ በምርጫው የመቀጠላቸው ነገር አጠራጣሪ መሆኑ ታውቆአል፡፡
አንድነት እና መኢአድ በመጪው ምርጫ ለመወዳደር ወስነው የምርጫ ምልክት ለቦርዱ ካስገቡት  ፓርቲዎች መካከል ሲሆኑ ቦርዱ ፓርቲዎቹ ያቀረቡትን ምልክት ላይ ለመወሰን ያላሟሉት የሕግ ጉዳይ አለ በሚል ሰሞኑን መግለጫ ማውጣቱ የሚታወስ ነው፡፡ ሁለቱ ፓርቲዎች አላሟሉም ከተባሉት መካከል አንዱ በፓርቲዎቹ ውስጥ ከተፈጠረ ውዝግብ ጋር ተያይዞ ትክክለኛ አመራሮቻቸውን አላሳወቁም ፣ የምርጫ ሕጉንና ሕገደንባቸውን አላከበሩም የሚለው የምርጫ ቦርድ ክስ ይገኝበታል፡፡ ፓርቲዎቹ ይህንን ችግር በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ አስተካክለው እንዲቀርቡ ቦርዱ ታህሰስ 4 ቀን 2007 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ ወስኖአል፡፡
በዚህም ውዝግብ ምክንያት ፓርቲዎቹ ለአምስት ሳምንት ገደማ በሚቆየው የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎች ምዝገባ ብቁ አይደሉም በሚል ከወዲሁ ሊሰርዛቸው ይችላል የሚል ግምት መኖሩን ምንጮቻችን ዋቢ በማድረግ የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ገልጿል፡፡ ቦርዱ በአሁኑ ሰዓት ከፓርቲዎቹ ጋር እየተጻጻፈ ያለው ደብዳቤ በኃላ ለሚወስደው እርምጃ ሕጋዊነት ለማላበስ ታቅዶ መሆኑን ምጮቻችን አስታውሰው ፓርቲዎቹ ሕግና ስርዓትን አላከበሩም በሚል ከምርጫው በማስወገድ ኢህአዴግ ከጥቂት አጃቢ ታማኝ ፓርቲዎች ጋር ለምርጫው ሊቀርብ እንደሚችል እየተነገረ ነው፡፡
ጠ/ሚኒስትር ኃ /ማርያም ደሳለኝ በምርጫ የሚፎካከሩዋቸውን ፓርቲዎች በሶስት መደቦች በመክፈልና ቀይ እና ቢጫ ካርድ የተሰጣቸው እንዳሉ በመግለጽ ማስጠንቀቂያ አዘል መልዕክት ሰሞኑን ማስተላለፋቸው ኢህአዴግ ለነጻና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳልተዘጋጀ የሚያሳይ መሆኑን ዘጋቢያችን ገልጿል።
በተመሳሳይ ዜና ደግሞ ታህሳስ 12/ 2007 ዓ.ም የተካሄደው የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ “በሀገራችን የምርጫ ቦርድ አለ ወይ” እንዲል አድርጎታል በማለት አንድነት ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።
የታህሳሱ 12 “የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ ነፃና ገልልተኛ አልነበረም ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የምርጫ ህጉን ተከተሎ ያልተካሄደ ሌላው ይቅርና የራሱ የምርጫ ቦርድ መመሪያን እንኳን ያልተከተለ ከመሆኑ አንፃር ተካሄዷል ብለን አናምንም” ሲል ፓርቲው አስታውቋል።
ህዝቡ በምርጫ ቦርድ በእኩል በይፋ የስብሰባ ጥሪ ያልተደረገለት መሆኑ፣  ፓርቲው ባሰማረባቸው የምርጫ ጣቢያ ቦታዎች ከሞላ ጎደል በአንድ ለአምስት ስርዓቱ ካደራጃቸው የራሱ አባላትና ደጋፊዎች በስተቀር ሌላው ህዝብ ሳያውቅ የተካሄደው መሆኑ፣  ከአስር ሺዎች በላይ ነዋሪ ያለባቸው አከባቢዎች ሀምሳ እና መቶ ሰው በተገኘባቸው አዳራሾች መካሄዳቸውን በችግርነት አንስቷል።
በመላ ሀገሪቱ የምርጫውን ሂደት ለመታዘብ የተሰማሩ አባሎቻቸው በፀጥታ ኃይሎች ለእስርና ለእንግልት መዳረጋቸውን፤  በበርካታ አከባቢዎች ምንም ዓይነት ምርጫ ያልተካሄደ መሆኑ ፤ በ2002 ምርጫ ታዛቢ የነበሩ ሰዎች እንዳሉ ለዘንድሮው የ2007 ምርጫም ታዛቢ እንዲሆኑ በጅምላ እንዲፀድቅላቸው መደረጉ በተለይም በአከባቢው የሌሉና የሞቱ ሰዎችም ጭምር የህዝብ ታዛቢ ሆነው የተመረጡበት ሁኔታ መፈጠሩ በተጨማሪ ችግርነት ተገልጿል።
በዘንድሮ የሚካሄደው የ2007 ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛና ተኣማኒ እንደማይሆን ከወዲሁ የሚያረጋግጥ ነው የሚለው አንድነት፣  ኢህአዴግንና ምርጫ ቦርድን እያጋለጠ በህዝባዊ ንቅናቄ ህዝቡን አደራጅቶ ትግሉን በቆራጥነት ይቀጥላል ሲል መግለጫውን ደምድሟል።
በሌላ በኩል ደግሞ በደሴ ዙሪያ የሚገኙ ቀበሌዎች ህዝቡ ኢህአዴግን እንደሚመርጥ ቃል የሚገባባትን ፎርም እንዲሞላ እየተገደደ ነው። ፎርሙን ያልሞላ ከማንኛውም ጥቅም እንደሚገለል የተገለጸ ሲሆን፣ አንዴ ፎርሙን የሞላ ሰው በሁዋላ ላይ መቀየር እንደማይችል ተገልጾለታል።

አየር ሃይል እየታመሰ መሆኑን ምንጮች ገለጹ


ታኀሳስ ፲፬(አስራ አራትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-የአየር ሃይል ባልደረባ የሆኑት ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝ ከበረራ ቴክኒሻኑ ጸጋ ብርሃን ግደይ ጋር በጋራ በመሆን የሚያበሩትን ሄሊኮፕተር ይዘው ከጠፉ በሁዋላ የአየር ሃይል አዛዦች አስቸኳይ ግምገማ ከተጠሩ በሁዋላ እርስ በርስ እየተገማገሙና ከእነዚህ ሰዎች ጋር ግንኙነት አላቸው ብለው የሚያስቡትን የአየር ሃይል አባላት ለማሰር እንቅስቃሴ መጀመራቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በተለይም የትግራይ ተወላጅ ከሆኑት ሻምበል ሳሙኤል ግዴይና ቴክኒሻኑ ጸጋ ብርሃን ጋር የቅርብ ግንኙነት አላቻው የተባሉ ሰዎች እየተጠሩ በመጠየቅ ላይ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሎአል። የመከላከያ ሚኒስትር ሻምበል ሳሙኤል ግደይን ከሃዲ ሲል ሲፈርጀው፣ መቶ አለቃ በልልኝ ደሳለኝንና ቴኒኪሻን ጸጋ ብርሃንን ደግሞ ተገደው መብረራቸውን ገልጿል።

የኢሳት ታማኝ ምንጮች እንደገለጹት ከፍተኛ የበረራ ልምድ ያላቸው ሻምበል ሳሙኤል የህወሃት ባለስልጣናት በኢትዮጵያ አየር ሃይል ላይ የሚያደርሱትን ጥፋት ከሚቃወሙት የትግራይ ተወላጆች መካከል አንዱ ነው። መቶ አለቃ ቢልልኝ ደግሞ በአየር ሃይል ውስጥ የተስፋፋውን ዘረኝነት ከሚኮንኑ አብራሪዎች መካከል መሆኑ ታውቋል። በ2 ሺ ዓም አየር ሃይልን የተቃለቀለው መቶ አለቃ ቢልልኝ ሱዳን ውስጥና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ሄሊኮፕተር በማብረር ብቻውን የተለያዩ ግዳጆችን መወጣቱን ምንጮች ገልጸዋል። ሁሉም ስርዓቱን በመቃወም ጥለው የጠፉ እንጅ፣ መንግስት እንዳለው አንዱ  ሌላውን አስገድዶ እንዲጠፋ አለማድረጉን ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁት ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል።
በሌላ በኩል መንግስት አብራሪዎቹ ሄሊኮፕተሩን ኤርትራ አሳርፈውታል የሚል መግለጫ ቢሰጥም፣ የኤርትራ መንግስት ምንም መግለጫ አልሰጠም። ኢሳት ሄሊኮፕተሩ የት እንዳረፈ ለማወቅ ያደረገው ሙከራም እስካሁን አልተሳካለትም። በአየር ሃይል አዛዦች ውስጥ የተፈጠረውን ትርምስ ተከትሎ ኮሎኔል አበበ ተካና በብርጋዴር ጄኔራል ማሾ ሃጎስ እርስ በርስ መወነጃጀል ጀምረዋል።
ኮሎኔል አበባ ተካ በህወሃት መሪዎች ዘንድ የሚወደዱ በመሆናቸው አየር ሃይልን ከጀርባ ሆነው እስካሁን ሲመሩት ቆይተዋል። አለቃቸው ብርጋዴር ጄኔራል ማሾ ሃጎስ ደግሞ ከህወሃት ባለስልጣናት ጋር በሚፈጥሩት አለመግባባት የተነሳ  ስልጣን ሳይኖራቸው  በስም ብቻ ተንሳፈው የሚኖሩ ናቸው። ብርጋዴር ጄኔራል ማሾ ቀደም ብሎ ከአየር ሃይል አዛዡ ሞላ ሃይለማርያም ጋር ከፍተኛ ጸብ ውስጥ ገብተው የነበር ሲሆን፣ ከኢታማጆር ሹሙ ሳሞራ የኑስ ጋርም ያላቸው ልዩነት እየሰፋ ሄዶ እርስ በርስ ማውራት ማቆማቸው ይነጋራል። ከጄ/ል ማሾ ጋር በእኩል ደረጃ የነበሩ ወታደራዊ  አዛዦች ቀድመዋቸው የጄኔራልነት ማእረግ ሲሰጣቸው እርሳቸው ግን ከሁለት ጊዜ በላይ እንደታለፉና  በቅርቡ በተደጋጋሚ ባሰሙት ቅሬታና ህወሃትን ከመከፋፈል ለማዳን በሚል ምክንያት የብርጋዴር ጄኔራልነት ማእረግ እንዲሰጣቸው ተደርጓል።
ጄ/ል ማሾ በሲነየርቲ ከፍተኛ የማእረግ ደረጃ ላይ መድረስ የነበረብኝ ቢሆንም፣ ከጓደኞቹ እንዳንስ ያደረገኝ ጄ/ል ሳሞራ በሚያደርስብኝ በደል ነው በሚል በተደጋጋሚ ቅሬታ እንደሚያሰሙና ከስራቸው እየቀሩ በተለያዩ ሱሶች ተጠምደው እንደሚውሉ የቅርብ ምንጮች ይገልጻሉ። ጄ/ል ማሾ ቦታውን በስም ብቻ እንዲይዙ ተደርጎ ዋናውን የበረራ ስምሪት የሚያካሂዱት ኮ/ል አበበ መሆናቸው ፣ ኮሎኔል አበበን በሚደግፉት በእነ ሳሞራ እና በጄ/ል ማሾ መካከል ያለው ውዝግብ እንዲሰፋ ተጨማሪ ምክንያት ሆኗል።
ኮ/ል አበባ ተካ አየር ሃይልን በተለይም የድሬዳዋን አየር ምድብ ማዘዝ ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ አየር ሃይሉን ጥለው የሚጠፉ አብራሪዎች ተበራክተዋል። ባለፉት 6 ወራት ብቻ 11  አብራሪዎች አየር ሃይልን ጥለው በመጥፋት ግንቦት7ትና አርበኞች ግንባርን  ተቀላቅለዋል። አብዛኞቹ ለመጥፋታቸው ከሚሰጡዋቸው ምክንያቶች መካከል ዘረኝነት፣  የተበላሸ አስተዳደራዊ አሰራር መኖርና በአገሪቱ የሚታየው የመብት አፈና  የሚሉት ናቸው።
የአየር ሃይል ምንጮች እንደሚሉት ኮ/ል አበበ ተካ የውቅሮ ተወላጅ ሲሆኑ፣ በድሬዳዋ ምድብ ውስጥ ያሉ የሃላፊነት ቦታዎችን በውቅሮ ልጆች ብቻ እንዲሞሉ አድርገዋል። ቀደም ብሎ የአየር ሃይል አዛዥ የነበሩት አበበ ተክለሃይማኖት በተመሳሳይ የውቅሮ ልጅ ሲሆኑ፣ ኮ/ል አበበን አሁን ላሉበት ደረጃ ያደረሱዋቸው እርሳቸው መሆናቸውንም ምንጮች ይገልጻሉ። ኮ/ል አበበ አየር ሃይል እንዲዳከም ከፍተኛ ሚና መጫወታቸውን የተለያዩ አብራሪዎች ቢናገሩም፣ እስካሁን ድረስ ማንም ደፍሮ እርምጃ አልወሰደባቸውም። እርሳቸው ሃላፊ ሆነው ከተሾሙ ወዲህ በ2001 ዓም ሃምሌ ወር ላይ 2 ኤፍ ኤፍ 260 የመሰረታዊ በረራ ማስተማሪያ ሄሊኮፕተሮች ተጋጭተዋል። እርሳቸው በሰጡት የተሳሳተ አመራር  2 ኤም አይ 35 ሄሊኮፕተሮች በአየር ላይ ተጋጭተው 6 አብራሪዎች አልቀዋል። አንድ ኤፍ ኤፍ ሄሊኮፕተር ደግሞ ሁርሶ ላይ ሞተር ጦፍቶበት የወደቀ ሲሆን፣ አብረራዎቹ እንደ እድል ተርፈዋል። እነዚህ ሁሉ ችግሮች የኮ/ል አበበ የአመራር አሰጣጥ ድክመት የፈጠራቸው መሆናቸው ቢታመንም፣ ለረጅም ጊዜ ጄ/ል ሞላ እንዳይገመገሙ አድርገዋቸው እንደቆዩ ጄ/ል ሞላ ሃላፊነቱን ከለቀቁ በሁዋላ ደግሞ ጄ/ል ሳሞራ እየተከላከሉላቸው ይገኛሉ።
ኮሎኔሉ አበበ በጦር ሄሊኮፕተሮች የኮንትሮባንድ እቃዎችን ወደ ድሬዳዋ እየጫኑ ከጄ/ል ሞላ ሃይለማርያም ጋር በመሆን ሲነግዱ እንደቆዩና ከፍተኛ የሆነ ሃብት እንዳከማቹ የቅርብ ምንጮች ይገልጻሉ። በድሬዳዋ፣ አዲስ አበባና መቀሌ ሰፋፊ ቦታዎችና በአዲስ አበባም አንድ ትልቅ ፎቅ አሰርተዋል በማከራየት ላይ ናቸው። እነዚህ ሁሉ ቸግሮች ጄ/ል ማሾ ኮሎኔል አበበን ለመክሰስ በቂ ምክንያቶች ቢሆኑላቸውም፣ ከላይ ባሉ ባለስልጣናት ድጋፍ በማጣታቸው እስካሁን ውጤታማ ሊሆኑ አልቻሉም። ሰሞኑን የጠፉትን አብራሪዎች ከጄ/ል ማሾ ጋር ለማያያዝ የእነ ኮ/ል አበበ ደጋፊዎች ጥረት እያደረጉ ሲሆን፣ ከጄ/ል ማሾ ጋር ግንኙነት አላቸው ወይም አላማቸውን ይደግፋሉ ያሉዋቸውን ሁሉ ለመምታት እየተንቀሳቀሱ ነው።
ኮ/ል አበበ ኢሳት ሊያነጋግራቸው ቢሞክርም ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸው ይታወቃል። ብርጋዴር ጄነራል ማሾን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።f

ቅዳሜ 19 ጁላይ 2014

Police detained more than 6 andnet party members at the get of Arada court. As Finote netsanet’s informers

Police detained more than 6 andnet party members at the get of Arada court. As Finote netsanet’s informers
- Daniel Feyisa –from udj
-Abinet regasa - from udj
-Fasika -from udj
- Berhanu YegelTu -from udj
- Mesele Admase from udj
-Tilaye Tarekegne - from udj are detained at ‘’Maekelawi’’ will list all lists soon.

ወይንሸት ሞላ ክፉኛ ተደብድባ ዝግ ችሎት ቀረበች!


ወይንሸት ሞላ ክፉኛ ተደብድባ ዝግ ችሎት ቀረበች!

(EMF) በትላንትናው እለት አንዋር መስጊድ ህዝበ ሙስሊሙ ሲደበደብ ወይንሸት ሞላ በስፍራው ነበረች። አንድ ከዚህ በፊት የሚያውቃት የደህንነት አባል በቀጥታ ወደሷ መጥቶ ይደበድባት ጀመር። በወቅቱ በስፍራው የነበረው በፍቃዱ ጌታቸው ስለሁኔታው እንዲህ በማለት ጽፎ ነበር።
በወቅቱ የሰማያዊ ፓርቲ የሰማያዊ ፓርቲ የብሄራዊ ምክር ቤት አባል የሆነችው ወጣት ወይንሸት ሞላ አብራኝ ነበረች፡፡ አንዋር መስጊድ በወንዶች መግቢያ ፊት ለፊት ካለው ህንጻ ላይ ሆነን ሁነቱን ስንከታተል ከአሁን ቀደም የሚያውቃትና ከህንጻ ላይ ሆኖ ሲቀርጽ የነበር ደህንነት ብቻዋን ነጥሎ እየደበደበ ወሰዳት፡፡  ‹‹ለምን ተወስዳታለህ!›› ብዬ በጠየኩበት ወቅት ከእነዛ ከመንገድ ተለቃቅመው ለድብደባ የተሰማሩት ወጣቶች መካከል አንዱ ሽጉጥ አወጣብኝ፡፡ ለመሳሪያ ልምድ የሌለው በመሆኑ ካርታው እግሩ ስር ወደቀበት፡፡ ወይንሸትን ይዘውም ወደ ውጭ ከነፉ!
ወይንሸት ሞላ
ወይንሸት ሞላ
ዛሬ ፍርድ ቤት ይዘዋት ቀርበዋል። ሁኔታውን የተከታተለው ዮናታን ተስፋዬ የታዘበውን እንዲህ በማለት ነው ያቀረበው። “እጇቿ ክፉኛ ተጎድተዋል፡፡ ጣቷ አብጧል፡፡ ፊቷ ገርጥቷል፡፡ የግራ እጇ በፋሻ ተጠቅልሎ አንገቷ ላይ እንደታሰረ በአንድ ፖሊስ እርዳታ ወደ ፍርድ ቤቱ ግቢ ገብታለች፡፡” ብሎ ነበር። ጥቂት ቆይቶ ባስተላለፈው መልእክት ደግሞ “ወይንሸት ጭንቅላቷን በቀኝ በኩል ተፈንክታለች፡፡ ተሰፍቶ ይታያል፤ ቀኝ እጇ መሰበሩ ተረጋግጧል፡፡ ሰውነቷ በጣም መጎዳቱ ያስታውቃል፡፡ ከፍርድ ቤት መልሰው አዲስ አበባ ፖሊስ ከሚሽን ወስደዋታል፡፡ ማንም እንዲያያት አልተፈቀደም የፍርድ ሂደቱንም ማንም መከታተል አልቻለም፡፡ ስንቅ ማቀበልም ተከልክሏል፡፡” በማለት ሁኔታውን አስረድቷል።

አሁን በደረሰን ዘገባ መሰረት በዝግ ችሎት የቀረበችው ወይንሸት ሞላ 14 ቀን ተጨማሪ ምርመራ ተጠይቆባት፤ 14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባታል፡፡ የፍርድ ቤቱን ሂደት ማንም ሰው እንዲከታተል አልተፈቀደም የህግ ሰውም እንዳያናግራት ተከልክሏል፡፡  አሁን ከማዕከላዊ አጠገብ በሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እስር ቤት ነች፡፡ የፖሊስ ጣቢያው ኃላፊዎች ማንም ሰው ሊያያት እንደማይችልና ስንቅም ሆነ ልብስ ላልተወሰነ ቀናት እንዳይመጣ በማለት መልሰውናል፡፡
አሁን ያለው ሁኔታ ይህን ይመስላል። ትንሽ ቆይተው እሷንም አሸባሪ ብለው መክሰሳቸው የማይቀር ነው። ሌላ የሽብር ክስ ከመስማታችን በፊት፤ ትክክለኛውን ነገር ከወዲሁ እንዲረዱት፤ ወይንሸት ሞላ ወደ አንዋር መስጊድ ከመሄዷ በፊት አግኝቷት የነበረው ዮናታን ቀደም ብሎ የዘገበውን እናስነብብዎ። እንዲህ በማለት ጽፎ ነበር።
ወይኒ ትናንት ጠዋት ላይ ቢሮ ቁጭ ብዬ ከላፕቶፕ ላይ እንደተደፋሁ መግባቷንም ሳላስተውል . . .
“እዚህ አፍንጫችን ስር ይህን የመሰለ ሰላማዊ ትግል ሲካሄድ ቢያንስ ሄደን አንታዘብም!? እዚህች መርካቶ አጠገብ ተቀምጠን ዘመን እየተጋራን – ታሪክ እየተጋራን . . .” ስትል ቀና ብዬ አየኋት።  . . . ምንም ማለት አልደፈርኩም. . . ለብዙ ጊዜ አንዋር መስጂድ እሄድ ነበር (በተለይ ባለፈው ዓመት)  የግልና የፖለቲካ ስራ ጊዜ አይሰጥም እንጂ አሁንም ብገኝ ምኞቴ ነው ፤ ሰው በጨካኞች ተከቦ ለመብቱ በፅናት ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ ሲጮህ መመልከት በራሱ ትልቅ መነቃቃት እና ተስፋ ይሰጣል፡፡
ወይኒን ተረዳኋት ግን ሰጋሁ፡፡ ምክንያቱም ወይኒ ቀጥተኛ ሰው ነች . . . የሰው ጥቃት አትወድም . . . ሰው ሲበደል እያየች ዝም የሚል አፍ አልፈጠረባትም . . . ትናገራለች በጣም ተቆጥታ ትናገራለች . . . እንኳን በቆመጥ ሲደበደቡ እያየች በክፉ ሲታዩም ይተናነቃታል . . . ከእንባዋ እየተናነቀች ምራቋን ውጣ ትናገራለች . . . ወይኒ እንዲህ ነች . . . ምናልባትም ይህ ተቆርቆሪ ስብዕናዋ ይሆናል ሰማያዊ ፓርቲ ከትማ ያገናኘን፡፡ እናም ሰጋሁ፡፡
እንጃ ቀልቤ የሆነ ነገር ሊፈጠር እንደሚችል አስቀድሞ አሳወቀኝ መሰል . . .  “ምንም እኮ አዲስ ነገር አይፈጠርም I’ve been there, you know, it’s all the same every Friday” ከልቤ አልነበረም …
“መርካቶ ጉዳይ አለኝ በዛው ሙስሊም ወገኖቼን አየት አየት አድርጌ እመለሳለሁ” ከነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ ጌታቸው ሽፈራዉ ጋር እንደምትሄድ ነግራን ሄደች። ጌች ተደብድቦ ሲመለስ እሷ በዛው ቀረች . . . የፈራሁት ሆነ የህወሓት ካድሬዎች እንደሚጠሏት አውቃለሁ፤ ግን ፅናቷ ያፅናናኛል፡፡
ጎንደር አብረን ታስረን የማይረሳ ትዝታ ቀርፃብኝ ነበር . . . የሳዑዲ መንግስትን ተቃውመን አደባባይ ስንወጣ ሶስት ጨካኝ ፌደራሎች ብቻዋን ደብድበዋት ኢያስፔድ ታቅፎ ከወደቀችበት ነጥቆ አስጥሏት ሮጦ ከጨካኞች ሲያመልጥ እንኳን በደከመ ሰውነቷ ወደ ተቃውሞው ለመመለስ ፍላጎት ነበራት . . . ማርች 9 የሴቶች ሩጫ ጊዜ ከጣይቱ ልጆች ጋር ከፊት ሆና እየመራች የህወሓት ደህንነቶች አይን ውስጥ መግባቷ በምርመራ ወቅት ለረጅም ሰዓት ያቆዩአት ነበር . . .
የሆነ ሆኖ የወይንእሸት ሞላ ዛሬ በእጃቸው ድጋሚ ገብታለች . . . በመጥፎ ሁናቴም ተደብድባ ተጎድታለች፡፡ ደስተኛ እንደሆነች ግን ውስጤ ይነግረኛል . . . እሷ ነፃ ነች የውስጧን ጥያቄ መልሳ ሰላም አግኝታለች፡፡
በርካታ ሙስሊም ወገኖቻችንም ይህ ሰላምና እርካታ በመከራና በእስር ውስጥ ሆነው እንደሚሰማቸው አምናለሁ፡፡ ለእውነት በፍቅርና በይቅርታ የቆሙ አይወድቁም ነብዩም መሲሁም ያስተማሩን ይህን ነው!!! በርቱ!” በማለት ነበር የትላንቱን ውሎ የገለጸው። ዛሬ ደግሞ ሌላ ቀ ነው፤ ወይንሸት ክፉኛ ተጎድታ ጉዳይዋ በዝግ ችሎት ታየ። መልሰውም ወሰዷት። እኛም መጨረሻዋን ሰላም ያድርገው፤ በማለት እንሰናበታለን።

የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራር በዞኑ አቃቤ ህግ ይግባኝ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን አመራር በዞኑ አቃቤ ህግ ይግባኝ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ
**************************************************************
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በደቡብ ክልል የወላይታ ዞን የፓርቲው አመራር የሆኑት ወ/ሪት ሀዲያ መሀመድ ዓሊ አንድነት ፓርቲ በወላይታ ለሚያደርገው ሕዝባዊ ስብሰባ በፓርቲው የተዘጋጀ ፍላየር ከፓርቲው አባሎች ጋር በመሆን ሲያሰራጩ በፖሊስ ተይዘው መታሰራቸው የሚታወስ ሲሆን ጥር 8 ቀን 2006 ዓ.ም በወላይታ ዞን ፍ/ቤት ቀርበው በ1000. 00 /አንድ ሺህ ብር/ ዋስትና መለቀቃቸውን ፍኖተ ነፃነት መዘገቧ ይታወሳል፡፡
በወላይታ ዞን ከ/ዐ/ህግ ይግባኝ ባይነት ጥር 8 ቀን የተሰጠው ውሳኔ ተከሳሿ ጥፋተኛ የተባሉበት ወንጀል በዓለም አቀፍ ሽብርተኞች አስተሳሰብ ሲቀሰቅሱ የነበሩትን እንዳለ በመውሰድ ከአስተሳሰብ ባለፈ መልኩ በተግባር በአገራችን ውስጥ ተቻችሎ የመኖር ሁኔታ የሚያቃውስና ወደ ጦርነት የሚያመራ ጽሑፍ በርካታ ገፆች ይዛ የተገኙትን ግለሰብ በጥፋታቸው ልክ መቅጣት ሲገባ በጣም ዝቅተኛና ተመጣጣኝ ያልሆነ ቅጣት በመሰጠቱ ቅር ብሎኛል በማለት የስር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማሻሻል ከጥፋታቸው ጋር የሚመጣጠን ቅጣት እንዲሰጣቸው በማለት በወላይታ ከተማ ለሚያስችለው መደበኛ ተዘዋዋሪ ችሎት እንዲቀርቡ አዟል፡፡
በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች የተቃዋሚ ፓርቲ አባሎችን በማስፈራራት፣ በመደብደብና በማሰር ሀሰተኛ ምስክር አዘጋጅቶ ክስ መመስረት ለማሸማቀቅ የሚደረገው ሙከራ አባላትን እያጠናከረ እንጂ እነሱ እንደሚያስቡት እንዳልሆነ ለፍኖተ ነፃነት የገለጹት የፓርቲው አባላት ወደፊትም ሰላማዊ ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡

ረቡዕ 16 ጁላይ 2014

የመኢአድና አንድነት ውህደት አመቻች ኮሚቴ የባንክ አካውንቱን ይፋ አደረገ


የመኢአድና አንድነት ውህደት አመቻች ኮሚቴ ስራውን በቅልጥፍና እና በትጋት እየተወጣ መሆኑን ለፍኖተ ነፃነት የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በዚህም መሰረት ለጉባኤው መሳካት ይረዳ ዘንድ መላው ኢትዮጵያውያን እንዲተባበሩ ጥሪ በማድረግ የባንክ አካውንቱን ይፋ አድርጓል፡፡
የባንክ አካውንት ቁጥር አቢሲኒያ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ UDJ A/C 47
የባንክ አካውንት ቁጥር አቢሲኒያ ባንክ ቦሌ ቅርንጫፍ AEUP SP 235

ማክሰኞ 8 ጁላይ 2014

ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ለኢትዮጵያ ሕዝብ የቀረበ የሰላማዊ ትግል ጥሪ


“ኢትዮጵያን ለመታደግ በንቃት እንደራጅ!!

ዛሬ በረገፈ ዘውዱና በረገበ ዙፋኑ ላይ ያለ አቅሙና ያለ ህዝባዊ ይሁንታ የቆጥ ላይ እንቅልፍ የሆነበትን “ሥልጣን” የሙጥኝ ብሎ ያለው መካሪና ዘካሪ አልባው የህወሓት /ኢህአዴግ “መንግሥት” የሚንሊክ ቤተ-መንግሥትን ከተቆጣጠረ ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ የራሱን ስውር ደባ ለማስፈፀም በሚያመቸው መንገድ ጥንተ ገናናዋን፣ የዓለም የነፃነት ተምሳሌቷን፣ የጥበብና የሥልጣኔ ጮራዋን፣ የይሁዲ የክርስትና የእስልምና ማደሪያ የሆነች ምድረ ገነት የብዙሺህ ዓመት እመቤት ውዲት ሀገራችን ኢትዮጵያን ከፋሺስት ጣሊያን ተውሶ ባመጣው ሽንሸና በዘርና በቋንቋ አቧድኖ ላለፉት 22 ዓመታት በአሰቃቂ ጭቆና በግፍ ረግጦ ሲገዛህ ቆይቷል፤ ይህንን ህዝብን በሙልጭልጭ ሰንካላ ምክንያቶች በመከፋፈል /በመለያየት፣ በማባላት /በማናከስ፣ በመናቅ/ በማዋረድ፣ በማሸማቀቅ /አንገት በማስደፋት ለመዋሸት /በመቅጠፍ ላይ የተመሰረተ የእውር ድንብር አስተዳደሩን የሚቃወሙ ዜጎችን በማሳደድ፣ በመደብደብ፣ በመግደል፣ ከሥራና ከመኖሪያ በማፈናቀል፣ ያፈሩትን ሃብት በመዝረፍ፣ ከቤተሰብና ከትዳር በመለያየት፣ ዘብጥያ በማውረድ፣ በኃይማኖት ጣልቃ በመግባት ከፈጣሪያቸው በመለየት፣ ራሳቸውን እንዲያጠፉ በማድረግ፣ የገዛ ሃገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ ከፈተኛ ጫና በማድረግ “የነፍስ ውጪ የነፍስ ግቢ” የጣር እስትንፍሱን ለማራዘም ሲፍጨረጨር ቆይቷል እየተፍጨረጨረም ይገኛል፡፡
ህወሓት /ኢህአዴግ የአንባገነንነቱን በትር ከጨበጠበት እለት ጀምሮ ከራሱ መሰል ግለሰቦችና ተላላኪዎች በስተቀር ሌሎች ዜጐች በሀገራችን ባይተዋርና የበይ ተመልካች ሆነን ለአንዲት ቀን እንኳ ከኑሮ ግብግብ አፎይ ሳንል በምንጓዛት አንዲት እርምጃ ሁሉ እንቅፋት የተሞላው ድቅድቅ ጨለማ ሆኖብናል፡፡ በዚህም ምክንያት ቀደም የነበረን የውስጥ ደስታና የርስ በርስ ፍቅር አጥተን በአስከፊ ስቃይ ላይ እንገኛለን፡፡
የሀገሪቱ የፖለቲካ የኢኮኖሚና ማህበራዋ እንቅስቃሴ ፈፅሞ ፍትህ የጐደለው ከመሆኑ የተነሳ ጥቂት አፍቃሬ ህውሓት /ኢህአዴግ የሆኑ ግለሰቦች በአንድ ጀንበር ሚሊየኒየር ሲያደርግ አጠቃላይ ዜጐችን ደግሞ እያንደረደረ ወደ ድህነትና ድንቁርና የሲኦል አዘቅት ያለርህራሄ ይወረውራቸዋል፣ ከዚህም የተነሳ የመላ ሃገሪቱ አዛዥና ናዛዥ እነርሱ አንተ ደግሞ ሁሉ ነገርህን ተነጥቀህ ጭሰኛ ከሆንክ ሰነባብቷል፡፡
ይህንንም አገዛዝ ለማሰንበት ይቻለው ዘንድ የህወሓት /ኢህአዴግ አምባገነን “መንግሥት” በየጊዜው የሚያወጣቸውና የሚያፀድቃቸው ፌደራላዊም ሆነ ክልላዊ ፖሊሲዎች በሙሉ ለሀገርም ሆነ ለህዝብ ጥቅም ታስቦ ሳይሆን ለህወሓት /ኢህአዴግ የፖለቲካ ትርፍ እንዴት እንደሚያስገኙለት ታሳቢ በማድረግ ብቻ ነው፡፡ ይህ ሀገርንም ሆነ ህዝብን አጥፊ የሆነ ሒደት ተገቶ በአገራችን ኢትዮጵያ ለህዝብ ተጠያቂና ተገዢ፣ የሆነ መንግሥት ተቋቁሞ ዲሞክራሲ፣ መልካም አስተዳደር፣ ፍትሕ፣ ሰላምና ብልፅግና ማስፈን እንዲቻል መኢአድ “የስልጣን ምንጭ ሕዝብ ነውና!” ኑ! አብረን በሰላማዊ ትግል ህወሓት /ኢህአዴግን እናበርክከው እያለ ህዝባዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

የአንድነት ስራ አስፈፃሚ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠራ

የአንድነት ስራ አስፈፃሚ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠራ
**************************************************
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊና የመኢአድ እና የአንድነት የውህደት ጉዳዮች አመቻች ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆነው ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ ሀብታሙ አያሌው ዛሬ ጠዋት በመንግስት የደህንነት ሀይሎች መታገቱን ተከትሎ ፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው በምን ሁኔታ እንደሚገኝ ለማጣራት ያደረገው ሙከራ ባለመሳካቱ ምክንያት ስራ አስፈፃሚውን አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል፡፡ ስራ አስፃሚው ከስብሰባው በኋላ ጠንከር ያለ ፖለቲካዊ አቋም ይይዛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የአንድነት ፓርቲ ወጣት አመራሮችን የመሰር ዘመቻው ቀጥሏል

የአንድነት ፓርቲ ወጣት አመራሮችን የመሰር ዘመቻው ቀጥሏል
------------------------
የአንድነት ፓርቲ ም/የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ ዛሬ ጠዋት ሜክሲኮ አካባቢ በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች ከተያዘ በኋላ በአሁኑ ሰዓት አየርጤና አካባቢ የሚገኘው መኖሪያ ቤቱ እየተበረበረ እንደሆነ ለፍኖተ ነፃነት የደረሰው መረጃ አመልክቷል፡፡

አቶ ሀብታሙ አያሌው ተያዙ፤ እስካሁን ያሉበት ሁኔታም ሆነ ቦታ አልታወቀም

አቶ ሀብታሙ አያሌው ተያዙ፤ እስካሁን ያሉበት ሁኔታም ሆነ ቦታ አልታወቀም
+++++++++++++++++++++++++++++++
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው በዛሬው እለት ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ላይ ወደ ቢሮአቸው በማምራት ላይ እንዳሉ ደንበል አካባቢ የፖሊስ የደንብ ልብስ በለበሱ አካላት መያዛቸውን ከስፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች የገለፁ ስሆን እስካሁን የት አውንዳሉና በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ አልተቻለም፡፡

ቅዳሜ 5 ጁላይ 2014

የተቃዋሚ አባላትን ማሰር ማወከብና ማፈናቀሉ ቀጥሏል

--------------------------------------------------
በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የሚኖሩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አባሎች የሆኑት
- አቶ ሞላ ገረመው
- አቶ ብርሃኑ ገረመው
- አቶ ካሳሁን እንዳለ ከረቡዕ ሰኔ 18 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ የተቃዋሚ አባል
በመሆናቸው ብቻ የሚያርሱትን መሬት ቀምተው አሳርሰውባቸዋል፡፡ ለምን እንቀማለን ዜጎች አይደለንም ወይ ብለው ተቃውሞ
ሲያሰሙ ከፓርቲው ለቃችሁ ካልወጣችሁ መሬታችሁ አይመለስም በማለት የቀበሌው ሊቀመንበር አቶ ፀጋዬ ጎሹ አስፈራርተዋቸዋል፡፡
እንዲሁም በምዕራብ ጎጃም በይልማና ዴንሳ ወረዳ (አዴት) የሚገኙ የመኢአድ አባላት ላይ እስርና አፈና የተፈጸመ ሲሆን አቶ በቃሉ
ደፋሩ የተባሉ የወረዳው አባል ከሳምንት በፊት በፖሊስ ተይዘው እስካሁን ፍ/ቤት አልቀረቡም፡፡
በዚሁ ወረዳ - አቶ አትገኝ እምሬ እንዲሁም
- ቄስ ይሁን ዘለቀ ከሐሙስ ሰኔ 19ቀን 2006ዓ.ም ሌሊት ጀምሮ የደረሱበት አይታወቅም ሲሉ የመኢአድ
የህ/ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል፡፡

የተቃዋሚ አባላትን ማሰር ማወከብና ማፈናቀሉ ቀጥሏል
---------------------------------------------------------------------
በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የሚኖሩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አባሎች የሆኑት
- አቶ ሞላ ገረመው
- አቶ ብርሃኑ ገረመው
- አቶ ካሳሁን እንዳለ ከረቡዕ ሰኔ 18 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ የተቃዋሚ አባል
በመሆናቸው ብቻ የሚያርሱትን መሬት ቀምተው አሳርሰውባቸዋል፡፡ ለምን እንቀማለን ዜጎች አይደለንም ወይ ብለው ተቃውሞ
ሲያሰሙ ከፓርቲው ለቃችሁ ካልወጣችሁ መሬታችሁ አይመለስም በማለት የቀበሌው ሊቀመንበር አቶ ፀጋዬ ጎሹ አስፈራርተዋቸዋል፡፡
እንዲሁም በምዕራብ ጎጃም በይልማና ዴንሳ ወረዳ (አዴት) የሚገኙ የመኢአድ አባላት ላይ እስርና አፈና የተፈጸመ ሲሆን አቶ በቃሉ
ደፋሩ የተባሉ የወረዳው አባል ከሳምንት በፊት በፖሊስ ተይዘው እስካሁን ፍ/ቤት አልቀረቡም፡፡
በዚሁ ወረዳ - አቶ አትገኝ እምሬ እንዲሁም
- ቄስ ይሁን ዘለቀ ከሐሙስ ሰኔ 19ቀን 2006ዓ.ም ሌሊት ጀምሮ የደረሱበት አይታወቅም ሲሉ የመኢአድ
የህ/ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል፡፡

ከመኢአድ/አንድነት የውህደት አመቻች ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ!!!

የኢትዮጵያን ህዝብ የለውጥ ፍላጎት እውን ለማድረግ የመኢአድ እና የአንድነት መዋሀድ ወሳኝ የፖለቲካ ምዕራፍ ነው!!!
*****************************************

የኢትዮጵያን ህዝብ የለውጥ ፋላጎት ዕውን ለማድረግ የተቃዋሚው ጎራ በመሰባሰብ አንድ ግዙፍ አማራጭ ኃይል ወደ መገንባት ሊሸጋገር እንደሚገባ መላው የአገራችን ህዝብ ለረጅም ግዜ ሲያሳስብ መቆየቱ የሚታወቅ ነው፡፡
በዚሁ መሰረትም ትግሉ የሚጠይቀውን የፖለቲካ ተክለ ቁመና ለመያዝ የመላ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የደረሱበትን ወሳኝ የፖለቲካ ምዕራፍ እውን ለማድረግ ከሁለቱም ፓርቲዎች በእኩል ቁጥር የተቀወከሉ አሥር አባላት ያሉት የውህደት አመቻች ኮሚቴ ተቋቁሞ የውህዱን ጉባኤ በስኬት ለማጠናቀቅ በርካታ ተግባራት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የውህደት አመቻች ኮሚቴው ሁለቱ ታርቲዎች በተናጠል የሚያካሂዱት እና በጋራ ውህዱ ፓርቲ የሚያደርገው ጉባኤ በተያዘለት ግዜ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ተግባር በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጂ የሁለቱ ፓርቲዎች መዋሃድ ከፍተኛ ስጋት የፈጠረበት ገዥው ፓርቲም ሆነ ሌሎች አካላት በውህደቱ ሂደት ላይ ተግዳሮት ለመደቀን በርካታ ጥረት እያደረጉ እንደሆነም አስተውለናል፡፡
ስለሆነም መላው የሀገራችን ህዝብ ጉዳዩን በንቃት እንዲከታተልና ገዥው ፓርቲ ከፍተኛ በጀት በመመደብ ከግሉ ሚድያ ጋር ተመሳስለው አፍራሽ ተልእኮ እንዲፈጽሙ ባደራጃቸው አካላት እና ሚዲያዎች ሁለቱ ፓርቲዎች የህዝብ ጥያቄ ለመመለስ የሚያደርጉትን ጥረት በማጠልሸቱ ተግባር ላይ እንዲሰማሩ እየተደረገ ያለውን ስውር ሴራ በጥንቃቄ ማየት እንደሚገባ ለመጠቆም እንወዳለን፡፡
የሁለቱ ፓርቲዎች መዋቅርም ሆነ ዋነኛ ባለቤት የሆነው የውህደት አመቻች ኮሚቴው መረጃዎችን በጥንቃቄ እንደሚከታተል እና ይፋ እንደሚደረግ እየገለፅን በአጭር ጊዜ ውስጥ ውህደቱን በማጠናቀቅ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ እንደምንሸጋገር ለመላው ህዝባችን እንገልጻለን፡፡ ስለሆነም በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ለውህደቱ መሳካት አስፈላጊውን የፋይናንስ፣ የማቴሪያል፣ የሞራልና የሀሳብ ድጋፍ በማድረግ ሀገራዊ ሃላፊነታችንን በጋራ እንድንወጣ ጥሪ እንቀርባለን፡፡
በ1997 ዓ.ም የታየውን የህዝብ የለውጥ ፋላጎት እና የፖለቲካ ተሳትፎ ዳግም ለመመለስ ሳንታክት እንሰራለን!!!
ከውህደት አመቻች ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
ሰኔ 26 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ

ሰኞ 23 ጁን 2014

የአምባገነኖችና ዴሞክራሲ ናፋቂዎች ግብግብ በአዋሳ


አዋሳ ሆይ እስከመቼ የዳንስ ከተማ ብቻ እንድትሆኝ ይፈረድብሻል? የፖለቲካ ከተማም ሁኝ እንጅ!!!
የህዝቡ የለውጥ ፍላጎት ገፍቶ በወጣ ቁጥር የአምባገነኖች መደናበር ያይላል፡፡ ሲደናበሩም ህግ ይጥሳሉ፣ ህዝብ ያሰቃያሉ፣ ሀገር ይበድላሉ፡፡ ግን እድሜ ልክ ዕየተጨቆኑ መኖር አይቻልም፡፡ ‹‹ተቀምጦ ከመኖር ቆሞ መሞት ይሻላል›› እንዲሉ፡፡ ቆሜ መሞት ይሻለኛል የሚሉ ዴሞክራሲ ናፋቂዎች እየበረከቱ ነው፤ እምቢ ከፈለግህ ይሄው እሰረኝ! የሚሉ ትንታግ ወጣቶች እየተፈጠሩ ነው፡፡
እንደዚህ እንድል ምክንያት የሆነኝ ‹በደቡብ ክልል› አዋሳ ከተማ አንድነት ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቶ ነበር፡፡ ህጉንም ጠብቆ ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቆም ነበር፡፡ ትናንት ይካሄድ ለነበረው የተቃውሞ ሰልፍም አዋሳ ካለው መዋቅር ጋር ተቀላቅለው ቅስቀሳ የሚያካሂዱ ትንታግ ወጣቶች ከአዲስ አበባ አዋሳ ገብተውም ነበር፡፡
ነገር ግን የአቶ ኃይለማርያምን በድጋፍ ወደ ስልጣን መምጣት ተከትሎ በተለይ በደቡብ የገዥነት መጥፎ ስሜት የተጠናወታቸው የታች ባለስልጣናት ህግ በአደባባይ እየደፈጠጡ ነው፡፡ ስለዚህ በቅስቀሳ ላይ የነበሩትን አባላትና አመራሮች አሰሩ፡፡ ዴሞክራት ወጣቶች ግን በእስሩ አልተበገሩም ‹‹ህጉን ጠብቀን አሳወቅን፣ የእውቅናውን ደብዳቤ መስጠት ይህን ሊሰራ የተቀመጠው አካል ድርሻ ነው፡፡ እውቅና ወረቀቱን የሚሰጠው አካል ስራውን ስላልሰራ እኛ ስራ ማቆም የለብንም፡፡›› በማለት ስራቸውን እንደሚቀጥሉ አሳውቀዋቸዋል፡፡ ይህ የሆነው ሐሙስ ነበር፡፡ አሳሪዎቹ ያለምክንያት ማሰራቸው ሲያስጨንቃቸው ማታውኑ ‹‹ነገ እንዳትቀሰቅሱ፣ ከቀሰቀሳችሁ እናስራችኋለን›› ብለው ይለቋቸዋል፡፡
ትንታጎቹ የዴሞክራሲ ናፋቂዎች ግን ህገ ወጡን ትእዛዝ አልተቀበሉም፡፡ ህገወጡን ትእዛዝ ከመቀበል መታሰር እንደሚሻል ወሰኑ፡፡ አርብ ጠኋትም ወደ ቅስቀሳቸው ገቡ፡፡ አሳሪዎችም ካቴናቸውን ይዘው መጡና አሰሯቸው፡፡ በአጠቃላይ በአዋሳ የሚገኙ አመራሮችንና አባላትን ከየቦታው ለቃቅመው አሰሯቸው፡፡ ሰልፉም በዴሞክራሲ ደፍጣጮች ጉልበት ለጊዜው ተስተጓጎለ፡፡
ግን ግን ‹‹መብቴን አሳልፌ ከምሰጥ መታሰርን እመርጣለሁ!!!›› የሚለውን የዚህ ትውልድ ቁርጠኝነት እንዴት ማሸነፍ ይቻላቸዋል???

ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ


በደቡብ ክልል በግንቦት 3/2006 በጐፋ ሳውላ በተደረገው የመኢአድ የተቃውሞ ሠላማዊ ሰልፍ ምክንያት በመኢአድ አባላት ላይ እየተፈጸመ ያለው የሰብአዊ መብት ጥሰት እንዲቆም እንጠይቃለን፡፡
ኢህአዴግ የግንቦት 3 ቀን 2006 ዓ.ም የጐፋ ሳውላ ሰላማዊ ሰልፍን እቅድ ከሰማበት ጊዜ አንስቶና ከሰልፍ በኋላም እጅግ አስከፊ የሰብአዊ መብት ረገጣ እየፈጸመ ይገኛል፡፡ ይህም የሰላማዊ ትግሉን ሂደት ከምርጫ 2007 የቅድመ ዝግጅት የዕለት ተዕለት ሥራው አንዱ ዲሞከራሲን የማጥፋት ተግባር በመሆኑ ለጐፋ አካባቢ ከተማ ፍ/ቤት ጀምሮ እስከ ወረዳ ፍ/ቤቶች ከፓሊስ ኃይል ጋር በመተባበር እያጠቁ ናቸው፡፡ ተግባሩን በምንከታተልበት ጊዜም ሊያነጋግሩን ፈቃደኛ አይደሉም የዜግነት መብታችንም እየረገጡ ይገኛሉ፡፡
የደምባ ጎፋ ወረዳ ፍ/ቤት ተከሳሽ ኮልታ ቀበሌ የመኢአድ አመራሮች 1ኛ. አቶ ባሻ በላይነህ እና አቶ በቀለ ዋና በወረዳው የኢህአዴግ ካድሬዎች በአቶ ለሌ ለበኔ ተልካ ማሳቸውን ተነጥቀው እና የፓርቲ ኘሮግራም ከእጃቸው ተቀምተው በሐሰት ክስ ወንጀል ተከሰው የብዙ ቤተሰብ አስተዳዳሪ የሆኑት ለ3 ወር ያህል ወደ ወህኒ ተወርውረዋል፡፡ በጌዜ ጎፋ ወረዳ፡- 12 የመኢአድ አባላት የቀበሌ መዋቅር በኃይል ማፍረስ፣ በራሳቸው ጊዜ ስልጣን መያዝ፣ ልማትን ማደናቀፍ፣ ሕገ-መንግሥቱን በኃይል ለመናድና የመንግሥት ንብረት ማውደም በሚል መጋቢት ወር 2006 ዓ.ም በፋይል ቁጥር 03673 ተከሰዋል፡፡
ይህንም በይግባኝ በአዋሳ ጠቅ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ጉዳያቸው እየታየ እያለ በቀን 26/09/2006 ዓ.ም ከሳውላ ማረሚያ ፍ/ቤት በደረቅ ፖሊስ ጣቢያ መልሰው በማሰር በድጋሚ በሦስት የወንጀል ክሶች ማለትም 1ኛ. ዕውቅና ያልተሰጠ ስብሰባ በማድረጋቸው 2ኛ. 226 የመኢአድ አባላትን በማሰባሰብ የመኢአድን መታወቂያ የያዛችሁ በሙሉ የልማት ሥራ እንዳትሠሩ በማለት አስተባብሯል፣ የመንግሥትን ትዕዛዝ እንዳይፈጸሙ በማለት የውንብድና ወንጀል ፈጽመዋል የሚሉ ናቸው፡፡ 3ኛ. በቡልቂ ከተማ ውሰጥ በመሆን በስልጣን ያለውን የመንግሥት መዋቅር ሳያስፈቅድ የፓርቲ መዋቅር በመዘርጋት አመራር በመሾም 226 አባላት በማደራጀት በሕገ-ወጥ መንገድ መዋጮ አሰባስቧል ተብለው ታስሯል፡፡
የአይዳ ልዩ ወረዳ ፍ/ቤት እነ አቶ አልታዬ ኤሶ 7 የመኢአድ አመራሮችና አባላትን በመንግሥት ላይ የሐሰተኛ ሐሜት በማነሳሳት በማለት በወረዳ ፋ/ቁ. 07417 ተከሰው በጎፋ አካባቢ ፍ/ቤት ፋይል ቁ. 10492 በተሰጠው ውሳኔ 1ኛ. በፋ/ቁ. 06362 በ16/09/05 የመንግሥት ሥራ አስናከሉ ከማለቱ በፊት ለ3 ወራት አስሯቸዋል፡፡ 2ኛ. በፍይል ቁ.06656 በቀን 09/05/2006 የሙታን ክብር በመንካት በሚል 300 ብር ተቀጥተዋል፡፡ 3ኛ. በፋ/ቁ. 06298 በቀን 27/06/05 በብር 150.00 ቅጣት ተከሰው ተቀጥተዋል፡፡ በ1ኛ ተከሳሽ ላይ 1 ዓመት በ8ኛ እና በ2ኛ ተከሳሽ ላይ 10 ወር በ3ኛ ተከሳሽ እና 5ኛ ተከሳሽ ላይ 9 ወር የተፈረደባቸው ሲሆን ይህ ድርጊት በቂም በቀልነት የተፈፀመ እየገለጽን፣ በመኢአድ ፓርቲ ተደራጅተው የመቃወም መብት አጥተው ሰላማዊ ትግሉን እንዲያቋርጡ የአፈና ተግባር እየተፈጸመባቸው ስለሆነ በአስቸኳይ እንዲቆም እንጠይቃለን፡፡
አንዲት ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)

ሰኞ 12 ሜይ 2014

መኢአድ ሳዉላ

መኢአድ ሳዉላ የተቃዉሞ ሰልፍ

 መኢአድ ሳዉላ
የተቃዉሞ ሰልፍ
ከ30000 ህዝብ በላይ በተቃዉሞ ሰልፍ ተገኝቶል፡፡
ፖሊስ እና የወያኔ ደህንነት ከፍተኛ ግፍ ፈጥሞል፡፡
የመኢአድ አመራሮች ኪሳቸዉ ሳይቀር ተፈተሸ፡፡
ደቡብ ኦሞ የትጥቅ ትግል ተጠናክሮል፡፡
የነፍጠኛዉ ቤዝ ደቡብ ነዉ ተባለ፡፡
ሰልፉ ከፍተኛ መሰዋትነት ተከፍሎበት በድል ተጠናቆል፡፡
ወያኔ የሞት ሞቱን ተፍጨርጨር፡፡
ሰላማዊ እንቢተኝነት በተግባር ዋለ፡፡
ቪዲወ እንለቃለን
ኔትዎርክ ሙሉ በሙሉ በሳዉላ ከተማ አልነበረም፡፡
ከምሽቱ 4 ሰዓት የመኢአድ አመራሮች ወላይታ ሶዶ ገቡ፡፡

 

ቅዳሜ 3 ሜይ 2014

Ethiopia: John Kerry raised concerns over the detention of bloggers

Ethiopia growth strains expose political fault-lines

US Secretary of State John Kerry yesterday raised concerns with the Ethiopian government about the detention in the past week of several journalists and bloggers. A number of opposition Blue Party members were also arrested last week ahead of a planned demonstration. US and other donor influence on the question of media freedom and repression of opposition is fairly limited, despite Ethiopia’s dependence on foreign aid. Nevertheless, the recent clampdown — coming amid a wave of protests by students at universities in the Oromo regional state against the pace of the capital city Addis Ababa’s expansion — highlights tensions created or exacerbated by the aggressive growth policies of the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF).

Secretary Kerry Speaks During News Conference in Ethiopia

በሰፊው የኦሮሞ ህዝብ እና ልጆች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ በአጽንኦት እናወግዛለን!!! ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በኢትዮጵያ የመሬት ስሪት ላይ ግልፅ አቋም እና ፖሊሲ ያለው ፓርቲ መሆኑ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ በዚህም መሰረት መሬት በሦስት መሰረታዊ አውድ ላይ እንዲመሰረት ይህም ማለት በወል፣ በመንግስትና በግል ይዞታነት እንዲከበር አቋም ይዞ ይታገላል፡፡ ነገር ግን ከወልና ከመንግስት ውክልና ውጪ ያሉት ይዞታዎች በግል ይዞታነት እንዲከበሩ አቋም ይዞ ይታገላል፡፡ ኢህአዴግ የገጠሩ መሬት የግል ከሆነ አርሶ አደሩ መሬቱን እየሸጠ ወደ ከተማ ይፈልሳል ብሎ ያምናል፡፡ ከምንም የተነሳ ስጋት ነው ባይባልም አንኳ ኢትዮጵያውያን ከመሬት ጋር ያለንን ስነልቡናዊ፣ ማህበራዊና ሁለንተናዊ መስተጋብርን ያላገናዘበና የተጋነነ ስጋት ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ከመሬት ጋር የተለየ ቁርኚት እንዳላቸሰው ለማወቅ ሞታቸውን ሲያስቡ እንኳ “የሀገሬ አፈር ይብላኝ” ሲሉ መመኘታቸው በቂ ማስረጃ ነው፡፡UDJ/Andinet party logo
ኢህአዴጎቹም በቀድሞ ስርዓት ሲተገበር የታገሉትን የመጨቆኛ መሳሪያ ለራሳቸው ሲሆን ተጠቀሙበት፡፡ የሆኖ ሆኖ ይህ የኢህአዴግ ስጋት እውነት ነው እንኳ ቢባል ኢህአዴግ የከተማውን መሬትስ የግል ይዞታ ያላረገው ከተሜው ወዴት እንዳይሰደድ ነው? ዋናው የገዥው ፓርቲ ፍላጎት መሬትን በጁ በማድረግ የዜጎችን ነፃነት በዚያኑ ያክል ለመሸበብ ነው፡፡ አርሶ አደሩም ሆነ የከተማው ህዝብ መሬት የኔ ነው ብሎ ካመነ ለኢህአዴግ ጫና ስለማያጎበድድ መያዣ ለማድረግ ነው፡፡ የህዝቡ የመሬት ባለቤትነት ቢረጋገጥ በመንግስትና ለኢንቨስትመንት በሚፈለጉ መሬቶች ላይ የመደራደር አቅሙ እጅግ ከፍ ይላል፡፡ መሬቱን በመልቀቁ በሚሰጠው ካሳ (ዋጋም) በቂ የኑሮ ዘዬ ሽግግር የሚያገርግበት አጋጣሚ ይፈጥራል፡፡ ይህ ሊሆን አልቻለም፡፡ በ02/ 08/ 06 ዓ.ም ቡራዩ አካባቢ በተደረገ የመሬት የሊዝ ጨረታ ለተነሺው አርሶ አደር በካሬ 10 ብር የታሰበለት መሬት በጨረታ በካሬ 17 ሺህ ብር መሸጡን ፓርቲያችን ያሰባሰበው ማስረጃ ያሳያል፡፡ በ10 ብር የታሰበለት አርሶ አደር የሚሰደደው በዚህ መልኩ መንግስት ሲቀማው እንጂ የመሬቱ ባለቤት ሆኖና ተደራድሮ በሚሸጥበት ወቅት አልነበረም፡፡
መሬት የምርጫ ድምፅ መያዣ፣ ለኢህአዴግ ገንዘብ ማሰባሰቢያ እና የድጋፍ ምንጭ ሆኗል፡፡ በቅርቡ በጉጂ ዞን ኦዶ ጉዶ አካባቢ ለ2007 ዓ.ም ምርጫ ሞዴል የተባሉ አርሶ አደሮች በቁጥር ከፍ እንዲሉ እንደሹመት ተሰጥቷቸው ሲያበቃ 500 ብር እንዲያዋጡ የመሬት ይዞታቸው ለማስፈራሪያነት መዋሉ እንደማሳያ ሊወሰድ ይችላል፡፡
በሌላ በኩል ምንም አይነት ህዝባዊ ውይይት ሳይደረግበት ከሰማይ ዱብ ያለው የአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የልማት መሪ ፕላን ያስቆጣቸው የኦሮሞ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሰልፍ በማድረጋቸው የደረሰባቸውን ህገ ወጥ ድብደባና እስራት አንድነት በእጅጉ ይቃወማል፡፡ ለእውነተኛ ልማት ነው እንኳ ተብሎ ቢታሰብ ኢህአዴግ ካለበት የተአማኒነት ችግር የተነሳ ተማሪዎቹ ለተቃውሞ አደባባይ ቢወጡ ተፈጥሯዊ እና ህገ መንግስታዊ መብታቸው ሊከበር በተገባ ነበር፡፡ ነገር ግን ሁሉን ነገር ካልጋትኳችሁ የሚለውና ለዴሞክራሲያዊ ሽንፈት የማይገዛው ኢህአዴግ በተማሪዎቹ ላይ ያደረሰውን እንቃወማለን፡፡ የታሰሩ ተማሪዎችም በአስቸኳይ እንዲፈቱም እንጠይቃለን፡፡ የኦሮሞ ተማሪዎችን በገፍ ከዩኒቨርሲቲ የትምህር ገበታቸው በማባረር የሚታወቀው የኢህአዴግ መንግስት ከዚህ ተደጋጋሚ ተግባሩ ታቅቦ ልጆቹን በአስቸኳይ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመልስ እንጠይቃለን፡፡
በአጠቃላይ መሬት የዜጎች መያዣ መሆኑ እንዲቀር እንታገላለን፡፡ ዜጎች በመሬታቸው የመደራደር እውነተኛ መብት ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ተቃውሞ የሚያነሱ ዜጎችም ድምፅ እንዲሰማ እናሳስባለን፡፡
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ
ሚያዚያ 22 ቀን 2006 ዓ.ም
አዲስ አበባ

ወያኔ የሚፈራው ምርጫ ወይስ ሕዝባዊ እምቢተኝነት (አመጽ)


በዚች አለም በሕዝቦቻቸው ላይ የሚፈነጩ አምባገነኖችን ለማስወገድ የሚደረጉ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ የወያኔ ዘረኛችን ለምን ሲያስደነብራቸውና በፍርሃት ሲያሸማቅቃቸው እንደሚኖር የሁሉም ሰው ጥያቄ ነው፡፡ የህውሃት ዘረኛ ቡድን በሕዝብና በሃገር ላይ የሚያደርሰው መጠነ ሰፊ ጥቃት ወይም ውድመት በተለያየ መንገድ ሕዝቡ ቅሬታውን ቢያሰማም እራሱ ለፈጠረው ዘርፈ ብዙ ችግር መፍትሄ ከመሻት ይልቅ የሕዝቡን ብሶት ለማዳፈን ሀላፊነት የጎደለው ተግባራትን እየፈፀመ ሃገርን የመበተን ስራውን ቀጥሎበታል፡፡The long youth march to freedom and dignity has begun in Ethiopia. It is beautiful.
በአዋጅ የተደነገጉ የሕዝብን አሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመደራጀትና የመሰብሰብ እንዲሁም ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብትን እየሸረሸሩና አዋጅን በተራ መመሪያ እየሻሩ የስቃይ ቀንበሩን ያከብዱበታል ፡፡በየትኛውም ሁኔታ ማለትም የሰብአዊ መብቱ የተረገጠውን፣ የሃገሬ ጉዳይ ያገባኛል ስላለ እንደ ሁለተኛ ዜጋ እየታየ የሚሰቃየውን የነፃነት ታጋይ፣ በስርዓቱ ብልሹና የተዝረከረከ አሰራር በኑሮ ውድነት እየማቀቀ ያለው የህብረተሰብ ክፍል ለጥያቄው ተገቢውን መልስ ወይ መፈትሄ ከመስጠት ይልቅ በተራ ካድሬያዊ ዲስኩር ከላይ ለዘረኛው ስርዓት ቃል አቀባይ ከሆነው ጠ/ሚ ተብዬው እስከ ልማታዊ ጋዜጠኛ ነን እስከሚሉት ድረስ በርሃብ ለጠወለገው ምስኪን ሕዝብ ጥጋብን፣ በገዛ ሃገሩ ፍትህ አጥቶ ለሚሰቃየው ፍትሃዊነትን እንዲሁም ሰብአዊ መብቱ ተገፎ ነፃነቱን ለተነጠቀው ሕዝብ ዴሞክራሲን ነጋ ጠባ ይሰብኩታል፡፡
ይህው የወያኔ ዘረኛ ቡድን ስለፈጠረው ሃገራዊ ቀውስ ብዙ ብዙ ቢባልም የዚህን መርዘኛ ስርዓት ሰንኮፍ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነቅሎ ለመጣል ከምርጫ ይልቅ ሕዝባዊ እምቢተኝነት(አመጽ) ስለመሆኑ ስርዓቱ በሚያሳየውና ከሚሰጋባቸው ነገሮች ለመረዳት ይቻላል፡፡
እንደሚታወቀው በተደጋጋሚ የተካሄዱት ምርጫዎች ከምርጫ 97 ውጪ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለወያኔ መሳሪያ ከመሆን ወጪ የስርዓቱ የአፈና መዋቅር ተቃዋሚዎችን የሚያወላዳ አልነበረም፡፡ ይህ ማለት ይካሄዱ የነበሩ ምርጫዎች በህውሃት ዘረኛ ቡድን በተጠና የአፈና እንዲሁም በዋነኝነት ምርጫን ምርጫ ሊያሰኙ የሚችሉ ገለልተኛ ተቋማት በጠቅላላ በስርዓቱ መዋቅር የተዋጡና የተተበተቡ በመሆናቸው ለመገናኛ በዙሃን ሸፋንና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ መደለያ ካልሆነ በስተቀር ምርጫው ሳይጀመር ውጤቱ የታወቅ እንደ ነበር ከማንም የተሰወረ አደለም፡፡ ስለሆነም የህውሃት ቡድን አምስት አመት ጠብቆ የሚመጣ ምርጫ ከላይ እንደተጠቀሰው ለአንዳንድ ግብአት ይጠቀምበት እንደሆን እንጂ ምርጫ ስለተቃረበ እንቅልፍ የሚያጣ አይመስልም ምክንያቱም የምርጫ አስፈጻሚ አካላት እስከ ፍትህ ስርዓቱ በእጁ ናቸውና፡፡
የልቁንም ለዚህ እኩይ ስርዓት የራስ ምታት የሚሆንበትና ሰላም የሚነሳው ሕዝባዊ እምቢተኝነት(አመጽ) ነው፡፡ በቃ የሚል ትውልድ ግፍና በደል ያንገሸገሸው ሕዝብ ለመሆኑ ማሳያ ይሆኑ ዘንድ አንዳንድ ነጥቦች እናንሳ፡፡
ከአመታት በፊት ቱኒዚያዊው ሙሃመድ ቡዋዚዝ የቢን አሊን አንባገነን መንግስት በሃገሩ በቱኒዚያና በሕዝቧ ላይ የሚያሳደረውን ዘርፈ ብዙ ችግር በመቃወም እራሱ ላይ ነዳጅ አርከፍክፎ ካቃጠለ በሗላ ቱኒዝያን ጨምሮ ሊቢያ፣ ግብጽ፣ የመን፣ እስካሁንም በነወጥ ውስጥ ያለች ሶሪያ የደረሰውን ሕዝባዊ እምቢተኝንትና በየሃገሩ የተለኮሰው አመጽ የወያኔን ዘረኛ ቡድን ያስፈራውና ያሸማቀቀውን ያህል አምስት አመት ጠበቆ የሚካሄደው የየስሙላ ምርጫ አላሸበረውም፡፡
ይህንንም ለመገንዘብ በዛን ወቅት ሟቹ መለስ ዜናዊ የወሰዳቸውን እርምጃዎች ማየት የበቃል፡፡ በመጀመሪያ የአረብን አለም አብዮት የሚዘገቡ አለም አቀፍ የመገናኛ ቡዙሃንን ማፈር ቀዳሚ ተግባሩ ነበር ሆኖም መረጃው በተለያየ መንገድ ሕዝብ ጋር መድረሱን የተረዳው ሟቹ ጠ/ሚንስትር የሕዝብን መንፈስ ለመሳብና ቤሔራዊ ስሜትን ሰቅጦ ይይዝልኛል ያለውን መላ ምቱ ዘየደ ባይሳካም ኤርትራን ለመውረር መዘጋጀቱን ማወጅ ነበር፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው አብዮቱ የኢትዮጲያንም በር እንዳያንኳኳ ካለው ከልክ ያለፍ ፍርሃት ነበር፡፡ ሆኖም ሕዝብ ኖሮውን እንጂ የወረራ ዲስኩር ችላ እንዳልው ሲረዳ በኤኮኖሚም በፖለቲካ እንዲሁም ሃገራችን ያላትን መልካም የውጪ ገንኙነት የላገናዘበ በተጨማሪም በባለሞያዎች በቃ ጥናትና ምርምር ያልተደረገበትን እስካሁንም ዘርፈ ብዙ ችግር አዝሎ የሕዝብ ኪስ የራቆተውን የአባይ ግድብን እንካችሁ ብሎ ሻማ አለን፡፡ የሟቹን አላማ ይህኛው በተወሰነ መጠን አሳካለት ሆኖም አብዮት የፈራው ወይም ሕዝባዊ እምቢተኝነትን የፈራው የህውሃት ዘረኛ ቡድን የማይገፋ እዳ ለሃገርን ለሕዝብ ትቶ ችግሩን ፍርሃቱ ፈታበት፡፡
በተጨማሪ ይህው ዘርኛ ቡድን በአለም ዙሪያ የተደረጉ የተሳካላቸው ምርጫዎችን እያነሳ የሰጋበት ግዜ አይታወስም፡፡ በአንጻሩ ምርጫ ያጭበረበሩ አምባገነኖችን ሕዝብ ሲቃወምና ድምጹን ለማስመለስ የሚያደርገውን የነፃነት ትግል አሉታዊ መልክ ሰጥቶ ባዘጋጃቸው የፖለቲካ ተንታኝ ተብዬዎች ውግዝ ከማርዮሰ ሲያስብላቸው ይውላል፡፡ በየትኛውም መልኩ የሚካሄዱ ሕዝባዊ እቢተኝነት(አመጽ) ከማውገዝ ወደ ሗላ ብሎ የማያቀው ይህ ስርዓት ሰሞኑን ዘጋቢ ፊልም መስራት በማይሰለቻቸው ልማታዊ ጋዜጠኞቹ ይቀርብ የነበረው የዚሁ የፍርሀትና እራሱን እየከፈነ ያለው ያበቃለት የህውሃት ዘረኛ ቡድን ቅዠት ነው፡፡
ቅዠቱ የቀለም አብዮት ይልና ከብርቱካናማው የዩክሬን አብዮት ጀምሮ ቬንዙዌላ የድርሳል አጠቃላይ ምልከታው አብዮት ወይም ሕዝባዊ እምቢተኝነት የሚከናወነው ሕዝብ ፈልጎት ሳይሆን ከምዕራባዊያን እዲሁም በምዕራባዊያን ሃገራት ከሚኖሩ ዜጎች ፈላጊነት የሚመነጭ ነው ይለናል ኸረ እንደውም እነዚሁ ምዕባዊያን የማይፈልጓቸውን መንግስታት የሚያሶግዱበት አንዱ መሳሪያ ሕዝባዊ አመፅ ነው በማለት ይቀጥላል፡፡ ሌላው የሚገርመው የ 97 ምርጫን ተከትሎ ሕዝብ የተቀማ ድምጹን ለማሰመለስ ያደረገውን እንቅስቃሴና ንጹሃን ወገኖቻችንን በዚሁ ዘረኛ ቡድን የተነጠቅንበት ትእይንትም እንደ ዘጋቢ ፊልሙ አገላለጽ በሌሎች ሃገራት እንደተደረገው ሁሉ በምህራባዊያንና በነዚሁ ሃገራት በሚኖሩ ዜጎች የተቀነባበረ እንደሆነ ያትታል፡፡ የሚገርመው ታዲያ ወያኔን ይህንን ያህል ዘመን በሕዝብ ጫንቃ ላይ ያስቀመጡት እነሱ ምዕራባዊያን ሆነው ሳለ ስጋቱን ምን እንዳመጣው ነው፡፡
ሕዝብ ለሚያቀርበው የመልካም አስተዳደር ጥያቄ፣ የፍትህ ጥያቄ እንዲሁም የዴሞክራሲና የነፃነት ጥያቄ ጀርባ ሰጥቶ በትምክህት መኮፈስ በቃኝ ለሚል ለውጥ ፍላጊ ትውልድ እሳት ላይ ነዳጅ እንደማርከፍከፍ ነው፡፡ የህውሃት ዘረኛ ቡድን አሁን የተያያዘው መንገድ ይህው ነው፡፡
ምን ያለበት ምን አይችልም እንደሚባለው የትም ይሁን የት መሰል የአመባገነኖችን ዙፋን የሚያነቃንቅ ሕዝባዊ አመጽ የሕውሃት ቡድን እራስ ምታት ነው፡፡ ሕዝብንም በመከፋፈልና በመለያየት የተጋው ፍርሃቱን ለማብረድ ነው፡፡ በተረፈ አምስት አመት ቆጥሮ የሚመጣን ምርጫ ያውም 99.6% ሊሰርቅበት የሚችል ለእርሱ በእርሱ የተከፈተ የምርጫ ስርዓት ያሰጋዋል ተብሎ አይገመትም፡፡ ከላይ እንደተገለጸው በፍርህት የሚያርደውም የሚያሶግደውም ሕዝባዊ እምቡተኝነት(ሕዝባዊ አመጽ) ነው፡፡ በተለይ አሁን ስርዓቱ በስብሶ እራሱን በገነዘበት ሰዓት ሊቀብረው የሚችል በኢትዮጲያዊነት ጥላ ስር በአንድነት የተደራጀ በቃ በሎ ነፃነቱ የሚያውጅ ተውልድ ነው!!!
ድል ለኢትዮጲያ ሕዝብ!!!

ክብርነቶ በተናገሩበት ሳመንት?

ሰኞ መያዚያ 13 2006 ባሌ ውስጥ የሁለት ንፁሀን ዜጎችን መገደል በመስማት ሳምንቱን ጀመርነው። አገዳደላቸው ወንጀላችሁን ከባድ ያደርገዋል። የመጀመርያው ልጅ በቁጥጥራችሁ ስር ነበር። በህግ አግባብ መጠየቅ ስትችሉ ነው በነጻ እርምጃ የገደላችሁት። አፉ ውስጥ ሽገጥ አስገብታችሁ ተኩሳችሁ። በሚቀጥለው ቀን ይህን ግፍ ዜጎች ስለተቃወሙ ሌላ ዜጋ ደግሞ በቀን ብረሀን ገደላችሗል።
ማክሰኞ መያዝያ 14 2006 አፋር ውስጥ አስር ንፁሀን ተገለዋል። ከቦታው ያንድ እህት ምስክርነት።” እኔ አራሴ የቆምኩት ስምንት እሬሳ ላይ ነው። ይህ የመጀመርያ አይደለም። በየቀኑ አምስት ልጅ፤ ስድስት ልጅ፤ ሰባት ልጅ፤ ስምንት ልጆች እየቀበርን ነው። ገዳዬች ፌደራል ፖሊሶች ናቸው። እጅግ ለጆሮ በሚከብድና በሚያሳዝን ሁኔታ ልጆ መገደሉ ሳያንስ ነብሰ ጡር እህትም በጽኑ ተጎድታለች። ይህቺ እህታችን ሳትሞትም አልቀረችም’”። በዚሁ ቀን ጋንቤላ ዲማ ላይ መከላከያ ሰራዊት አባለት አስገድደን ፍቶወት ካልፈጸምን ብለው ባስነሱት አንባጓሮ ከመከላከያ ሶስት ከፌደራል አንድ ሞተዋል። “ጋዜጠኛ መሳይ ዝሆኖች ሲጣሉ” ብሎ እንደገለጸው ይህ ገጠመኝ ቁጥሩ ከራት በላይ የሆኑ ንፁሀን ዜጎች ሂወት ያለአግባብ እንዲጠፋ አድርጓል ። ህጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚታገሉት ድርጅቶች ውስጥ ሰማያዊ ፓርቲ አስራ ስምንት አባላቱ ምንም ወንጀል ሳይሰሩ በዚሁ እለት ታስረውበታል። የአገሪቷ ህግ ተቃውሞ ለማድረግ ፍቃድ የማያሻ መሆኑን ቢደነግግም በዚሁ እለት አንድነት ፍቃድ ከለከልንህ ብላችሁታል።
እሮብ መያዝያ 15 ካመት በፊት ዴሬደዋ ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ በተያያዘ የታሰረ ዳንኤል ጎሳ የሚባል ዜጋ አሰቃይታችሁ ገድላችሗል። ይህ ወገን ደብደባ ሲፈፀምበት ነበር። ለእሬሳ ምርመራ ፖሊስ ከቤተሰቡ ጋር ወደ አዲስ አበባ ተልኳል። የተላከው ፖሊስ ገዳዩ እራሱ አለመሆኑ የታወቀ ነገር የለም። የሬሳ ምርመራው አምስት ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ተጠናቋል። ሐኪምቤቱ የሬሳ ምርመራ ውጤት ቅጂውን እንኳ ለቤተሰቡ አልሰጥም ነው ያለው። ባንፃሩ አባት አበበ ጎሳ ልጄን ገድሏል ብለው ከጠረጠሩት አካል ነው የምርመራውን ውጤት ያገኛሉ የተባሉት። አቶ አበበ ያላቸው አንድ ልጅ ብቻ ነው። እሱኑ ነው የገደላችሁባቸው። ልጅ የሙት ልጅ ነው። አባት በወንድ አቅማቸው ብቻቸውን ሆነውና መከራ አይተው ያሳደጉት መሆኑን ተናግረዋል። እናንተ እንዳላችሁት እራሱንም ያጥፋ ወይ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ይገደል በናንተ እጅ እያለ ስለሞተ መንግስቶት ተጠያቂነት አለበት።
ሐሙስ መያዚያ 16 ጎንደር ጪንጋ ላይ ዜጎች ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ የመብት ጥያቄ ማንሳት ከጀመሩ ቀናቶች ተቆጥረዋል። ይህን ምክንያት አድርጋችሁ አራት ዜጎችን ገድላችሗል። እንዲሁ አንድ ፖሊስ ሞታል ሌላ ቆስሏል። ነዋሪው ተቃውሞ ሲያሰማ የነበረው መሳርያ ሳይዝ ስለነበር ህዝብ ፖሊሶቹ እርስ በእራሳቸው ተጋዳድለዋል እያለ ነው። እነዚህ ፖሊሶች የሞቱትም ሆነ የቆሰሉት በየትኛውም መንገድ ይሁን ወናው ጉዳይ እናንተ በተሸነፋችሁ ጊዜ ወይ ከዛም በሗላ አልቻልንም ብላችሁ ስልጣን ስላለቃቅችሁና ሁሌም ችግሮችን ሁሉ በምትፈቱበት የሀይልና ግጭት ያለበት መንገደ ምክንያት ስለሆነ አሁንም ለነዚህም ዜጎች ሞትም በቀጥታ ተጠያቂ ናችሁ። በዚሁ እለት የቆሰሉት ዜጎች ብዙ መሆናቸውና ባህር ዳር ሆስቢታል ልህክምና መግባታቸውን ሰምተናል። አስራ ስድስት ተጨማሪ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ማታሰራቸውንም በዚህ ቀን ነው የሰማነው።
አርብ መያዚያ 17 የሰላማዊ ፓርቲ ሰላሳሶት አባላት ሊቀመንበሩን ጨምሮ መታሰራቸውን ሰምተናል። እነዚህ ዜጎች ያለምንም ጥፋት የታሰሩት ለሰላማዊ ሰልፍ ህዘብን ሲቀሰቀሱ በነበረበት ጊዜ ነው። የጋዜጠኛ የሱፍ ጌታቸው ዘግናኝና ልታፍሩበት የሚገባ ግብራችሁን የሰማንበትም ቀን ነው። የዞን ዘጠኝ ስድስት አባላትም መታሰራቸውን የሰማነው በዚሁ ሳምንት ነው። መብራት አገልግሎት ለረጅም ጊዜ እያገኘን አይደለም ያሉ የሽሮ ሜዳ አካባቢ ነዋሪዎችን አፍሳችሁ አስራችሗል።
ቅዳሜና እሁድ ዜና ሰለሌ ነው እንጂ ግድያው፤ እስሩ፤ ማንገላታቱ ይኖራል። ግፋችሁን በማጋለጥ እንኳ እኩል ልንራመድ አልቻልንም። ጨርሼ ሳለቀው ሌላኛው ሰኞ መጥቶ ይህም ሳምንት እንዲሁ በመገደል በማሰር በማሸበር መጀመሩን እየሰማው ነው። በቀጣይ ያንድነት ሰላማዊ ተቃውሞ አለ። የስልምና እምንት ተከታይ ወንድሞቻችን ጥያቄያቸውን ለማስመለስ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ አለ። አስተዳድራችሁ አድሏዊ ሆኖ እያለ አዲስ አበባን እናስፋፋለን በሚል ደሀ ዜጎችን ከመሬታቸው ለማፈናቀልና ለማኝ ለማድርግ የዘየዳችሁት እቅድ መረረ ተቃውሞ ከዜጎች እየስነሳ ነው። ጎንደር፤ ጋንቤላ ባጠቃላይ በመላ አገሪቱ የለውጥ ፍላጎት እየተንቀለቀለ ነው። ሰንቱን ገድላችሁ፤ ስንቱን አስራችሁና አሰቃይታችሁ እንደምትወጡት የምናየው ይሆናል።
ይህን እንዳስብ ያደረገኝ ሰባቱንም ቀን በየቀኑ በግፍ ስለተገደሉ እንሰማባቸው የነበሩ ሳምንታት እጅግ ብዙ መሆናቸውን ስለታዘብኩ ነው። በሳምንት አምስቴ፤ ሶስቴ ወይ አንዴ መስማት የተለመደ ነው። የታሰረውን፤ ግፍና ስቃይ የተፈፀመበትን ወይ ያሰደዳችሁትን ዜጋ ጨምረን እንይ ካልን ይህን አይነቱ ወንጀል ሳይፈፀምና እኛም ሳንሰማ ያሳለፍነው ቀን ማግኘት አይቻልም። ይህ እንግዲህ የመገናኛ ሽፋን ለማግኘት የቻለው ብቻ ተወስዶ ነው።
በእርግጥ ንፁሀን ዜጎችን መግደል ማሰር ማሰቃየት ማሰደድ ትግል ላይ እያሉም ያለቆቾ ዋና ሞያቸው እንደነበረ ብዙዎች መስከረዋል። ሚኒልክ ቤተ መንግስት ከገባችሁ ሀያ ሶስትኛ አመታችሁ ላይ ናችሁ። ታዲያ ከሀያ ሶስት አመት በሗላ ዛሬስ ነጻ እርምጃን ማቆም ቻላችሁ ወይ ነው ጥያቄው?። የለመግባባቶችን፤ ልዩነትን ሳትገድሉን ዜጋውን ሳታሸብሩ መፍታት ትችላላችሁ ወይ ነው ጥያቄው?። ከላይ እንዳዩትና ልትክዱት የማያችላችሁ ይህ ችግር ከአመት አመት የሚጨምር እንጂ የሚቀንስ በጭራሽ አልሆነም። ስለዚህ መልሱ ባጭሩ አልቻላችሁም ነው። በእርግጥም ይህን የሀያሁለት አመት እብደት ላየ መግደልና ግፍ መፈፀም እንዳትችሉ እስክናደርጋችሁ ወንጀላችሁ አይቆምም ብሎ ድምዳሜ ዜጋው ላይ ባይደርስ ሲፈጥረው ጅላንፎ ሆኖ ነው ማለት ይቻላል። እርሶ እራሶ ዘላለማዊ ከብርና ሞገስ ብለው ማሀላ ፈፅመው ስልጣን ከያዙ በሗላ እንኳ ብዙ ንፅሀን ዜጎች በነጻ እርምጃ ተገለዋል። ያለጥፋታቸው ዜጎች በገፍ እየታሰሩና ስቃይ እየተፈፀመባቸው ነው። የታዘለች ህፃንም አልቀረላትም። ይህን አይነት መንግስታዊ ሽብር በሚፈፀምበት አገር ለአፍ ካልሆነ ፖለቲካ ማህደሩ ስፍቷልም ጠቧልም ብሎ መከራከር ልብ ድክም ማድረግ ነው።
በጠቅላላው የስልጣን ዘመናችሁ የፈፀማችሁት ፍጅት ቢወዳደር ከደርጉ የሚብስ ይመስለኛል። ምክንያቱም በዚህ ደረጃና በማያባራ ሁኔታ በየቀኑ በግፍ ስለሚገደሉ ስለሚታሰሩ ሰቆቃ ስለሚፈፀምባቸው ንፁሀን ዜጎች በኔ እድሜ ያኔ አይሰማም ነበር። በርግጠኛነት ግን እስቲ ቦንብ አፈንድተን ሀያ ሰላሳ ሰው እንግደልና የዜጋውን ስሜት እናጥና ወይ ፖለቲካ እንስራበት ብለው ፍጅት የሚፈፅሙ መሪዎች አልነበሩም።” ጦርነት ሰርተን” የምትባለው አለቆቾ የሚወዷት የጫወታ አይነትን ማለቴ ነው።
ደርጉም አንባገነን ስርአት ስለነበር ሰፈራ የመሳሰሉ ግብታዊና ጎጂ እቅዶችን ተግባራዊ አድርጓል። ዜጎች ያልተስማሙባቸውና አምርረው የተቃወሟቸው ቢሆንም እንደናንተ ያጉረመረመውን ሁሉ በገፍ መግደል ወና የቅዱ ማስፈፀሚያ ግን አልነበረም። ሰበብ አይሁን ለማለት ነው። ህንፃ ለመግንባት፤ መንገድ ለመስራት፤ አበባ ለመትከል የንፁሀን ሂወት እስርና ስቃይ የግንባታዎቹ ሁሉ መሰረቱ እኮ ነው የሆነው። ይህ የባህሪያችሁ ከመሆኑም በተጨማሪ ሁላችሁም ጋር ከፍተኛ የማስተዳደር እውቀት አለ ማለት ብቻ ነው የሚቻልው።
ክብር የሆነው ለሰው ልጅ ሂወት የሚሰጠው ዋጋ ከፍተኛ በነበረበት ዘመን ዜጎች ግዛው ለምን ለምን ሞተ? ማርታ ለምን ለምን ሞተች ብለው ጉሮሮ ሊይዙ ይደርሱ እንደነበር ያውቃሉ። ዛሬ ከአንድ እስከ አስር ዝም ብሎ ዜናችን ነው። ለምን ተብሎ መጠየቅ አይደለም ገደሏቸው እኮ ተብሎም በቀጣይ አናወራበትም። ሀምሳ፤ መቶና ሶስት መቶ አዲስ ቁጥር አየደለም። ከዚህ በፊት አድርጋችሁታላ። ያዋጣል ካላችሁ ግን ለወደፊቱም በርቱ። ይህን በሚመስል እውነታ ውስጥ ጊዜና ሁኔታ ይመቻቻል። ያኔ ገደላችሁ አይደለም ገላመጣቸሁ የስልጣናችሁን ፍፃሜ እንደሚያደርገው እነግሮታለው። ማወቅ ያለቦት የተለወጠ ነገር የለም ያው ኢትዬጵያዊ ነው።
በግሌ ስልጣኑ የያዙ ለት ያደረጉትን ንግግሮትን ካዳመጥኩበት ጊዜ ጀምሮ ሁሌም ሳዮትም ሆነ ስሰማዎት አብሮአደጌን ሞዘዘኝን ነው የሚያስታወሱኝ። በዛኑ ሰሞን በፃፍኩት ፅሁፍ ስለዚሁ ጉዳይ ልነግሮት ነበር። ሰው ናቸው የሚሉ ሲበዙ አልቸኩል ሊሆኑ ይችላሉ ብዬ ተውኩት። ይህን ክፍል ጎርጄ በሌላ ገፅ ላይ አኖርኩት። ዛሬ ኮፒ ፔስት ነው ያደረኳት። በርግጥ ሰበአዊነት ያለበትና ልጆቼ ተቆጡኝ። ፀለይኩኝም የምትለዋ ቃለ መጠይቆት አጭበርብራኝለች።
ልጆች ሆነን ከልጅነቱ ጀምሮ የመጨረሻ ገንገበት የነበረ ልጅ ነበር። ለዚህ ልጅ የሆነ ጊዜ ላይ ይህን ባህሪውን ያየ ሌላኛው አብሮ አደጌ ሞዘዘኝ ብሎ የቅጥል ስም አወጣለት። ገንገበቶች ገገማ ስለሆኑ እንደተጠመቀበት ወይ እንደሰለጠኑበት ጉዳይ ነው ለመሀበረሰቡ ጠቃሚም ጎጂም የሚሆኑት። አክራሪ የእምነት ሰው፤ ወይ ገገማ ቀልደኛ፤ ጨካኝ መርማሪ ወይ ለእውነት የሚሞት ዳኛ ወይ የሚያናድድ ሊስትሮ ጠራጊ ሊሆኑ ይችላሉ። ሞዘዘኝ ከፍ ሲል የሰፈር የጠብ ቡድን አገኘው። ከዛ አንዷን ጡቷ ላይ በጩቤ ወጋት፤ እትዬ እንትናን በድንጋይ ፈነከታቸው። የዛን ሰፈር ልጅ በብረት ሰንሰለት ቀጠቀጠው። ብቻ ስሙ ባንዴ ዝነኛማ ተፈሪም ሆነ። የጠብ ቡድን ውስጥ ደግሞ ድርሻቸው ማካበድና ማሟቅ የሆነ አሉ። ሀይ ሀይ ስለበዛበት ሞዘዘኝ እስታ ሊል አልቻለም። ቆያይቶ ተገደለ።
እርሶን ሳይ ትግሬ ተጋዳላዮች ምርጥ መጠቀሚያ ነው ከመንጋው መዘው ያወጡት እላለው። ገንገበቶችን እንዲሞቃቸው በማድረግ ብቻ እንደፈለጉ ሊነዷቸው መቻላቸውን አውቀዋል። የዚህ አይነት ሰዎችን ምንም አይነት ወንጀል ማሰራት ቀላል ነው። የሚፈልገው ጎሽ አበጀህ፤ አቤት ድፍረት፤ ለርሶ ሲሆን ባለእራዩም እንዲህ ሊያሳምረው አይችልም ነበር። እስከዛሬም ተሳስተናል አይነት ሙገሳን መጨመር ነው። በርግጠኛነት ከበቀደሙ የፓርላማ ውሎዎ መልስ ብዙዎች ይህን አይነት አስተያየት ሰጥተዎታል። ከዋኖዎቹ ለዚሁ ጉዳይ ተደውሎሎታል። ሙገሳ ያለበት ተመሳሳይ ነገርን ብለዎታል። ለሁሉም መልክቴን ጠቅላይ ሚንስትሩ ሞዝዘውኛል። ብዬ አቆማለው።

በጎንደር ተኩሱ ቀጥሏል፣ በግጭቱ 6 ሰው ሞቷል

May 1, 2014

Update:

ፖሊስ በነዋሪዎቹ ላይ የወሰደው እርምጃ ያስቆጣው የጎንደር ህዝብ በቁጣ የአጸፋ እርምጃ እየወሰደ እንደሆነ ከጎንደር የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በፖሊስ እርምጃ የተቆጡ ወጣቶች የፖሊስ መኪና በመሰባበር ላይ ናቸው ተብሏል፡፡ ህዝቡ በነቂስ እየወጣ ግጭቱ እየተባባሰ መሆኑንም ምንጫችን ጠቅሷል (ነገር-ኢትዮጵያ)

——————————
ነገረ-ኢትዮጵያ – ጎንደር ከተማ ውስጥ ቀበሌ 18 ልዩ ቦታ አርምጭሆ ሰፈር፣ ገንፎ ቁጭና ህዳሴ የተባሉ ሰፈሮች የከተማው አስተዳደር ‹‹ህገ ወጥ ሰፈራ ነው፡፡›› በሚል ቤቶችን ለማፍረስ መዘጋጀቱን ተከትሎ አፍራሾቹ ከህዝብ ጋር በፈጠሩት ግጭት ከ6 በላይ ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸውንና መታሰራቸውን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ግጭቱ ከሶስት ሰዓት እስከ አራት ሰዓት ተኩል ድረስ ቀጥሎ የነበር ሲሆን ምንጫችን ደውሎ በሚነግረን ወቅት (ከቀኑ 6፡ 43) ተኩስ እንደነበር ለመረዳት ችለናል፡፡
የአካባቢው ነዋሪዎቹ ሚያዝያ 7/2006 ዓ.ም ቤታቸውን እንዲያፈርሱ ትዕዛዝ በተላለፈበት ወቅት ህገ ወጥ አለመሆናቸውን፣ ካልሆነም መንግስት ቅያሬ ቦታና ጊዜ መስጠት እንዳለበት በመግለጽ አንለቅም ብለው እንደነበር ይታወቃል፡፡ በዛሬው ቀን ግጭቱ የተነሳውም አፍራሾቹ እንዲፈርሱ የተወሰነባቸውን ቤቶች ቀለም በመቀባታቸውና ህዝቡም እንዳይቀቡ በመከልከሉ መሆኑ ታውቋል፡፡
በግጭቱ ፖሊስ፣ ፌደራልና ልዩ ኃይል የተሳተፈበት ሲሆን ከተገደሉትና ከቆሰሉት በተጨማሪ የአካባቢው ወጣቶች ላይ ድብደባና እስራት እየፈጸሙባቸው እንደሆነ ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ‹‹ወጣቶችን እንደ እንሰሳ በአንድ ገመድ አስረው እየደበደቧቸው ነው፡፡ ህዝብ በጅምላ እየታሰረ ይገኛል፡፡ ግጭቱ ቢያቆምም በአሁኑ ወቅት በሶስቱም ሰፈሮች ጥይት እየተተኮሰ ነው›› ያሉት የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች የተወሰደው እርምጃ የጎንደርን ህዝብ በማስቆጣቱ ከዚህ የባሰ ግጭት እንዳይፈጠር ያሰጋል ሲሉም ገልጸውልናል፡፡ በግጭቱ ወቅት የመጀመሪያዋ የሞት ሰለባ የሆነችው ልዩ ኃይል ቤቷ እንዲፈርስ ቀለም ሲቀባ የተቃወመች የልጆች እናት እንደሆነችም ታውቋ፡፡

አንድነት ፓርቲ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ “የእሪታ ቀን” በሚል ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ይቀላቀሉ! (ግዛቸው ሽፈራው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር)

ጤና ይስጥልኝ
ግዛቸው ሽፈራው እባላለሁ። የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀመንበር ነኝ። አንድነት በኢትዮጵያ ሕጋዊ ፍቃድ አግኘቶ፣ በአገሪቷ ባሉ ክልሎች ሁሉ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀሰ ድርጅት ነው። አንድነት ከማንም ኢትዮጵያዊና ድርጅት ጋር ፀብ የለዉም። የአንድነት ፖለቲካ የኢትዮጵያዊነት፣ የፍቅርና የመቻቻል ፖለቲካ ነው። አላማችን ፣ የበለፀገች፣ ልጆቿ፣ በዘር ፣ በሃይማኖት፣ በጾታ ልዩነት ሳይደርገባቸው እኩል የሆኑባት፣ አንድነቷና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን መመስረት ነው።
አሁን በስልጣን ላይ ያለው የኢሕአዴግ መራሹ መንግስት፣ ግልጽነት የጎድለው፣ ተጠያቂነት የሌለው፣ በሙስና የተዘፈቀና የመልካም አስተዳደር ችግር ያለበት እንደመሆኑ፣ በሕዝብ ላይ ትልቅ በደል እያደረሰ ይገኛል። የሚከተለው የተሳሳተና ጎጂ የመሬት ፖሊሲ፣ ዜጎች፣ በልማት ስም፣ በቂ ካሳ ሳይከፈላቸው፣ ከቤታቸው እና ከእርሻ ቦታቸው በኃይል እንዲፈናቀሉ እያደረገ ነው። የሰብአዊ መብት ረገጣው፣ ተማሪዎች፣ ጋዜጠኞች የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ….. በግፍ መታሰራቸው፣ የኑሮ ዉድነቱ ሕዝቡ ከሚሸከመው በላይ እየሆነበት ነው።
ሕዝባችን ከዚህ የተሻለ ይገባዋል። ኢትዮጵያዉያን አሁን ያለውን አሳዛኝ ሁኔታ አንቀበለም በማለት፣ ለዉጥ መጠየቅ፣ ባለስልጣናትን ተጠያቂ ማድረግ ይኖርብናል።
ሕዝቡ ድምጹን ማሰማት የሚችልበት መድረክ ያገኝ ዘንድ፣ አንድነት፣ በሚመለከታቸው የመንግስት አካላት እውቅና ያገኘበት፣ ሁለት ታላላቅ ሰላማዊ ሰልፎች ፣ እሑድ ሚያዚያ 26 ቀን፣ በአዲስ አበባ እና በደቡክ ክልል በምትገኝ የድራሼ/ጊዶሌ አዘጋጅቷል። የአዲስ አበባ እና የጊዶሌ ነዋሪዎች፣ በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን እንዲያሰሙ በአክብሮት ጥሪ አቀርባለሁ። ነጻነት ነጻ አይደለም። ነጻነትን ከሌሎች አናገኝም። ነጻነትን እኛዉ እራሳችን ነን ለራሳችን ማወጅ የምንችለው። እራሳችንን በግል ካያነው፣ ምንም ማድረግ የማንችል፣ አንድ ተራ ሰው አድርገን ልንቆጠር እንችላለን። ነገር ግን ተራ ሰዎች፣ በሚሊዮን ሲቆጠሩ፣ እነርሱን ማነቃነቅ የሚችል ምንም ኃይል አይኖርም። እንነሳ። ሰልፍ እንዉጣ። ድምጻችንን እናሰማ። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን ! እራሳችንን ነጻ በማወጣት አገራችንን ነጻ እናውጣ!
እንግዚአብሄር አገራችን ኢትይጵያን ይባርካት
ግዛቸው ሽፈራዉ

UDJ Addis Ababa demonstration on May 4

“የፈሪ ዱላው አስር” ኢህአዲግ ፈርቷል። ለመሆኑ ኢህአዲግ ያሰራቸው ምንም አይነት ድብቅ አላማ የሌላቸው የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች እነማን ናቸው?

ጉዳያችን ብሎግ ፍርሃት የማያሰራው ነገር የለም።ኢህአዲግ በከፍተኛ የፍርሃት ማጥ ውስጥ ነው።ሁሉንም ይፈራል።አይዞህ አትፍራ ቢሉትም የሚችል አይመስልም።በሕዝብ ላይ የሰራቸው ሕዝብ የሚያውቃቸው እና የማያውቃቸው ብዙ ድብቅ ስራዎች ስላሉት የመፍራት ደረጃው ከዕለት ወደ ዕለት እየባሰበት እንጂ እየተሻለው አልሄደም። የሚደግፉትም ልያፅናኑት አልቻሉም።ከሚገባው በላይ ፍርሃት ሲያንቀጠቅጠው ሲመለከቱ እነርሱም ይብሱን ፈሩ።ብዙ የስርዓቱ ደጋፊዎች እና በሀብት የደለደሉቱ ሀገር ጥለው እየወጡ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።ይህ ደግሞ ሌላው የፍርሃት ገፅታ ነው።Get all the best tweets and latest buzz about freezone9bloggers
የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሌሎች ሰሞኑን የተያዙት ጋዜጠኞች ምንም የተደበቀ አጀንዳ የሌላቸው ግን ህገ መንግስቱ ላይ የሰፈረው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ይከበር ያሉ በእዚህም መስረት የሕገ መንግስቱን አንቀፅ እየጠቀሱ የሃሳብ የመግለፅ መብታቸውን የተጠቀሙ፣የሚሰሩት በመንግስት መስርያቤቶች የሆነ፣የሚፅፉት አይደለም ምን በልተው ከማን ጋር ውለው እንዳደሩ መንግስት ብቻ ሳይሆን ሕዝብ የሚያውቃቸው ኢትዮጵያውያን ናቸው።ከእዚህ በፊት በሃሳብ የሞገቱትን ሁሉ ”ህገ መንግስቱን እና ስርዓቱን ለመናድ የተንቀሳቀሱ” እያለ ሲያስራቸው የነበረው መንግስት ዛሬ እራሱ ህገ መንግስቱን አክብረው ሕግ እየጠቀሱ የፃፉትን በ20 ዎቹ እድሜዎች ውስጥ የሚገኙ ወጣቶችን ”ሃገርን በውጭ ከሚኖር ድርጅት ጋር ተመሳጥረው ሊያሸብሩ” እያለ ፌዝ አይሉት ቀልድ መሰል ክስ አቅርቦ ማዕከላዊ እስር ቤት አስገባቸው።ምንም አይነት ወንጀል እንደሌለባቸው እራሱ ኢህአዲግ ያውቀዋል።ግፍ መስራት የማይሰለቸው እና በፍርሃት የተዋጠ መሆኑ ግን የእዚህ አይነቱን ተግባር እንዲቀጥልበት አድርጎታል።
”የፈሪ ዱላው አስር” እንዲሉ የኢህአዲግ አባላት ማታ ኢቲቪ ዜና ላይ የግብፅ፣የየመንን በቅርቡ ደግሞ የዩክረንን የህዝብ ንቅናቄ እያዩ በሰላም መተኛት አልቻሉም።ያ ቀፎው እንደተነካ ንብ የሚተመው ሕዝብ አንድ ቀን እኛም ላይ ይነሳል የሚል ስጋት አድሮባቸዋል።ለእዚህም ማስረጃው ኢቲቪ ባለፈው ሰሞን ያሳየው የዩክሬንን አመፅ የተመለከተ ፊልም መጥቀሱ ይበቃል።ፍርሃታቸውን ደግሞ እነ ሚሚ ስብሃቱ ቀዝቃዛ ውሃ ውስጥ ገብቶ እንደሚንዘፈዘፍ ሰው እየተንቀጠቀጡ ሲናገሩ ሕዝብ ታዝቦ ”ወይ ፍርሃት” ብሏል።ግንቦት 20 ስመጣ ጀግና እንደነበሩ ከሃያ ዓመት በፊት የነበሩ አሮጌ ታንኮች ያሳየናል።መለስ ብለው ደግሞ በፈስ ቡክ እና በጡመራ ፈራን ይላሉ።አጀብ ነው።
ኢህአዲግ ፈራሁ ብሎ ያሰራቸው ንፁሃን ጦማርያን እና ጋዜጠኞች እነማን ናቸው? የወጣቶቹን የስራ መስክ ግልፅነት እና ሙያ ተመልክታችሁ ፍረዱ።ለፈሪዎችም እዘኑላቸው።
1/ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ
ለተባበሩት መንግሥታት ዜና አገልግሎት ኢሪን ለረጅም ጊዜ የሰራ የእንግሊዝኛው ‘ፎርቹን’ ጋዜጣ አምደኛ እና ዘጋቢ
2/ ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ
አዲስ ጉዳይ መፅሄት ከፍተኛ ኤዲተር
3/ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ
በአካባቢ ጥበቃ የሰለጠነች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ እና በቀድሞው ‘እንቢልታ’ ጋዜጣ ዘጋቢ
4/ በፍቃዱ ኃይሉ
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ፣ብሎገር እና ቅድስት ማርያም ዩንቨርስቲ በሙያው የሚሰራ
5/ አቤል ዋበላ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ የአየር መንገዱ ‘ግራውንድ ቴክኒሻን’
6/ ማህሌት ፋንታሁን
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ምሩቅ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሰራተኛ
7/ አጥናፍ ብርሃኔ
የ25 ዓመት ወጣት በፌስ ቡክ ሃሳቡን የሚገልፅ በብሎጉ ላይ ሃሳቡን የገለፀ
8/ ናትናኤል
የ 26 ዓመት ወጣት የኢኮኖሚ ባለሙያ፣’የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር’ አባል
9/ ዘላለም ክብረት
የሕግ ባለሙያ፣ማስተርሱን ከሰራ ገና ሳምንታት የሆነው በአምቦ ዩንቨርስቲ የሕግ ትምህርት መምህር ናቸው።
ምንጭ – ከጦማርያኑ ውስጥ በውጭ ሀገር የሚገኙት እንዳልካቸው እና ሶልያና ለቪኦኤ የአማርኛው አገልግሎት ሚያዝያ 20/2006 ዓም ከሰጡት መግለጫ የተገኘ።
ጉዳያችን
ሚያዝያ 21/2006 ዓም

ሰኞ 28 ኤፕሪል 2014

Ethiopia: Arrests Upstage Kerry Visit

(Nairobi) – The Ethiopian authorities should immediately release six bloggers and three journalists arrested on April 25 and 26, 2014, unless credible charges are promptly brought.

United States Secretary of State John Kerry, who is scheduled to visit Ethiopia beginning April 29, should urge Ethiopian officials to unconditionally release all activists and journalists who have been arbitrarily detained or convicted in unfair trials. The arrests also came days before Ethiopia is scheduled to have its human rights record assessed at the United Nations Human Rights Council’s universal periodic review in Geneva on May 6.

“The nine arrests signal, once again, that anyone who criticizes the Ethiopian government will be silenced,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “The timing of the arrests – just days before the US secretary of state’s visit – speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech.”

On the afternoon of April 25, police in uniform and civilian clothes conducted what appeared to be a coordinated operation of near-simultaneous arrests. Six members of a group known as the “Zone9” bloggers – Befekadu Hailu, Atnaf Berahane, Natnael Feleke, Mahlet Fantahun, Zelalem Kibret, and Abel Wabela – were arrested at their offices and in the streets. Tesfalem Weldeyes, a freelance journalist, was also arrested during the operation. Edom Kassaye, a second freelance journalist, was arrested on either April 25 or 26; the circumstances of her arrest are unclear but all eight individuals were apparently taken to Maekelawi Police Station, the federal detention center in Addis Ababa, the capital.

The police searched the bloggers and journalists’ offices and homes, reportedly with search warrants, and confiscated private laptops and literature. On April 26, another journalist, Asmamaw Hailegeorgis of Addis Guday newspaper, was also arrested and is reportedly detained in Maekelawi.

The detainees are currently being held incommunicado. On the morning of April 26, relatives were denied access to the detainees by Maekelawi guards, and only allowed to deposit food.

Human Rights Watch released a report in October 2013 documenting serious human rights abuses, including torture and other ill-treatment,unlawful interrogation tactics, and poor detention conditions in Maekelawi against political detainees, including journalists. Detainees at Maekelawi are seldom granted access to legal counsel or their relatives during the initial investigation phase.

The Zone9 bloggers have faced increasing harassment by the authorities over the last six months. Sources told Human Rights Watch that one of the bloggers and one of the journalists have been regularly approached, including at home, by alleged intelligence agents and asked about the work of the group and their alleged links to political opposition parties and human rights groups. The blogger was asked a week before their arrest of the names and personal information of all the Zone9 members. The arrests on April 25, 2014, came two days after Zone9 posted a statement on social media saying they planned to increase their activism after a period of laying low because of ongoing intimidation.

A Human Rights Watch report in March described the technologies used by the Ethiopian government to conduct surveillance of perceived political opponents, activists, and journalists inside the country and among the diaspora. It highlights how the government’s monopoly over all mobile and Internet services through its sole, state-owned telecom operator, Ethio Telecom, facilitates abuse of surveillance powers.

Kerry is scheduled to meet with Prime Minister Hailemariam Desalegn and Foreign Minister Tedros Adhanom in Addis Ababa “to discuss efforts to advance peace and democracy in the region.” Kerry should strongly urge the Ethiopian government to end arbitrary arrests, release all activists and journalists unjustly detained or convicted, and promptly amend draconian laws on freedom of association and terrorism that have frequently been used to justify arbitrary arrests and political prosecutions. The Obama administration has said very little about the need for human rights reforms in Ethiopia.

“Secretary Kerry should be clear that the Ethiopian government’s crackdown on media and civil society harms ties with the US,” Lefkow said.  “Continued repression in Ethiopia cannot mean business as usual for Ethiopia-US relations.”

እሑድ 27 ኤፕሪል 2014

Ethiopian to Demand John Kerry Raise Human Rights Issue


Demonstration to demand Secretary Kerry raise Human Rights Violations during his upcoming trip to Ethiopia and to show solidarity for jailed Semayawi (Blue) party members, Zone independent Journalists and all Political Prisoners.
Demonstration head of Secretary John Kerry's scheduled visit to Ethiopia.A protest demonstration has called for Monday April 28, 2014 in Washington, DC in front of the State Department ahead of Secretary John Kerry’s scheduled visit to Ethiopia. The protest rally is planned to show our solidarity with detained Semayawi Party members, recently arrested independent journalists and bloggers from Zone 9 group and political prisoners and to urge Secretary Kerry to make human rights and freedom of expression as one of his main topics of discussion during his stay in Addis Ababa.
It’s to be recalled that in the last few days, the TPLF lead Ethiopian regime has arrested over 50 Semayawi ( Blue) Party members ahead of their planned peaceful and legal protest rally on Sunday April 27. The regime is also tightening its suffocating grip on freedom of expression in a major crackdown with the arrest of numerous members from independent blogger and activist group ( Zone 9). With still a year to go before the “general elections”, the regime is tightening the screws on its iron curtain on freedom of speech, opinion and thought.
We urge Ethiopians and friends of Ethiopians in Washington DC metro and surrounding areas to join us to express our outrage at TPLF lead governments spiteful action against peaceful political party members, independent journalists and to demand release of political prisoners and to urge Secretary Kerry to make human rights and freedom of expression as one of his main topics during his upcoming visit to Ethiopia.

For more information contact
Semayawi Support-North America
P.O.Box 75860, Washington, DC 20013
semayawiusa.org
info@semayawiusa.org

ቅዳሜ 26 ኤፕሪል 2014

Ethiopia detains bloggers and journalist


 


The Ethiopian government has arrested six independent bloggers and a journalist in what human rights group Amnesty International has called a "suffocating grip on freedom of expression".
Six members of independent blogger and activist group ‘Zone 9’ and a prominent Ethiopian journalist were arrested on Friday in the capital Addis Ababa.

All six bloggers were arrested at night by armed security forces and taken from their homes to the Federal Police Crime Investigation Sector ‘Maikelawi’, where political prisoners are alleged to be held in pre-trial, and sometimes arbitrary detention.

The Zone 9 group who are said to be very critical of government policy and have a strong following on social media had temporarily suspended their activities earlier this year after accusing the government of harassing their members.

Journalist Tesfalem Waldyes who writes independent commentary on political issues for a Ethiopian newspaper was also arrested.

According to Ethiopian journalist Simegnish Yekoye, Waldyes is being denied visitation by friends and family and it's unclear what prompted his arrest and what charges he is being held under.

Simegnish Yekoye told Al Jazeera she was unaware of why the government had clamped down on journalists and their was growing fear on the future of a free press.

"I am very scared, I don't know what's going to happen next," she said.
Ranked 143 in the 2014 Reporters Without Borders press freedom index, media watchdogs say 49 journalists fled the country between 2007 and 2012 to evade government persecution.

uman rights group Amesty International criticised the arrests, saying "these arrests appear to be yet another alarming round up of opposition or independent voices".

"The Ethiopian government is tightening its suffocating grip on freedom of expression in a major crackdown which has seen the arrest of numerous independent, critical and opposition voices over the last two days", Claire Beston, Ethiopia researcher at Amnesty International, said.
Al Jazeera's Mohammed Adow reporting from Bahir Dar said it was unclear what will happen to the detained journalists.

"There are scores of journalists currently serving between 14 and 27 years in prison with some charged on terrorism offences."


Source : http://www.aljazeera.com/news/africa/2014/04/ethiopia-detains-bloggers-journalist-2014426163222797965.html 

ሰበር ዜና፣ ፖሊስ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ማሰሩን ቀጥሏል

በዳንኤል ሃረጋዊSemayawi party members on action
ፖሊስ ቀስቃሾቹን እያሰረ ነው ፖሊስ የእውቅናው ደብዳቤ አልደረሰኝም በሚል በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ቅስቀሳ ላይ የተሰማሩትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እያሰረ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በየካ፣ ካሳንቺስና አቧሬ ሲቀሰቅሱ የነበሩ ወጣቶች በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል፡፡ ቀስቃሾቹ ሰልፉ እውቅና እንደተሰጠው የሚያመለክተውን ወረቀት ለፖሊስ ቢያሳዩም ፖሊሶች የእውቅናው ደብዳቡ አልደረሰንም በሚል አስረዋቸዋል፡፡ ቀስቃሾቹ የያዙት የእውቅና ደብዳቤ ግልባጭ ለፖሊስ የተጻፈበት በመሆኑ ሰልፉ እውቅና አግኝቶ እያለ ሆን ተብሎ ለማደናቀፍ እንደሆነ ምክትር ሊቀመንበሩ አቶ ስለሽ ፈይሳ ገልፀዋል፡፡
በላም በረት፣ ቦሌ ድልድይ፣ ኮተቤ፣ መገናኛ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ቅስቀሳቸውን በተሳካ መልኩ አጠናቀዋል፡፡ በሌሎች አካባቢዎች የተሰማሩት አባላት ቅስቀሳውን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ በሌላ በኩል በየካ፣ ካሳንቺስና አቧሬን ጨምሮ በሌሎች የከተማይቱ ክፍሎች ፖሊስ ከ20 በላይ አባላትን ማሰሩ ታውቋል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ ፖሊስ ቅስቀሳው ላይ ያልነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችንም እያሰረ ነው፡፡ የታሰሩትን አባላትና ደጋፊዎች ሁኔታ ለማጣራት ወደ የካ ፖሊስ ጣቢያ ያቀኑ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ፖሊስ አስሯቸዋል፡፡
በዛሬው ቀን ካሳንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩት
1. ብሌን መስፍን
2. አስናቀ በቀለ
3. መስፍን
4. ተስፋዬ አሻግሬ
5. እዮብ ማሞ
6. ኩራባቸው
7. ተዋቸው ዳምጤ
የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች
1. ፍቅረ ማሪያም አስማማው
2. እያስፔድ ተስፋዬ
3. ጋሻው መርሻ
4. ተስፋዬ መርኔ
5. ሀብታሜ ደመቀ
6. ዘሪሁን ተስፋዬ
7. ጌታነህ ባልቻ
8. ንግስት ወንዲፍራው
9. ሜሪን አለማየሁ ናቸው
የካ አካባቢ ታስረው የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ምግብ እንዳይገባላቸው ተከልክለዋል፡፡ በሌላ በኩል አህመድ መሃመድ፣ሀይለማሪያም፣ ሱራፌልና አምሃ የተባሉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መገናኛ አካባቢ ተይዘው ወደ የካ ፖሊስ ጣቢያ ተዘዋውረዋል፡፡ በአጠቃላይ የካ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙት 14 መሆናቸው ታውቋል፡፡ በሁሉም ፖሊስ ጣቢያዎች የሚገኙት አመራሮችና አባላት በአሁኑ ወቅት ቃል እየሰጡ ሲሆን ሊያድሩ እንደሚችሉም ተነግሯቸዋል፡፡
በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ቢሮ ተደውሎ የሰላማዊ ሰልፉን አስተባባሪዎች ጧት ሁለት ሰዓት ላይ ‹‹ኑ እና እንነጋገር!›› የሚል ጥሪ አድርጓል፡፡ ከሰልፉ አስተባባሪዎች መካከል አቶ ጌታነህ ባልቻ ታስሮ ይገኛል፡፡

ሰበር ዜና፡ “ሰማያዊ ፓርቲ የእሁዱን ሰልፍ በታቀደው መሰረት ለማከናወን በሙሉ ቁርጠኝነት ላይ ይገኛል!!!”

ከአመራሩ በተጨማሪም የታሰሩ አባላት ዝርዝርSemyawi party leaders arrested
የካ ክፍለ ከተማ ሾላ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩ
1. ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት -የፓርቲው ሊቀመንበር
2. ስለሽ ፈይሳ- ምክትል ሊቀመንበር
3. ብርሃኑ ተክለያሬድ-የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
4. ዳዊት ጸጋዬ
5. አወቀ ተዘራ
6. ኢብራሂም አብዱሰላም
7. ሁሴን
8. ሙሉጌታ መኮንን
ጉለሌ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩ
1. ዮናስ ከድር
2. እየሩስ ተስፋው
3. እመቤት ግርማ
4. የሽዋስ አሰፋ
5. አበራ
6. አበበ መከተ
ካሳንቺስ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩት
1. ብሌን መስፍን
2. አስናቀ በቀለ
3. መስፍን
4. ተስፋዬ አሻግሬ
5. እዮብ ማሞ
6. ኩራባቸው
7. ተዋቸው ዳምጤ
ከየካ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ቤላ አካባቢ ተዛውረው ታስረው የሚገኙት
1. ፍቅረማሪያም አስማማው
2. እያስፔድ ተስፋዬ
3. ጋሻው መርሻ
4. ተስፋዬ መርኔ
5. ሀብታሜ ደመቀ
6. ዘሪሁን ተስፋዬ
7. ጌታነህ ባልቻ
8. ንግስት ወንዲፍራው
9. ሜሮን አለማየሁ
ስማቸው ያልደረሱን የታሰሩ ሌሎች ወደ 15 የሚጠጉ አባለት እንዳሉ(አድዋ ድልድይ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያና ለጊዜው ቦታቸውን ባላወቅናቸው ፖሊስ ጣቢያዎች ታስረው እንደሚገኙ) መረጃ ደርሶናል ስማቸው ሲደርሰን እናሳዉቃለን፡፡
በተጨማሪ መረጃ ህወሓት/ኢህአዲግ ሰልፉን በተለያየ መልኩ ለማደናቀፍ ቢጥርም ሰማያዊ ፓርቲ የእሁዱን ሰልፍ በታቀደው መሰረት ለማከናወን በሙሉ ቁርጠኝነት ላይ ይገኛል፡፡ የአመራሮችም ሆነ የአባላት እስር የምናደርገውን ትግል ከፍ አድርጎታል፡፡ የያዝነውን የሰላማዊ ትግል ስልትም ከዚህ በበለጠ አጠናክረን ወደፊት እንጓዛለን፡፡ እሁድ 03:00 ሰዓት ላይ ካሳንቺዝ እንደራሴ ሆቴል አካባቢ በሚገኘው በፓርቲያችን ጽ/ቤት ተገናኝተን ስለመብታችን በጋራ እንተማለን!
ኑ ራሳችንን ነፃ በማውጣት የሀገራችንን እጣ ፈንታ እንወስን
ሰማያዊ ፓርቲ!

ረቡዕ 26 ማርች 2014

Washington DC hosts Andualem Aragie’s book signing and celebration


“ከአንድነት ፓርቲ ጋር የሚደረገው ውህደት በግለሰቦች ደረጃ እንጂ በተቋሞቹ ውስጥ አልሞተም”

መጋቢት 11 ቀን 2004 ዓ.ም. በመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ መካከል የነበረው የቅድመ ፓርቲዎች ውህደት ሳይፈጸም ቀርቷል። ሁለቱም ፓርቲዎች አንዱ አንዱን እየከሰሱ ይገኛሉ።

በተለይ አንድነት በአመራሩ በኩል ከመድረክ ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን መግለፁ ለውዝግቡ መፈጠር በአይነተኛ ምክንያትነት ይጠቀሳል። መኢአድ በበኩሉ በብሔር ከተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በጋራ ለመስራት ፍላጎት እንደሌለው ከበፊቶቹ አመራሮች እስከ አሁን ፓርቲውን ከሚመሩ አመራሮች ጭምር ወጥ አቋም ሲያንፀባርቁ ይሰተዋላል። ከዚህ መነሻነት ከአንድነት ፓርቲ ጋር ውህደት ለመፈጸም የጀመሩት ጉዞ በአንዳንድ የአንድነት አመራሮች ተጨናግፏል በማለት መግለጫ አውጥቷል። እኛም ይህን የውህደት ልዩነት ከግምት በመውሰድ የመኢአድ ፕሬዝደነት የሆኑትን አቶ አበባው መሐሪን አነጋግረናቸዋል።

ሰንደቅ፡- ድርድሩ ለምን በተፈለገው ፍጥነት አልሄደም? ለድርድሩስ አለመሳካት በመሰረታዊነት የሚያነሷቸው ነጥቦች ምንድን ናቸው?

አቶ አበባው፡-በመጀመሪያ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሳወቅ የምፈልገው ድርድሩ አሁን በያዘው ቅርጽ ይሄዳል የሚል እምነት አልነበረንም። ሁሉም ነገር በቀና መንገድ ይጓዛል የሚል ጤናማ አመለካከት ይዘን ነበር ወደ ድርድሩ የገባነው። ሆኖም በእኛ ቀናነት ብቻ የሚሆን ነገር ባለመሆኑ ውህደቱ አለመሳካቱን ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል የሚል እምነት አለን።

ለድርድሩ አለመሳካት ቢያንስ ሶስት መሰረታዊ ነገሮች ማስቀመጥ ተገቢ ነው። አንደኛው፤ አንድነት ፓርቲ ከመድረክ ጋር በግንባር ለመስራት ፈቃድ የወሰደው ከምርጫ ቦርድ ነው። ይሄውም ከሌሎች ሶስት ፓርቲዎች ጋር በጋራ በምርጫ ሕጉ መሰረት ለመስራት አመልክተው ተፈቅዶላቸው እየሰሩ የሚገኙበት ሁኔታ ነው ያለው። ስለዚህም በመጀመሪያ ደረጃ ከመኢአድ ጋር ውህደት ለመፈጸም አንድነት ከመድረክ የግንባር አደረጃጀት መልቀቅ ይጠበቅበታል። አንድነት ከመድረክ መውጣት እስካልቻለ ድረስ ሕዝቡም እንደሚያውቀው ከመኢአድ ጋር መዋሃድ አይችልም። ምክንያቱም መኢአድ ከመድረክ ጋር ያለው ልዩነት ግልፅ በመሆኑ ነው። በእኛ በኩል በመጀመሪያ ከመድረክ ሙሉ ለሙሉ መውጣታችሁን የሚገልጽ መረጃ ስጡን የሚል ጥያቄ አቅርበናል። አያይዘንም ከእኛ ጋር ውህደት ከፈጸሙ፣ ከመድረክ ጋር በጋራ ሊሰሩ እንደማይችሉ አቋማችንን ግልጽ አድርገናል። እነሱም እንደሚገነዘቡት ውህደት ፈጽመን ወደ መድረክ በጋራ ልንሄድበት የምንችልበት አንዳችም ውለታ የለንም። ይህን መስመር ሊያጠራ የሚችል በአንድነት በኩል የቀረበ ማስረጃ የለም። ይህ በሆነበት ሁኔታ በጥድፊያ የቅድመ ፓርቲ ውህደት ፊርማ የምናኖርበት ሁኔታ ሊኖር እንደማይችል ገልጸንላቸዋል።

ሁለተኛው ነጥብ፤ በውህዱ ፓርቲ ውስጥ አስራ ዘጠኝ የሥራ አስፈፃሚ ቦታዎች ላይ እኩል ሃምሳ ሃምሳ ቦታ ይኑረን ብለናል። መኢአድ መዋቅራዊ አደረጃጀትና ስፋቱ የተሻለ መሆኑ ሁሉም ቢያውቀውም በመርህ ደረጃ ይህን ጥያቄ አቅርበናል። ሌላው፣ ለሊቀመንበሩ ቦታ ግልፅ መስፈርት ይውጣለት ለሚለውም ጥያቄ በምንም መልኩ መስፈርት ሊወጣ አይችልም የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን። በአጠቃላይ ሲታይ የድርድሩ ነጥቦቹ በግልፅ ሳይቀመጡ እና ውይይት ሳይደረግባቸው እንፈራረም ነው የሚሉት።ይህን መሰል አካሄድ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ ከዚህ በፊት ብዙ ተሞክሮዎች ስላሉ አልተቀበልነውም። ተመሳሳይ ስህተትም ለመፈጸም ዝግጁ አይደለንም።

ሰንደቅ፡- በውህደቱ ላይ የጊዜ ጥያቄ ብቻ ነው ያላችሁ?

አቶ አበባው፡- የጊዜም የሕግም ጥያቄ ነው ያቀረብነው። ጊዜ ለምትለው በአንድነት በኩል እነአቶ ብሩ ቢያንስ የቅድመ ፓርቲው ፊርማ ለመጋቢት 18 ይሁን የሚል መቃወሚያ አቅርበው ነበር። ኢንጂነር ግዛቸው ፈጽሞ አይሆንም የሚል ምላሽ አቅርበው በግድ ለመጋቢት 11 ነው የሆነው። መሰረታዊ ነጥቡ ግን አንድነት በመድረክ ላይ የሚከተለው ግልፅ ያልሆነ አካሄድ ነው። የሚገርመው የተፈጠሩትን ችግሮች ለመመልከት ከሥራ አስፈፃሚዎች መካከል አቶ ካሳሁን አበባ፣ አቶ ሲራክ አጥናፉ እና አቶ ገለቱ ጀጀርሳ የደቡብ ቀጠና አስተባባሪን ልከን ከኢንጅነሩ ጋር ውይይት እንዲያርጉ አድርገናል። በውይይቱም ከስምምነት ለመድረስ የቻሉ ቢሆንም፣ ከተስማሙ በኋላ መኢአድ ድርድሩን አፈረሰው የሚል መግለጫ ማምሻውን ማውጣታቸው በጣም አሳዛኝ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው። በተለይ ይህን መሰል ጥድፊያ የሚያሳየው፣ ከጀርባቸው የተለየ ተንኮል መኖሩን ነው።

ሰንደቅ፡- ከእርስዎ መረዳት አንፃር፣ የአንድነት ፓርቲ አቀራረብ ስትራቴጂክ ወይንስ ስልታዊ ነበር?

አቶ አበባው፡-እየተፈጸመ ካለው ሁኔታ የተረዳሁት ሂደቱ በሙሉ የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ ወይም የምክር ቤቱ አካሄድ አይደለም። የግለሰብ እርምጃ ነው ጎልቶ የወጣው። በግለሰቦች እይታ ድርድሩ የሞተ ነው የሚመስለው። በፓርቲዎቹ በኩል ግን የሞተ ነገር አለ፣ የሚል እምነት የለኝም። በተለይ የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ እየሆኑ ያሉትን ነገሮች በጥልቀት ያወቃቸው አልመሰለኝም። የግለሰቦች ማፈግፈግ፣ መቁነጥነጥ ከተመለከትነው ግን የአንድነት አካሄድ ስልታዊ እንጂ ስትራቴጂካዊ አካሄድ አድርጎ ለመቀበል በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ነው ያለው።

ሰንደቅ፡- በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል አደራዳሪዎች መኖራቸው ይታወቃል። አደራዳሪዎቹ ይህን ችግር ሊፈቱት አልቻሉም? በምንስ አግባብ ነው የአደራዳሪነት ሚና የወሰዱት?

አቶ አበባው፡- መታወቅ ያለበት እነዚህን አደራዳሪዎች ኢንጅነር ግዛቸው ናቸው መርጠው ያመጧቸው። ቤታችንን አንኳኩተው የገቡት እራሳቸው ናቸው። እኛ አልመረጥናቸውም። እናሸማግላችሁ ሲሉን ነው ያየናቸው። መልካም፣ ለማሸማገል ከሆነ ብለን ተቀበልናቸው። በሂደት ግን ነገሩ ሁሉ የተገላቢጦሽ ነው የሆነው። ይህን ስል ግን ሁሉንም ሽማግሌዎች ማለቴ አይደለም።
ሰንደቅ፡- መኢአድ ባልመረጣቸው ሽማግሌዎች ለመደራደር መዘጋጀቱ በየዋህነት የሚወሰድ ነው ወይንስ የፖለቲካ ስህተት መሆኑን ይቀበላሉ?

አቶ አበባው፡-በእኛ በኩል የነበረው፤ እነዚህ ሰዎች ሙሁራን ናቸው። ለሀገር አስበው ነው ከሚል ቀና መነሻ ነው የተቀበልነው። በጀርባ በኩል የሚመጣ ነገር አለ ብለን አላሰብንም። እየወቀስኩ አይደለም፣ መጡብን ብቻ ለማለት ነው። በቀና ልቦና ነገሮችን መውሰድ በእኔ እምነት የፖለቲካ ስህተት አይደለም።

ሰንደቅ፡- በሌሎች ባለድርሻ አካላት የሚቀርበው ውህደቱ ሀገር በቀል ሳይሆን ውጭ ባሉ አካላት የተፈበረከ በመሆኑ ነው፣ ለአለመስማማት የዳረጋቸውም ከውጪ የመጣ ስለሆነ ነው እየተባለ ነው። በዚህ ላይ የእርስዎ ምላሽ ምንድን ነው?

አቶ አበባው፡- ትክክል ነው። ሆኖም ውህደቱን ሕዝቡ ይፈልገዋል። ዋናው ነጥብ መታየት ያለበት ይህ ይመስለኛል። ነገር ግን ከሁኔታዎች መነሻነት ከተመለከትነው የውህደቱ ጥንስስ ከውጪ ተቀምሮ የመጣ ነው የሚለው ጥርጣሬ ሚዛን የሚደፋ ነው። ስትራቴጂው የተነደፈው ውጪ ነው። ሀገር ውስጥ ያሉት አስፈፃሚዎች ናቸው። በእውነተኛ ፍላጎት የመጣ የድርድር ሂደት ቢሆን ስህተት ማንም ይስራ ማንም በትዕግስት ውህደቱን መፈጸም እንጂ ይቋረጥ የሚል የተጣደፈ የአደባባይ ምላሽ አይሰጥም። በእኛ በኩል ውይይቱ ይቀጥል እያልን እየጠየቅን በር ዘግተውብን ጥለውን ባልሄዱ ነበር። ስለዚህ የውህደቱ ቅመራው ያለው ውጪ ሀገር ነው።

ሰንደቅ፡- ቅመራው ውጪ ነው ብለው የሚያምኑ ከሆነ፣ እንዴት በዚህ ሂደት ውስጥ ተሳታፊ ይሆናሉ?

አቶ አበባው፡- ይህን ነጥብ በትክክል መመልከት ተገቢ ነው። የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ እና የምክር ቤት አባላት ሁኔታውን በጥልቀት ሳይመለከቱት በቀናነት በተቆርቋሪነት እየሰሩ ነው የሚገኙት። የቅመራው ባለቤቶች አንዳንድ ግለሰቦች ናቸው። መታወቅ ያለበት ከአንድነት ፓርቲ ጋር የሚደረገው ውህደት በግለሰቦች ደረጃ እንጂ በተቋም ደረጃ አልሞተም። በርግጠኛነት ሁለቱ ፓርቲዎች ይህን ስልታዊ ቅመራ በጋራ በመሆን እናከሽፈዋለን። ምክንያቱም ይህ አሁን እየተቀነቀነ ያለው አስተሳሰብ የግለሰቦች በመሆኑ ነው። እንዲሁም የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ የምክር ቤት አባላት ፍላጎት እንዳልሆነ ስለምንረዳ ነው። 

ሰንደቅ፡- በእናንተ አባላት የሚቀርበው ቅሬታ፣ አንድነት የመኢአድን መዋቅር ጠቅልሎ በመውሰድ ራሱን የበለጠ ለማደራጀት የሚፈልግ ፓርቲ ነው የሚል ነው፤ በዚህ ነጥብ ላይ ምን አስተያየት አልዎት?

አቶ አበባው፡- አንድነት መዋቅር አለው፣ የለውም የሚለው ክርክር እንደተጠበቀ ሆኖ፣ መኢአድ ያለውን መዋቅር ሰጥቶም ቢሆን ለሕዝባችን አማራጭ ፓርቲ መሆን በጋራ እስከቻልን ድረስ ብዙ ችግር የለውም።

ሰንደቅ፡- ሌሎች ወገኖች በበኩላቸው ገዢው ፓርቲ ሁለቱ ፓርቲዎች እንዳይስማሙ ሰርጎ ገብቷል እያሉ ነው የሚገኙት። ይህን ሃሳብ ምን ያህል ይጋሩታል?

አቶ አበባው፡- እንዲህ እንደሚባል እኛም እንሰማለን። የሚገርመው እኛ የተስማማነው ነገር ሳይኖር ገዢው ፓርቲ ምኑን ነው የሚያፈርሰው። አንድነት ከመድረክ ሙሉ ለሙሉ መውጣት አለበት ለሚለው ጥያቄ፣ አንድነት እንጂ ገዢው ፓርቲ ምላሽ መስጠት ያለበት አልመሰለኝም። መጠራጠሩ ግን ክፋት የለውም፣ ተጨባጭ ለማድረግ ግን ብዙ መስራት ይፈልጋል።

ሰንደቅ፡- በተደጋጋሚ ግለሰቦች እያሉ ነው። እነዚህ ግለሰቦች ለምን በይፋ በማሳወቅ አትታገሏቸውም?

አቶ አበባው፡- ጋዜጠኛ እንዲህ ብሎ አይጠይቅም። ከዚህ በፊት የነበረውን ቅንጅት ማን እንዳፈረሰው ታውቃላችሁ። ለምሳሌ ብርቱካን በእስር በነበረችበት ጊዜ ብርቱካን የታሰረችው በራሷ ችግር እንጂ በፓርቲ አይደለም። አዲስ ሰው መሾም አለበት ያለው ማነው? ከዚህ በፊት አንድነትን ከመድረክ ጋር ለማዋሃድ ሽማግሌ የነበሩት ሰዎች እነማን ናቸው? ከዶክተር ነጋሶ ጋር ከስምምነት የደረስንበትን ሰነድ አልፈርምም ያለው ማን ነው? ለምንስ ተደራዳሪ የነበሩት እንዲነሱ ተፈለገ? ድርድሩ ከቆመበት መጀመር ሲገባው ለምን እንደአዲስ እንዲጀመር ተፈለገ? ከመድረክ ውጪ ሆነናል ተብሎ በአደባባይ ከተናገሩ በኋላ፤ መለስ ብሎ ጋዜጦችን ጠርቶ ከመድረክ ጋር እንሰራለን ማለት ምን ማለት ነው? የአንድነት ወጣት አመራሮች መድረክን በአደባባይ እየተቃወሙ፣ ግለሰቦች ግን ከመድረክ ጋር እንሰራለን ለምን ይላሉ? ስለዚሀም የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ እና ምክር ቤት ይህን እውነት ፈትሾ የውህደቱን ሂደት እንደሚቀጥል ተስፋ አለኝ። ይህ የማይሆን ከሆነም እንደበፊቱ በትብብር ለመስራት ዝግጁ ነን።

እሑድ 16 ማርች 2014

አንድነትና መኢአድ መጋቢት 11 የቅድመ ውህደት ፊርማ ሊያደርጉ ነው


የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት እና የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት አባላት በጋር ባካሔዱት ስብሰባ ሁለቱ ፓርቲዎች የፊታችን ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም የቅድመ ውህደት ፊርማ እንዲያደርጉ መመሪያ ማስተላለፋቸውን ስብሰባውን የተከታተለው የፍኖተ ነፃነት ባልደረባ ዘገበ፡፡







ሰኞ 3 ማርች 2014

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብት አያያዝ አብጠለጠለ

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብት አያያዝ አብጠለጠለ

የካቲት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መስሪያ ቤቱ በ2013 ሪፖርቱ በአገሪቱ የሚታዩ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን በዝርዝር አስቀምጧል። በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚታዩት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መካከል ሃሳብን በነጻነት የመግልጽና የመደራጀት መብት ቀዳሚ መሆኑን ሪፖርቱ ይገልጻል።
ዜጎች በዘፈቀደ ይታሰራሉ፣ ይታፈናሉ፣ በእስር ቤት ይሰቃያሉ፣ ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ ይገደላሉ፣ በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት ማስፈራሪያ ይደርስባቸዋል እንዲሁም በእስር ቤት ውስጥ አሰቃቂ ድርጊቶች ይፈጸሙባቸዋል።
ፍርድ ቤቶች በመዳከማቸው የፖለቲካ ፍለጎት ማስፈጸሚያ መሳሪያ መሆናቸውን፣ ዜጎች መንግስትን የመለወጥ እድላቸው አነስተኛ መሆኑን፣ ፖሊስ፣ አስተዳደርና ፍርድ ቤቶች በሙስና የተዘፈቁ በመሆናቸው ተጠያቂነት ያለበት ስርአት ማስፈን አለመቻሉን ሪፖርቱ ያስረዳል።
በእስር ላይ የሚገኙ ዜጎች ቁልቁል የፍጢኝ ታስረው የውስጥ እግራቸው እንደሚገረፍ፣ በውሃ ውስጥ እየገቡ እንዲሰቃዩ እንደሚደረግ፣ በእስር ቤት ውስጥ ድብደባ መፈጸምና ለህይወት አስጊ በሆነ እስር ቤት ውስጥ እንዲቆዩ በማድረግ መቅጣት በኢትዮጵያ የተለመደ ነው ብሎአል።
ከልካይ የሌለበት የሶማሊ ክልል ልዩ ሚሊሺያም ዜጎችን እንደፈለገ እንደሚገድልና እንደሚያስር፣ በክልሎች ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ልዩ ሚሊሺያዎችም እንዲሁ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ጉዳይ አስፈጻሚዎች መሆናቸውን አትቷል።
ከሁለት አመት በፊት ባለው አሃዝ በ6የፌደራልና በ120 የክልል እስር ቤቶች ከ70 እስከ 80 ሺ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ወንጀሎች መታሰራቸውን የገለጸው ሪፖርት፣ በይፋ የማይታወቁ በጦር ካምፖች ውስጥ ያሉ እስር ቤቶችንም ዘርዝሯል። ደዴሳ፣ ብር ሸለቆ፣ ጦላይ፣ ሆርማት፣ ብላቴ፣ ታጠቅ፣ ጅጅጋ፣ ሆለታና ሰንቀሌ ስውር እስር ቤቶች ተብለው ተጠቅሰዋል።
የኢድ አል ፈጥር በአልን ለማክበር በስታዲየም ላይ ተገኝተው በነበሩ ሙስሊሞች ላይ መንግስት በወሰደው እርምጃ ከታሰሩት ወደ 1 ሺ ከሚጠጉት ሰዎች መካከል የተወሰኑት በእስር ቤት ውስጥ መሞታቸውንም ሪፖርቱ ጠቅሷል።
የሙስሊም ጉዳዮች መጽሄት አዘጋጅ ሰለሞን ከበደ በእስር ቤት ውስጥ ድብደባ እንደተፈጸመበት የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ርእዮት አለሙ፣ በ አንዱአለም አራጌ፣ ኦባና ሊሌሳ፣ በቀለ ገርባና ሌሎችም የፖለቲካ እስረኞች ላይ እየደረሱ ያሉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን እንዲሁም በሴቶችና ህጻናት ላይ ስለሚደርሱ የመብት ጥሰቶች፣ በአናሳ ጎሳ አባላት ላይ ስለሚደረሰው መፈናቀልና ግጭት በዝርዝር አስቀምጣል።
የአሜሪካ ምክር ቤት የኢትየጵያ መንግስት የሰብአዊ መብቶች አያያዙን እስከሚያከብር ድረስ የ2014 እርዳታ እንዳይሰጥ  ህግ ማውጣቱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን ደረስ በዚህ ህግ ዙሪያ የሰጠው አስተያየት የለም።

ዓርብ 28 ፌብሩዋሪ 2014

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ………..

‹‹ የኢትዮጵያ ሃየር መንግድ ለአፍሪካ ኩራት ነው ›› ሲባል ከቃላት መፈክርነት ባለፈ የአውነትም ኩራት ስለመሆኑ ጥርጣሪ የሚያድርባቸው ዜጎች እንደሚኖሮ እገምታለው፡፡ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ አየር መንግድ በረዥም ታሪኩ ውስጥ ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች በአንፃራዊነት በተቋሙ ውስጥ ስማቸው እጅግ የገነነ ብቁ አብራሪዎች፣የቴክኒክ ባለሙያዎች (ግራውንድ ቴክኒሻን) እና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች በአብዛኛው በኢትዮጵያዊያን የተሞላ ነው፡፡ ለዚህም ነው የአፍሪካ ኩራት ለመባል የበቃው፡፡ ይህ ኩራት እና አድናቆት ከታላቁ አፍሪካዊ የነፃነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ጀምሮ ጥቂት በማይባሉ አፍሪካዊያን ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ ነው፡፡
በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሎሜ፣ማላዊ እና ቶጎ በመሳሰሉ የአፍሪካ አገሮች ከፍተኛ አክሲዮን ሼር በመግዛት እያስተዳደረ እና እያንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡እንዲሁም የተለያዩ የአፍሪካ አገር ተወላጆች በአብራሪነት እና በቲክኒሻንነት እያሰለጠነ ይገኛል፡፡ ይህ ደገሞ አየር መንገዱ በይለጠ በአፍሪካ እና በተቀሩት የዓላም አገራት ተቀባይነት ለማግኘት የሚያስችሉት መልካም ተግባራቶች ናቸው፡፡ እንዲ አይነቱ ለውጥ እና እድገት ለአገር ኩራት ስለመሆኑ ጥርጣሪ የሚያሳድር አይደለም፡፡ ይሁን እንጂ ከላይ የተገለፁት የአየር መንገዳችን መልካም ስራዎች በተቋሙ ውስጥ ለሚታዩ የአስተዳደር ችግሮች እና አየር መንገዱ ሊደርስበት ይገባው ለነበረ የእድገት ደረጃ አለመድረስ ምክንያቱ ምን እንደሆነ እና መሰል አሳቦችን አንስቶ ለመወያየት ብልጭ ድርግም የሚለው የአየር መንገዳችን እድገት የአሳብ ፍጭት ለማድረግ የሚገድብ አይደለም፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የራሱ የሆነ ድንቅ ታሪክ ያለው ነው፡፡ የአየር ኃይል ካፒቴኖቻችን እንደ ንስር አሞራ ከሰማይ ወደ ምድር በሚገርም ብቃት በመብረር ጠላትን እና የጠላት ሠፈርን አመድ በማድረግ የሚታወቁ ናቸው፡፡እንዲህ አይነቱ ግርማ ሞገስ ያለው የአገር ኩራት የሆነው ተቋም እና ተቋሙ ያፈራቸው ባለሙያዎች በወያኔ/ኢህዴግ መንግስት ቀጥተኛ ትዕዛዝ ለመፍረስ በቃ እንጂ፡፡ ተቋማትን አፍርሶ እንደ አዲስ መገንባት አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት የስርዓቱ ዋንኛ መገለጫ ነው፡፡ ለዚህም ነው ሁሉ ነገር እንደአዲስ የመጀመር መርዘማ የሆነ የኋላ ጉዞ ሙጥኝ ብለው የተያያዙት፡፡ የሰዎቹ አደገኝነት የሚጀምረው ኢትዮጵያ የምትባል አገር እንደ አገር መታየት ከጀመረች መቶ ዓመት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ነው ብለው የነገሩን ዕለት ነው፡፡ በዚህም መሠረት የኢትዮጵያን አየር ኃይል በማፍረስ አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በአዲስ መልክ እንዲቋቋም ያደረገ ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት እጅግ በጣም ድንቅ የሆኑ የአየር ኃይል ካፒቴኖቻችን ከአገር ለመሰደድ ተገደዋል፡፡
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት የአንድ ሳንቲም ግልባጭ የሆኑት የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አየር ኃይል ካፒቴኖቻችን ሽሽትና ምክንያት እንዲሁም ውጤት በአጭሩ ለማየት ከላይ የቀረበው አሳብ እንደመንደርደሪያን ሊያገለግል ይችላል፡፡
በአብዘኛው የአየር መንገድ ሠራተኞች በተለይ በአብራሪዎች እና በቴክኒሻኖች የሚነሳው ጥያቄ አስተዳደራዊ በደሎች ናቸው፡፡ እነዘህም ተመጣጣኝ የደሞዝ ክፍያ፣የሰራ እድገት እና የስራ ዝውውርን የሚመለከት ነው፡፡ ለምሳሌ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ የሚሰራ ኢትዮጵያዊ አብራሪ የወር ደሞዙ ትልቁ 7 ሺህ ዶላር ሲሆን ( ይህ የገቢ ግብር ጭምር የሚያካትት ነው) ለውጭ አገራት ዜጎች ግን ላቅ እንደሚል ሠራተኞች ይናገራሉ፡፡ በእርግጥ በኢትዮጵያ የኑሮ ሁኔታ ሲታይ የብሩ መጠን ከፍተኛ ነው፡፡ ነገር ግን ክፍያው የሚፈፀመው የኢትዮጵያ አየር መንገዱ አለም አቀፍ እንደመሆኑ መጠን አለም አቀፍ ደረጃ በጠበቀ መልኩ ነው መሆን ያለበት ፤ለዚህም ነው ወራዊ ደሞዝ በብር ሳይሆን በዶላር የሚከፈለው፡፡ይህንን መሠረት በማድረግ ነው የአየር መንገድ ካፒቴኖች ለስራቸው ተመጣጣኝ ክፍያ እንዲከፈላቸው የሚጠይቁት፡፡
ይሁን እንጂ ሠራተኞች እንደሚናገሩት አስተዳደሩ ለጥያቂያቸው ተገቢ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ‹‹ ስራውን መልቀቅ ትችላላችሁ ›› ነው የሚባሉት፡፡ በዚህም ምክንያት ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ዋና እና ምክትል አብራሪዎች ከአገር በመውጣት በተለያየ አገር የሥራ ብቃታቸውን እያሳዩ ይገኛሉ፡፡ ነገሩን የበለጠ ግልፅ ለማድረግ እንዲረዳ ይህን መመልከት በቂ ይመስለኛል ባለፈው ሳምንት ተጠለፈ የተባለው ET 702 አውሮፕላን ዋና አብራሪ የነበሩት ግለሰብ Air Italia ( Al-Itaia ) በተባለ የአየር መንገድ ድርጅት ውስጥ ሲያገለግሉ ቆይተው በውር 3 ሺህ ዶላር እየተከፈላቸው በጡረታ ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ እኚህ ግለሰብ በኢትዮጵያ አየር መንግድ ውስጥ 14 ሺህ ዶላር እየተከፈላቸው ይገኛል ፡፡
ሌላው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ አገራት ውስጥ ሎሜ፣ቶጎ እና ማላዊ እንዲሁም በተቀሩት ማህከላዊ ምዕራብ አፍሪካ አገራት ውስጥ ባለው ከፍተኛ የሼር መጠን የሚያንቀሳቅሳቸው እና የሚያስተዳድራቸው የአየር መንገድ ድርጅቶች አሉ፡፡ በእነዚህ የአየር መንገድ ድርጅቶች ውስጥ በቴክኒሻንነት የሚያገለግሉ ማንኛው የውጪ አገር ዜጋ ከ 3 እስከ 5 ሺህ ዶላር ክፍያ ያገኛል፡፡ነገር ግን ተመሳሳይ የት/ት እና የስራ ልምድ ያለው ኢትዮጵያዊ ቴክኒሻን የሚከፈለው 1 ሺህ ዶላር የማይሞላ ነው፡፡
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ድርጅት ውስጥ ሌላው በሠራተኞች ዘንድ ትልቅ ቅሬታ ሆኖ የሚነሳው የስራ ዝውውር እና እድገት ግልፅነት እና ተጠያቂነት የሌለው መሆኑ ነው፡፡ወደ ተሻለ የስራ ቦታ ለመዘዋወር እና የደረጃ እድገት ለማግኘት በአብዛኛው በቅርብ አለቃ መላካም ፍቃድ ላይ የተመሰረተ እንጂ የሥራ ውጤትን ግብ ያደረገ አይደለም ፡፡ ይህም ማለት በአየር መንገድ ድርጅት ውስጥ በሚኖሩ የስራ ክፍሎች በዋና ተጠሪነት የሚቀመጡት በአብዛኛው ለወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ቅርብ ከመሆናቸው በላይ ለስርአቱ ደም እና አጥንታቸውን የገበሩ ናቸው፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ ለሰራተኛ እድገት እና ዝውውር ዋንኛ መመዘኛ በማድረግ ተመልክተው ፍቃዳቸውን የሚሰጡት የሰራተኛው የስራ ልምድ እና የት/ት ዝግጅት በመመልከት ሳይሆን፣ ለወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ያለውን አመለካከት እና ጎሳን መሠረት ያደረገ ነው፡፡ ይህም በመሆኑ አብዛኛው የአየር መንገድ ሰራተኞች በድርጅታቸው ለሚታየው የአስተዳደር ችግሮች በቁጭት ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ የተቀሩት ደግሞ ሰራቸውን በመልቀቅ ከአገር ወጥተው ይገኛሉ፡፡
ይህ በእንዲ እንዳለ ከሰሞኑ ትልቅ አጀንዳ በመሆን መነጋገሪያ የሆነው የረዳት አብራሪ ሃይለመድህን አበራ የአውሮፕላን ጠላፍ ነው፡፡ የአውሮፕላን ጠላፍ ፖለቲካን መሰረት አድርጎ በአገራችን የተጀመረው ህዳር 29 ቀን 1965 ዓ.ም ሲሆን እነዋለልኝ መኮንን እና ማርታ መብራቱ ያካተተ ነበር፡፡የያኔው ጠላፋ ተሳክቶ ቢሆን ኖሮ ዋና አሳቡ ፖለቲካ ጥገኝነትን በመጠየቅ ከአገር ሸሽቱ ለመኖር ሳይሆን በጃንሆይ እና በአስተዳደራቸው ላይ ለተነሳው አመፅ የአውሮፕላን ጠለፋው የአመፁ የእስትራቴጂ አካል ጭምር ስለነበረ ነው፡፡
በእንዲ መልኩ የተጀመረው ፖለቲካዊ ይዘት ያለው የአውሮፕላን ጠለፋ በደርግ መንግስት ምን ያህል ተግባራዊ እንደሆን መረጃ ለማግኘት በእኔ በኩል ያልተቻለኝ ቢሆንም፤ነገር ግን የአውሮፕላን ጠለፋ በቁጥር እና በአይነት በዝቶ ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ጠለፋ የታየው በወያኔ/ኢህአዴግ የመንግስት የአስተዳደር ወቀት ስለመሆኑ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ እንዲሁም ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ የመንገደኛ እና የጦር አውሮፕላን ካፒቴኖች በተለያየ አገር የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቀው በመኖር ላይ ይገኛሉ፡፡
በእርግጥ የእነዚህ ካፒቴኖች የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቅ በራሱ የእውነት ፖለቲካዊ ይዘት አለው ወይስ የለውም ለማለት ተገቢ የሆነ ጥናትና እውነታን የሚጠይቅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ካፒቴን ተሾመ ተንኮሉ እና መስል አጋሮቹ በመንግስት ከደረሰባቸውን በደልና ግፍ በላይ በአገር ላይ የሚፈፀም በደል አላስችል ሲላቸው የፈፀሙት ገድል ሁሌም ታሪክ በበጎ የሚያስታውሰው ነው፡፡
ሌላው እና ለዚህ ጹሑፍ ዋንኛ መነሻ የሆነው አሳብ የረዳት አብራሪ ሃይለመድህን አበራ ጉዳይ ነው፡፡ እኔ ብቻ ሳልሆን ማንም ሰው በእርግጠኝነት ሊናገር የሚችለው አውሮፕላኑ ከአዲስ አበባ መነሳቱ እና ጄኔቫ ማረፉ ሲሆን፣ አውሮፕላኑ በጄኔቫ ያረፈው በታቀደው መልኩ ሳይሆን ከዚያ ውጪ በሆነ በረዳት አብራሪ ሃይለመድን አበራ ፍቃድ ብቻ መሆኑ ነው፡፡ከዚህ ውጪ ያሉ ነገሮች በአብዛኛው መላ ቅጡ በጠፋ መረጃ የተተበተበ ነው፡፡በማህበራዊ ድረ-ገፅ እና በተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች የሚነገሩ ነገሮች በአብዛኛው የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ደጋፊ፣ እንዲሁም ተቃዋሚም የሆን ሁሉ ዋንኛ መነሻ አሳባብ ከራስ ጥቅም እና ፍላጎት የመነጨ ነው፡፡ ይህም ስለመሆኑ የተነገሩት እና የተለቀቁትን መረጃዎች በማየት መገንዘብ ይቻላል፡፡
የነገሩን ውስብስብነት የበለጥ የሚያገላው ደግሞ የፓይለቱ ቤተሰቦች የሚሰጡት መረጃ ነው፡፡ ለማሳየነትም እንዲረዳ እህቱ ፣አክስቱ ፣ወንድሙ እንዲሁም የአጎቱ ባለቤት እና የቅርብ ጎደኛ በጉዳዩ ላይ የሚሰጡት ቃላቸው ፈፅሞ ሊቀራረብ የማይችል ነው፡፡ በተለይ ታላቅ ወንድሙ በአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ባደረገው ቃለ መጠይቅ በአብዛኞቻቸን ዘንድ ሞቅ አድርግን ይሆናል ብለን በገመትነው ነገር ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ነው የደፋበት፡፡
የረዳት ካፒቴን ሃይለመድን አበራ አውሮፕላኑን የጠለፈበት ምክንያት በእርግጠኝነት ልናውቅ የምንችለው ከራሱ በሚነገር እውነት ብቻ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ቀኑ የራቀ አይደለም ፤ስለዚህም ቀኑ ተጠብቁ ሙገሳውም ትችቱም ቢቀርብ ይበለጥ የተሻለ ይሆናል፡፡ እኔ በበኩሌ በዚህ ጉዳዩ ከመጀመሪያው ጀምሮ የያዝኩት አቋም ይህን ነው ፡፡
የዚህ ጹሑፍ ማጠቃለያ የሚሆነው በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚታዩ ችግሮች ዋንኛ ምክንያት የአስተዳደር የአቅም ውስንነት መሆኑ ነው፡፡ ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ቀጥተኛ የሆነ የመንግስት ጣልቃ ገብነት እና ብልሹ ፖለቲካዊ የአገር አስተዳደር ነው፡፡ በመሆኑም ሥራቸውን ብቻ በማየት በሥራቸው ለደረሰባቸው በደል አየር መንገዱን ለቀው ጥገኝነት የጠየቁ፡፡ እንዲሁም ከሚከፈላቸው ዶላር በላይ ስለአገራቸው እና ስለ ህዝብ ተቆርቁረው እንቢ ለሀገሬ ብለው ለተሰደዱ ለሁሉም ተጠያቂው በስልጣን ላይ ያለው የወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት ነው፡፡
ይድነቃቸው ከበደ