ማክሰኞ 19 ኤፕሪል 2016
ሰኞ 18 ኤፕሪል 2016
የመላው ኢትዮጲያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ) አመራሮች ዛሬም በሥቃይ ላይ ናቸው
የመላው ኢትዮጲያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ)
አመራሮች ዛሬም በሥቃይ ላይ ናቸው
የነጻነት የፍትህ የኩልነት
ታጋዮች ያለምንም ፍርድ...
በህወሓት ማሠቃያ ቤት እየተሠቃዩ ይገኛሉ
1ዓመት ከ7ወር ሙሉ ያለምንም ማሥረጃ
ያለምንም ፍርድ ታሥረው ይገኛሉ
የህወሓቱ ዳኛ የሁኑትን እሣቸው ዘንድ የቀረበን ሁሉም የፖለቲካ እሥረኛ ተበቂ በላይ ቢከላከል እንኳን መንግሥት ያለመረጃ አይከሥም በማለት ሣያገናዝቡ ፍርድ ይሠጣሉ ከድሜልክ እሥራት እሥከ ሞት በዚህ ፍርድ (አቡሃይ )ችግር የለባችውም እኒህን ዳኛ ይቀየሩልን በማለታቸው ምክንያት
ከታሣሥ 4/4 /2008 ጀምርው ያለምንም ውሣኔ በሥር ላይ ይገኛሉ
በሥር ላይ የሚገኙት ሥም ዝርዝር
በነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮነን የክሥ መዝገብ ላይ ያሉት 16 ሠዋች
1ኛ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮነን
2ኛ በላይነህ ሢሳይ
3ኛ አለባቸው ማሞ
4ኛ አወቀ ሞኝሆዴ
5ኛ ዘሪሁን ብሬ
6ኛ ወርቅየ ምሥጋናው
7ኛ ኣማረ መሥፍን
8ኛ ተሥፋየ ታሪኩ
9ኛ ቢሆነኝ አለነ
10ኛ ተፈሪ ፋንታሁን
11ኛ ፈረጀ ሙሉ
12ኛ አትርሣው አሥቻለው
13ኛ እንግዳው ዋኘው
14ኛ አንጋው ተገኘ
15ኛ አግባው ሠጠኝ
16ኛ አባይ ዘውዱ
እኒህ የህሌና እሥረኞች ያለምንም ማሥረጃ
በሥር እየተሠቃዩ ይገኛሉ
ህወሃት ሆይ
በማፈን በማሠር በመግደል ሠላም አይገኝም
የነጻነትን ጎህ ሣንቀናጅ በፍጹም ትግሉ አይቆምም
እኛ የተደራጀነው ይህን አሥከፊ አረመኔ ጨካኝ ሥርአት ለማሥወገድ ነውና
በቆራጥ አመራር በቆራጡ ህዝባችን ታጅበን
በበደኖ አርባ ጉጉ
በጋንቤላ ጉራ ፈርዳ
በመላ አገራችን እየተፈጸመ ያለውን የዘር መጽዳት ዘመቻ
ላንዴና ለመጨረሻ ግዜ ለማሥወገድ ነውና
ከፕሬፌሠር እሥክ ዶክተር
ካርሦ አደር እሥከ ሙህር
ከሹፌር እሥከ ርዳት
ከተማሪ እሥከ አሥተማሪ
ያለውን ያገራችንን ህዝብ አደራጂተው
ያሥረከቡንን
የነጻነት ፋና ቀዳጂ የሆኑትን ክቡር ፕሮፌሠር አሥራት ወልደየሥን
እሣቸው ጀምረው መሣውት የሆኑበትን ኣላማ ከዳር ለማድረሥ
እኛም ልጆቻቸው ጠንክረን እንሠራለን
እሥከ መጨረሻው
አንዲት ኢትዮጲያ ለዘላለም ትኑር!!!!!!
ረቡዕ 13 ኤፕሪል 2016
በኢትዮጵያ በአለም ደረጃ በጣም ውድ የሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት እንደምታቀርብ ተገለጸ
ኢትዮጵያ በአለማችን ካሉ ሃገራት መካከል የኢንተርኔት አገልግሎትን በጣም ውድ በሆነ ክፍያ በማቅረብ ግንባር ቀደም ሃገር ሆና መገኘቷን በጉዳዩ ዙሪያ ጥናትን ያደረገ አንድ የቴክኖሎጂ ተቋም ይፋ አድርጓል።
ይኸው የ120 ሃገራትን ታሪፍ በንጽጽር ያቀረበው ኑሚቢዬ የተሰኘው አካል በኢትዮጵያ ዝቅተኛ ፍጥነት ባለው የኢንተርኔት አገልግሎት ክፍያው የማይቀመስ መሆኑንም አመልክቷል።
የኢትዮ-ቴለኮም ባለስልጣናት ይህንኑ አገልግሎት ጨምሮ በቫይበር የሚደረግ የስልክ ጥሪ ልውውጥ ላይ ክፍያን ተግባራዊ ለማድረግ ምክክርን በማካሄድ ላይ መሆኑን ባለው ሳምንት ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።
በሃገሪቱ በብቸኝነት የስልክ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ኩባንያው በአገልግሎቱ ላይ አዳዲስ የቁጥጥር ስርዓቶችን ተግባራዊ ከማድረጉ ጎን ለጎን የተንቀሳቃሽ የእጅ ስልኮችንም ለመመዝገብ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል።
ይኸው የ120 ሃገራትን ታሪፍ በንጽጽር ያቀረበው ኑሚቢዬ የተሰኘው አካል በኢትዮጵያ ዝቅተኛ ፍጥነት ባለው የኢንተርኔት አገልግሎት ክፍያው የማይቀመስ መሆኑንም አመልክቷል።
የኢትዮ-ቴለኮም ባለስልጣናት ይህንኑ አገልግሎት ጨምሮ በቫይበር የሚደረግ የስልክ ጥሪ ልውውጥ ላይ ክፍያን ተግባራዊ ለማድረግ ምክክርን በማካሄድ ላይ መሆኑን ባለው ሳምንት ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።
በሃገሪቱ በብቸኝነት የስልክ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ኩባንያው በአገልግሎቱ ላይ አዳዲስ የቁጥጥር ስርዓቶችን ተግባራዊ ከማድረጉ ጎን ለጎን የተንቀሳቃሽ የእጅ ስልኮችንም ለመመዝገብ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል።
ማክሰኞ 12 ኤፕሪል 2016
የማህበራዊ ድምጽና ምስል አገልግሎቶች በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ተቋረጡ
መንግስት በኢንተርኔት አማካኝነት የሚደረጉ የድምፅና የምስል አገልግሎቶች ላይ አዲስ መመሪያን እንደሚተገብር ማስታወቁን ተከትሎ አገልግሎቱ በሃገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ተቋረጠ።
በተለይ በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተገናኘ ተቃውሞ በተቀሰቀሰበት የኦሮሚያ ክልል የትዊተርና የWhatsAPP አገልግሎቶች ከተቋረጡ አንድ ወር አካባቢ እንደሆናቸው ብሉምበርግ የዜና ወኪል የተለያዩ መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ማክሰኞ ዘግቧል።
በኦሮሚያ ክልል በተጨማሪ አገልግሎቶቹ በደቡብ ክልል ሃዋሳ ከተማና በተለያዩ አካባቢዎች ተቋርጦ እንደሚገኝም የተለያዩ አካላት ለዜና ወኪሉ ያስታወቁ ሲሆን፣ በምስራቅ ለንደን ዩኒቨርስቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት አቶ ስዩም ሃሜሶ ሃገር ቤት ከሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ጋር እንኳን መገናኘት እንዳልቻሉ ተናግረዋል።
የመንግስት ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ አገልግሎቱ ሊስተጓጎል የቻለው በቴክኒክ ችግር ሊሆን እንደሚችል ገልፀው፣ መንግስት የማገድ ፖሊሲ እንደሌለው ለዜና አውታሩ አስተባብለዋል።
ይሁንና የስልክ አገልግሎት ተጠቃውሚዎችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች መንግስት ተግባራዊ ሊያደርግ ያሰበው አዳዲስ መመሪያዎች በኢንተርኔት እና በስልክ የመልዕክት ልውውጦች ላይ ቁጥጥርን እንዲሁም የስነ-ልቦና ተፅዕኖን ለመፍጠር እንደሆነ አስታውቀዋል።
በአምቦ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት አቶ ስዩም ተሾመ በተቀንሳቃሽ የእጅ ስልክ የሚደረጉ የተለያዩ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ተቋርጠው እንደሚገኙ ለብሉምበርግ የዜና አውታር አስረድቷል።
በቅርቡ የWhatsAPP ኩባንያን የገዛው ፌስቡክና ትዊተር ድርጅቶች በኢትዮጵያ እገዳ ተጥሎበት ስላለው አገልግሎት ተጠይቀው ምላሽ ከመስጠት መቆጠባቸው በዘገባው ያወሳው የዜና ወኪሉ እገዳው በተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ዘንድ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኖ እንደሚገኝም አስነብቧል።
በኢትዮጵያ የሰብዓዊ የመብት አያያዝና የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት ዙሪያ የሰላ ትችትን የሚያቀርበው ሂውማን ራይትስ ዎች በበኩሉ ድርጊቱ ቀድሞ የተተነበየ እንደሆነና መንግስት የመረጃ ልውውጦች ላይ ቁጥጥሩን እንዳጠናከረ ገልጿል።
መቀመጫውን በሰርቢያ ያደረገውን በቴክኖሎጂ ዙሪያ የሚሰራው ኩባንያ በየጊዜው የሚያወጣቸው መረጃዎች በቢቢሲ እና በሌሎች አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘንድ በመረጃነት እንደሚቀርቡም ለመረዳት ተችሏል።
ቤርሙዳ ኢዝቤኪስታን እና ሚያንማር ከኢትዮጵያ በመቀጠል ከሁለተኛ እስከ አራተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ ከሚያደርገው ቁጥጥር በተጨማሪ የሚጠይቀው ክፍያም ውድ መሆኑን የተለያዩ አካላት ሲገልጹ መቆየታቸው ይታወሳል።
መንግስት በገጠመው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ፣ በውጭ ሃገር ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በህዳሴ ግድብ እንዲሁም በመኖሪያ ቤት ግንባታ ገንዘብ ለማሰባሰብ አዲስ ዘመቻ መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል
በተለይ በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተገናኘ ተቃውሞ በተቀሰቀሰበት የኦሮሚያ ክልል የትዊተርና የWhatsAPP አገልግሎቶች ከተቋረጡ አንድ ወር አካባቢ እንደሆናቸው ብሉምበርግ የዜና ወኪል የተለያዩ መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ማክሰኞ ዘግቧል።
በኦሮሚያ ክልል በተጨማሪ አገልግሎቶቹ በደቡብ ክልል ሃዋሳ ከተማና በተለያዩ አካባቢዎች ተቋርጦ እንደሚገኝም የተለያዩ አካላት ለዜና ወኪሉ ያስታወቁ ሲሆን፣ በምስራቅ ለንደን ዩኒቨርስቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑት አቶ ስዩም ሃሜሶ ሃገር ቤት ከሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ጋር እንኳን መገናኘት እንዳልቻሉ ተናግረዋል።
የመንግስት ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ አገልግሎቱ ሊስተጓጎል የቻለው በቴክኒክ ችግር ሊሆን እንደሚችል ገልፀው፣ መንግስት የማገድ ፖሊሲ እንደሌለው ለዜና አውታሩ አስተባብለዋል።
ይሁንና የስልክ አገልግሎት ተጠቃውሚዎችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች መንግስት ተግባራዊ ሊያደርግ ያሰበው አዳዲስ መመሪያዎች በኢንተርኔት እና በስልክ የመልዕክት ልውውጦች ላይ ቁጥጥርን እንዲሁም የስነ-ልቦና ተፅዕኖን ለመፍጠር እንደሆነ አስታውቀዋል።
በአምቦ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት አቶ ስዩም ተሾመ በተቀንሳቃሽ የእጅ ስልክ የሚደረጉ የተለያዩ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ተቋርጠው እንደሚገኙ ለብሉምበርግ የዜና አውታር አስረድቷል።
በቅርቡ የWhatsAPP ኩባንያን የገዛው ፌስቡክና ትዊተር ድርጅቶች በኢትዮጵያ እገዳ ተጥሎበት ስላለው አገልግሎት ተጠይቀው ምላሽ ከመስጠት መቆጠባቸው በዘገባው ያወሳው የዜና ወኪሉ እገዳው በተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ዘንድ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኖ እንደሚገኝም አስነብቧል።
በኢትዮጵያ የሰብዓዊ የመብት አያያዝና የመገናኛ ብዙሃን ነጻነት ዙሪያ የሰላ ትችትን የሚያቀርበው ሂውማን ራይትስ ዎች በበኩሉ ድርጊቱ ቀድሞ የተተነበየ እንደሆነና መንግስት የመረጃ ልውውጦች ላይ ቁጥጥሩን እንዳጠናከረ ገልጿል።
መቀመጫውን በሰርቢያ ያደረገውን በቴክኖሎጂ ዙሪያ የሚሰራው ኩባንያ በየጊዜው የሚያወጣቸው መረጃዎች በቢቢሲ እና በሌሎች አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘንድ በመረጃነት እንደሚቀርቡም ለመረዳት ተችሏል።
ቤርሙዳ ኢዝቤኪስታን እና ሚያንማር ከኢትዮጵያ በመቀጠል ከሁለተኛ እስከ አራተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል። የኢትዮጵያ መንግስት በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ ከሚያደርገው ቁጥጥር በተጨማሪ የሚጠይቀው ክፍያም ውድ መሆኑን የተለያዩ አካላት ሲገልጹ መቆየታቸው ይታወሳል።
መንግስት በገጠመው ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ፣ በውጭ ሃገር ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በህዳሴ ግድብ እንዲሁም በመኖሪያ ቤት ግንባታ ገንዘብ ለማሰባሰብ አዲስ ዘመቻ መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል
እሑድ 27 ማርች 2016
የሄነከን ቢራ ዘረፋ ምስጢር በኢትዮጵያ ሲጋለጥ – ክንፉ አሰፋ
የሄነከን ቢራ ዘረፋ ምስጢር በኢትዮጵያ ሲጋለጥ – ክንፉ አሰፋ
የሆላንድ ዜምብላ[1] ጋዜጠኞች የኦሮሞ ጸሃፊው የሆነውን ያሶ ካባባን ይዘው ወደ ጊንጪ ያመራሉ። እግረመንገድ ላይ የሚያገኟቸው ገበሬዎችም ሲጠይቋቸው በምስሉ ይታያል። እነዚያ በቀያቸው ማረፍያ እንኳን የሌላቸው ገበሬዎች የጋዜጠኞቹን መኪና ከብበው እንዲህ ሲሉ ይደመጣሉ። “መሬታችንን ቀምተው ለነጮች ሰጡብን። እኛንም በታተኑን…”
በገዛ ቀያቸው ስደተኛ የሆኑ እነዚህ ወገኖቻቸን ሰቆቃቸው የከፋ ነበር። በመጨረሻ ተሰባሰቡና መከሩ። ሰባት ሺህ የሚሆኑ የጊንጪ ተወላጆች ሆ! ብለው ወጥተው ይህንን የሁለት ሚሊዮን ዩሮ (ሃምሳ ሚልዮን ብር) ንብረት በሰኮንዶች ውስጥ አወደሙት። ምስላቸውን ለካሜራ ሳይደብቁ፣ ስሜታቸውን እና የወደፊት እቅዳቸውን ይናገራሉ። “ከአንባገነን መንግስት ጋር አብሮ ከመስራት ይልቅ የአካባቢው ነዋሪዎች ሊጠቀሙ በሚችሉበት መንገድ መስራት እንደሚችሉም።” ለፈረንጆቹ ይመክራሉ። “ይህ ካልሆነ ግን ማውደሙን እንቀጥልበታለን!” ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ይህ ማስጠንቀቅያ ግዙፉ አለም አቀፍ ኩባንያ የሆነው ሄነከን ቢራንም ይመለከታል።
ባለፈው ሳምንት በሆላንድ ብሄራዊ ቴለቭዥን የተላለፈው ዜምብላ ፕሮግራም የሚሊዮኖችን ቀልብ ስቧል። ለዚህም ምክንያቶች አሉት። አንደኛው ምክንያት፤ የዜምብላ ፕሮግራም በምርመራ ጋዜጠኞች የሚሰራ በመሆኑ እጅግ የሚፈራ እና በሃገሪቱ ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ማሳደሩ ሲሆን፣ በሁለተኛ ደረጃ በኢትዮጵያ እየወደመ ያለው ይህ ንብረት የተቋቋመው በሆላንድ መንግስት ድጎማ ሲሆን፣ ይህ ደግሞ የእያንዳንዱ ሆላንዳዊ ግብር ከፋይ ገንዘብ በመሆኑ ነው።
የሆላንድ የልማትና ትብብር ሚንስተር ለድሃ ሀገሮች እርዳታ ከመለገስ ይልቅ ወደ ንግድ ድጎማ ፊቱን ባዞረ ግዜ፣ 130 አትራፊ የንግድ ድርጅቶች ድጎማ እየተቀበሉ ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። ከነዚህ ውስጥ ትልቁን የድጎማ ድርሻ የወሰደው ሄነከን ቢራ ነው። ሄነከን ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ የሆላንድ መንግስት አንድ ቢሊየን ዩሮ ድጎማ አድርጓል። እንደ ሆላንድ መንግስት እሳቤ፣ ይህንን የልማት ትብብር ገንዘብ በእርዳታ መልክ ከመስጠት ይልቅ ይህንን አትራፊ ተቋም አበራትቶ ስራ በመፍጠር እና በንግድና በስራ ታክስ ሃገሪቱ ተጠቃሚ እንድትሆን ማድረግ ነበር። የሆነው ግን በተቃራኒ ነው።
የዜምብላ ቴሌቭዥን ዘገባ ያጋለጠው ጉዳይ በእጅጉ ያስደምማል። እንዲህ ነው የሆነው። እ.ኤ.አ. በ 2011 ሄነከን ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ የቢራ ስራ አዋጭ መሆኑን ስለተገነዘበ ስመ ጥሮቹን በደሌ እና ሃረር ቢራን ገዛቸው። ስራውንም በእጅጉ አስፋፋ። በአኢትዮጵያ የቢራ ተጠቃሚዎች ቁጥር በእጥፍ እንዳደገም ዘገባው አስምሮበታል። ትርፉም እንደዚያው አደገ።
በደሌ ቢራ ከመሸጡ በፊት አንድ ነጥብ አምስት ሚሊየን ዩሮ ግብር ይከፍል ነበር። ሄነከን ከገዛው በኋላ ግን የከፈለው ዘጠኝ መቶ ሺህ ዩሮ ብቻ ነው። አንድ ሚሊየን ዩሮ ግብር ይከፍል የነበረው ሃረር ቢራም አሁን ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ዩሮ ብቻ ነው ያስገባው። ትርፉ ከእጥፍ በላይ እያደገ፣ ግብሩ ከእጥፍ በላይ የመቀነሱ ምስጢር ምን ይሆን?
የግብር ማጭበርበር ጥቆማ የደረሳቸው እነዚህ ጋዜጠኞች ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ንግድ ሚንስትር ሄዱ። ምኒስትሩ በዚህ የማጣራት ጉዳይ ላይ ሊተባባራቸው ፈቃደኛ አልነበረም። ከዚያም ወደ ጉምሩክ እና ቀረጥ ቢሮ አመሩ። እዚያም ምንም መረጃ እንሰጥም ይሏቸዋል። ምስጢሩን ለማውጣት የጓጉት እነዚህ ጋዜጠኖች ተስፋ አልቆረጡም። በመጨረሻ ወደ ንግድ ምክር ቤት አመሩ። የዚያ ባለስልጣን የሰጧቸው ምላሽ የሚያስቅ ነው። “የንግድና ትርፍ ዘገባ አይደርሰንም።” አሉ። ታዲያ ንግድ ምክር ቤት ይህንን ካልመዘገበ ምን ይሆን የሚሰራው?
የንግድና የስራ ግብር መቀነሱ ብቻ አይደለም። ቀድሞ በሃረር እና በበደሌ ቢራ ቋሚ ሰራተኛ የነበሩ 699 (44%) ሰራተኞችም ከሄነከን ቢራ ተቀንሰዋል። የሆላንድ መንግስት ስራ ፍጠሩ ብሎ ድጎማ ሲያደርግ፣ ይልቁንም ነባሩን ሰራተኛ ከስራው አፈናቀሉት።
በኢትዮጵያ የሄነከን ተወካይ ሆላንዳዊ ነው። የዜምብላ ጋዜጠኖች የዚህን እንቆቅልሽ ለመፍታት እሱን ማፋጠጥ ይችላሉ። ስለዚህም ወደሱ አመሩ። የገቢና ወጪ ዘገባውን እንዲሰጣቸው ጠየቁት። እንቢ እንዳይል ቸገረው። ምክንያቱም በዚያ ዘገባ የሆላንድ መንግስት የድጎማ ገንዘብ ሰላለበት። እሺ ብሎ ይፋ እንዳያደርገው ደግሞ ምስጢሩ ለህዝብ ሊወጣ ነው። እሱም አለ። “የፋይናንስ ሪፖርቱን እሰጣችኋለሁ። እናንተ ግን ለህዝብ ይፋ እንደማታደርጉት ቃል ግቡልኝ።”
ዘገባውን በእጃቸው ያስገቡት እነዚህ ጋዜጠኖች፣ ዶክመንቱን አለም አቀፉ የገንዘብ ተቁዋም አማካሪዎች ጋ ይዘውት ሄዱ። የ አይ. ኤም. ኤፍ. ባለሙያው ወረቀቱን እንዳየ ምስጢሩን ለማወቅ ሰከንዶች አልፈጁበትም። የኢትዮጵያ ህዝብ በታክስ ተዘርፏል። ሰራተኛውም ወገን ከስራው እንዲፈናቀል ተደርጓል።
የመንግስት ባለስልጣን ሃገር ሲዘረፍ እና ወገን ከስራ ሲፈናቀል፣ ጉዳዩን ማፈን መርጠዋል። ምክንያት ቢኖራቸው እንጂ ይህን መረጃ መስጠት ሀገርን የሚጠቅም ነበር። በእርግጥ ይህ የግብር ማጭበርበር ተግባር እነሱ ሳያውቁት ሊሆን አይችልም። “የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ!” ነው ነገሩ። እንዲህ እየተዘረፈ ኢኮኖሚው እንዴት ነው በ 11 በመቶ የሚያድገው?
እንግዲህ ይህ በኢትዮጵያ ከዘመቱት 130 የሆላድ የንግድ ድርጅቶች አንዱ ታሪክ ነው። ገቢውና ወጭው በግልጽ የሚታይ፣ ግዙፍ እና አለም አቀፍ ድርጅት። ሄነከን ከገዥው ፓርቲ ባለስልጣናት ጋር በመመሳጠር ይህንን ያህል ከዘረፈ የሌሎቹ – የማይታወቁት ምን ያህ ይሆን?
የቀድሞው የሆላንድ ልማትና ትብብር ሚንስቴር የነበሩት ጃን ፕሮንክ፣ በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ከልማት እና እደገት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት ለሌላቸው የንግድ ድርጅቶች የገንዘብ ድጋፍ ማድረግን ክፉኛ ይወቅሳሉ። በተለይ መንግስታቸው በልማትና ትብብር ስም፣ በብሄራው ጥቅም ስም የስብአዊ መብት ረገጣን ችላ ማለቱን ያወግዛሉ።
በልማት ስም በሚሊዮኖች እየፈሰሰ ያለው የሆላንድ ግብር ከፋዮች ገንዘብ በኢትዮጵያ ስራ አልፈጠረም። እንደውም ሰራተኞችን አፈናቀለ። ሀገሪቱን በበለጠ የስራና የንግድ ግብር ተጠቃሚ ያደርጋል ይባል እንጂ ግብሩ በ 70 እጅ ያነሰ ሆኗል። ከሁሉም በላይ ደግሞ የገበሬው መሬት እየተነጠቀ ለነዚህ ዘራፊዎች መሰጠቱ የህዝብ ቁጣን አስነስቷል።
በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት እየተካሄደ ያለው ህዝባዊ አመጽ የገዥው ፓርቲ ችግር ብቻ ሳይሆን የሆላንድም ችግር መሆኑን በመግለጽ ዜምብላ ዘገባውን ይደመድማል።
ረቡዕ 16 ማርች 2016
Ethiopians hold demonstration in DC denouncing human rights violations in their country, demand US to take firm stand
Ethiopians living in the metropolitan Washington, DC area held a
demonstration at the US State Department on Tuesday denouncing the human
rights violations perpetrated by the tyrannical regime in their country
against the people of Surma in South Ethiopia as well as the human
rights abuses at various locations in the country.
The demonstrators also demanded the US government to show unwavering
stance against the human rights abuses perpetrated by its ally in
Ethiopia.
An international uproar ensued last week after a picture of Surma men
in a chain gang, loaded on a police pickup, surfaced on the social
media. They were apparently held by the regime’s forces for protesting
the seizure of their land by the government for sugar plantations.
The Ethiopians demanded the regime in their country to immediately
desist the wide range of human rights violations in Oromia, Wolkait in
Amahra and Gambella regions and other corners of the country. The
demonstrators hold the oppressive regime in Ethiopia responsible for the
death of hundreds of people in the Oromia region of Ethiopia in the
last four months protests.
The organizers of the demonstration have submitted to the US State
Department a paper detailing the various human rights violations in
Ethiopia.
Tuesday’s demonstration was organized by the Washington DC Joint Task Force, civic, political and religious organizations.
ሰኞ 14 ማርች 2016
በኮንሶ ግጭቱ አገረሸ ፤ ሰዎች ተገደሉ:: የካራት ከተማና አጎራባች ቀበሌዎች ትምህርት ቤቶች ተዘጉ::
– በኮንሶ ህዝብ የተነሳውን የአከላለል ጥያቄ ተከትሎ በሕወሓት አገዛዝ ታጣቂ ኃይሎችና በህዝቡ መካከል የተነሳው
ግጭት ላለፉት ሁለት ቀናት ጋብ ብሎ የነበረ ቢሆንም እንደገና አገርሽቶ ሦስት ሰዎች ሲሞቱ ሁለት ደግሞ ቆስለዋል፡፡
የካራት ከተማ አጎራባች ከሆኑት ቀበሌዎች አንዱ በሆነው ደበና ቀበሌ ወጣት ፋንታዬ ጊዮርጊስ፣ ወጣት ሞሎ ቱሌ እና
አንድ ስሙ ያልደረሰን 10ኛ ክፍል ያጠናቀቀ ሥራ አጥ ወጣት በሕወሓት አገዛዝ የጸጥታ ኃይሎች የተገደሉ ሲሆን
በተጨማሪም ሁለት ወጣቶች ቆስለዋል ፡፡ በዚህ ግጭት ሳቢያ የካራት ከተማና አጎራባች ቀበሌዎች እስካሁን ትምህርት
ቤቶች እንደተዘጉ ሲሆን ከተማዋና አካባቢው በመኪና ላይ በተጠመዱና የነፍስ ወከፍ መትረየስ ታጣቂዎች ተወሮ፣ ኮንሶ
ልዩ ወረዳ ከዳር እስከ ዳር በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ናቸው፡፡

የኮንሶ ህዝብ የጀመረውን የአከላለል ጥያቄ ጋር በተያያዘ በህዝቡ ላይ በደቡብ ልዩ ኃይልና መከላከያ ሰራዊት
እየደረሰ ያለው የአፈና ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በዚሁ መሰረት በከተማው የሰፈረው ታጣቂ ከከተማዋ አጎራባች
ቀበሌዎች እየዘመተ በህዝቡ የተዘጉ መንገዶችን ለማስከፈት በሚል በዜጎች ላይ በሚወስደው የኃይል እርምጃ በ- ደቤና
ቀበሌ ገ/ማ አቶ ‹‹ሷይታ ጋራ ›› ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ወጣት ‹‹ ተስፋዬ ማሙሽ›› ከ -ከርታሌ ቀበሌ እግሩ
ተሰብሮ በባህል ህክምና እየተደረገለት በካራት ከተማ የሚገኝ ሲሆን አንድ የ65 ዓመት አዛውንትም ተሰብረው ባሻ ጤና
ጣቢያ ይገኛሉ፡፡ ከባለፈው ዓርብ/25-06-08/ ጀምሮ 23 ሰዎች/ሃያ ሁለት ወንዶችና አንዲት ሴት/ ከፍተኛ
ድብደባ ተፈጽሞባቸው በከተማዋ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከል ውስጥ ታስረው እንደሚገኙ ተገልጧል፡፡ በከተማዋ
የሚገኙት የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች በሙሉ የተዘጉ ሲሆን የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛው ወደ እስር ቤት
ተቀይሯል፡፡
ወደከተማው የሚያስገቡ መንገዶች እስካሁን የተዘጉ ሲሆን በተለይ የ -ደራ እና ጃርሶ ቀበሌ ነዋሪዎች መትረየስ በታጠቁ የልዩ ኃይል አባላት ተወረዋል፡፡ በጃርሶ ቀበሌ ሰገን ወንዝ ዳር የሰፈረው ኃይል የነዋሪዎችን ፍዬሎች እየዘረፈ አርዶ እንደሚበላ፣ የፓፓያ፣ማንጎ አቮካዶ እና የፍራፍሬ ዛፎችን በበቀል ስሜት እያበላሸ/እያወደመ እንደሚገኝም ህዝቡ በምሬት እየገለጸ ነው፡፡
ታጣቂ ኅይሉ በዚህ የኃይል እርምጃ የካራትን ከተማ አቋርጦ የሚያልፈውን የአርባ ምንጭ -ጂንካ መንገድ ማስከፈት ቢችልም ከተማዋን ከማሳለፍ ውጪ የሚሰጠው ዋስትና ያለመኖሩ አሽከሪካሪዎችን ስጋት ላይ በመጣሉ ከመንግስት መኪናዎች ውጪ የትራንስፓርት እንቅስቃሴ አይታይም፡፡ የመንግስት መኪና ተጠቃሚዎችም ቢሆኑ ከልዩ ኃይል ጋር ተነጋግረው መግባባት ባለመቻላቸው በትናንትናው ዕለት የደቡብ ኦሞ/ጂንካ ባለሥልጣናትን ይዞ ይጓዝ የነበረ መኪና ለ2 ሰዓታት ካራት ላይ በታጣቂ ኃይሎች ታግቶ ቆይቶ እንደተለቀቀ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
በአጠቃላይ ከተማዋና አካባቢው በመኪና ላይ በተጠመዱና የነፍስ ወከፍ መትረየስ ታጣቂዎች ተወሮ፣ ኮንሶ ልዩ
ወረዳ ከዳር እስከ ዳር በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ይገኛል ፡፡ የአገር ሽማግሌዎችና ወጣቶች ፣ሴቶችና ህጻናት ሳይቀሩ
ቱንም ዋጋ እንከፍላለን እንጂ ጥያቄኣችን ሳይመለስ ወደቤት አንገባም /አንመለስም በማለት ያላቸውን ቁርጠኝነት
እየገለጹ መሆኑን እነዚሁ ታማኝ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡ እኛም የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት ሆይ ‹‹አፈና እና
የኃይል እርምጃ ›› የህዝብን ብሶት ሲባብስ እንጂ ለህዝብ ጥያቄ መልስ አይሆንምና ከህዝቡ ላይ እጅህን አንሳ፣
ለሰላማዊ ጥያቄው ተገቢውን ምላሽ ስጠው፣ ህገ መንግስታዊ መብቱን አክብርለት እንላለን ፡፡
ወደከተማው የሚያስገቡ መንገዶች እስካሁን የተዘጉ ሲሆን በተለይ የ -ደራ እና ጃርሶ ቀበሌ ነዋሪዎች መትረየስ በታጠቁ የልዩ ኃይል አባላት ተወረዋል፡፡ በጃርሶ ቀበሌ ሰገን ወንዝ ዳር የሰፈረው ኃይል የነዋሪዎችን ፍዬሎች እየዘረፈ አርዶ እንደሚበላ፣ የፓፓያ፣ማንጎ አቮካዶ እና የፍራፍሬ ዛፎችን በበቀል ስሜት እያበላሸ/እያወደመ እንደሚገኝም ህዝቡ በምሬት እየገለጸ ነው፡፡
ታጣቂ ኅይሉ በዚህ የኃይል እርምጃ የካራትን ከተማ አቋርጦ የሚያልፈውን የአርባ ምንጭ -ጂንካ መንገድ ማስከፈት ቢችልም ከተማዋን ከማሳለፍ ውጪ የሚሰጠው ዋስትና ያለመኖሩ አሽከሪካሪዎችን ስጋት ላይ በመጣሉ ከመንግስት መኪናዎች ውጪ የትራንስፓርት እንቅስቃሴ አይታይም፡፡ የመንግስት መኪና ተጠቃሚዎችም ቢሆኑ ከልዩ ኃይል ጋር ተነጋግረው መግባባት ባለመቻላቸው በትናንትናው ዕለት የደቡብ ኦሞ/ጂንካ ባለሥልጣናትን ይዞ ይጓዝ የነበረ መኪና ለ2 ሰዓታት ካራት ላይ በታጣቂ ኃይሎች ታግቶ ቆይቶ እንደተለቀቀ ምንጮች ገልጸዋል፡፡

እሑድ 13 ማርች 2016
Egregious Human Rights Violations In the OMO Valley of Ethiopia
If you think the image you see below is from the archives of the slave trade in the 1800s you are wrong. This is 2016 #Ethiopia where the government chains and forcefully removes indigenous peoples from their ancestral homeland for sugar cane plantation.
The minority government thinks it is. In the name of development, dehumanization and the degradation of human dignity are the order of the day throughout Ethiopia. These gross violations of human rights are taking place with the blessing of the West especially, the US and UK - the unconditional financial, political, diplomatic, and military aid for the TPLF for the past 25 years has enabled the regime to terrorize Ethiopian citizens with impunity.
ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
በአገራችን እየተነሱ ያሉ ግጭቶች መኢአድን በእጅጉ አሳስቦታል!
ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
I. የኢህአዴግ መንግሥት በ1983 ዓ.ም ሥልጣን ከመያዙ በፊት የኢትዮጵያ ሕዝብ በተወለደበት ቀዬ፣ በዘሩና በቋንቋው ሳይሆን በኢትዮጵያዊ ማንነቱ በመኩራት በአንድነትና በመተባበር የአገሩን ዳር ድንበር ሲያስከብርና አገሩን ሲገነባ ኖሯል፡፡ በ1983 ዓ.ም የተቋቋመው የሽግግር መንግሥት በተደነገገው በሕገመንግሥት አንቀጽ 39 ላይ ባወጣው የራስን እድል በራስ መወሰን እንከመገንጠል መብት በመገፉፉት የኢትዮጵያ ሕዝብ ከኢትዮጵያዊነቱ ይልቅ ለተወለደባት ቀበሌና ለወጣበት ዘር፣ ከአንድነት ይልቅ መለያየት፣ አብሮ በመሥራትና አብሮ በማደግ ከመበልጸግ ይልቅ ተበታትኖ የጐሪጥ ስለሚተያይ በአገራችን ዕድገት ላይ መሰናከል በመፈጠሩ በችግር ላይ ይገኛል፡፡
ይህ የመለያየትና የመከፋፈል በሽታ ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥ እያደገ መጥቶ ዛሬ ልንወጣው በማንችልበት የገደል አፋፍ ላይ ጥሎናል፡፡
በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል ሕዝብ የቀረበው ጥያቄ በወጉና በባህሉ መሠረት ሊመለስ ባለመቻሉ ጥያቄው ወደ ሕዝባዊ አመፅ ተቀይሮ በሰውና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ ይገኛል፡፡ ይህ ጥያቄውን በሰላማዊ መንገድ መመለስ አለመቻልና በድብደባ፣ በእስራትና በግድያ ለማብረድ መሞከሩ አመፁን ከማባባሱና ጉዳቱን ከማስፋት ውጭ የሚፈይደው አንዳችም ነገር የለም፡፡
ከዚህ ቀደም ከአለን ተሞክሮ እንደምንረዳው እንደነዚህ ያሉ ቅራኔዎች በሚከሰቱበት ወቅት እየተናቁና ትኩረት እያጡ በመቆየታቸው በአገራችንና በሕዝባችን ላይ ከፍተኛ ቀውስና ውድቀት ሲያስከትሉ ቆይተዋል፡፡
ከኢህአዴግ መንግሥት ባለሰልጣናት የሚነገረው የቅራኔው መነሻ የመልካም አስተዳደር እጦት ነው የሚል ነው፡፡ ይህ አባባል መልካም ሰው ከአገር አጥፍቶ መልካም አስተዳደርን አመጣለሁ ማለቱ ስህተት ቢሆንም ቅሉ በአገሪቱ ውስጥ እየተነሱ ያሉ ቅራኔዎች ከመልካም አስተዳደር እጦት የዘለሉና ብዙ ድርብርብ ጥያቄዎችን ያዘሉ ለመሆኑ መንግሥት ሊጠራጠር አይገባውም፡፡ ምክንያቱም በሀገራችን ያለው የኑሮ ውድነት፣ ሙስና፣ ፍትሀዊ ያልሆነ የኢኮኖሚ ክፍፍልና የመለካም አስተዳደር እጦት በአገሪቱ ተንሰራፍተዋልና ነው፡፡
I. የኢህአዴግ መንግሥት በ1983 ዓ.ም ሥልጣን ከመያዙ በፊት የኢትዮጵያ ሕዝብ በተወለደበት ቀዬ፣ በዘሩና በቋንቋው ሳይሆን በኢትዮጵያዊ ማንነቱ በመኩራት በአንድነትና በመተባበር የአገሩን ዳር ድንበር ሲያስከብርና አገሩን ሲገነባ ኖሯል፡፡ በ1983 ዓ.ም የተቋቋመው የሽግግር መንግሥት በተደነገገው በሕገመንግሥት አንቀጽ 39 ላይ ባወጣው የራስን እድል በራስ መወሰን እንከመገንጠል መብት በመገፉፉት የኢትዮጵያ ሕዝብ ከኢትዮጵያዊነቱ ይልቅ ለተወለደባት ቀበሌና ለወጣበት ዘር፣ ከአንድነት ይልቅ መለያየት፣ አብሮ በመሥራትና አብሮ በማደግ ከመበልጸግ ይልቅ ተበታትኖ የጐሪጥ ስለሚተያይ በአገራችን ዕድገት ላይ መሰናከል በመፈጠሩ በችግር ላይ ይገኛል፡፡
ይህ የመለያየትና የመከፋፈል በሽታ ባለፉት 24 ዓመታት ውስጥ እያደገ መጥቶ ዛሬ ልንወጣው በማንችልበት የገደል አፋፍ ላይ ጥሎናል፡፡
በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል ሕዝብ የቀረበው ጥያቄ በወጉና በባህሉ መሠረት ሊመለስ ባለመቻሉ ጥያቄው ወደ ሕዝባዊ አመፅ ተቀይሮ በሰውና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ ይገኛል፡፡ ይህ ጥያቄውን በሰላማዊ መንገድ መመለስ አለመቻልና በድብደባ፣ በእስራትና በግድያ ለማብረድ መሞከሩ አመፁን ከማባባሱና ጉዳቱን ከማስፋት ውጭ የሚፈይደው አንዳችም ነገር የለም፡፡
ከዚህ ቀደም ከአለን ተሞክሮ እንደምንረዳው እንደነዚህ ያሉ ቅራኔዎች በሚከሰቱበት ወቅት እየተናቁና ትኩረት እያጡ በመቆየታቸው በአገራችንና በሕዝባችን ላይ ከፍተኛ ቀውስና ውድቀት ሲያስከትሉ ቆይተዋል፡፡
ከኢህአዴግ መንግሥት ባለሰልጣናት የሚነገረው የቅራኔው መነሻ የመልካም አስተዳደር እጦት ነው የሚል ነው፡፡ ይህ አባባል መልካም ሰው ከአገር አጥፍቶ መልካም አስተዳደርን አመጣለሁ ማለቱ ስህተት ቢሆንም ቅሉ በአገሪቱ ውስጥ እየተነሱ ያሉ ቅራኔዎች ከመልካም አስተዳደር እጦት የዘለሉና ብዙ ድርብርብ ጥያቄዎችን ያዘሉ ለመሆኑ መንግሥት ሊጠራጠር አይገባውም፡፡ ምክንያቱም በሀገራችን ያለው የኑሮ ውድነት፣ ሙስና፣ ፍትሀዊ ያልሆነ የኢኮኖሚ ክፍፍልና የመለካም አስተዳደር እጦት በአገሪቱ ተንሰራፍተዋልና ነው፡፡
ስለዚህ፡-
1. በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ሰላማዊ በሆነ ውይይትና መግባባት እንዲፈታ አጥብቀን እንጠይቃለን፤
2. እስራት፣ ድብደባውና ግድያው ቅራኔውን ከማባባሱ ውጭ የሚያመጣው ፋይዳ ስለማይኖር በአስቸኳይ ቆሞ ለጉዳዩ ሰላማዊ መፍትሔ እንዲፈለግለት
1. በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ሰላማዊ በሆነ ውይይትና መግባባት እንዲፈታ አጥብቀን እንጠይቃለን፤
2. እስራት፣ ድብደባውና ግድያው ቅራኔውን ከማባባሱ ውጭ የሚያመጣው ፋይዳ ስለማይኖር በአስቸኳይ ቆሞ ለጉዳዩ ሰላማዊ መፍትሔ እንዲፈለግለት
II. በአንዳንድ አላዋቂ እና ፅንፈኛ የፖለቲካ ሰዎች የተደረጉ ውሳኔዎች በፍቅርና በአንድነት ለብዙ ሺ ዓመታት አብሮ የኖረውን ወንድማማች ሕዝብ ወደማይመለስ ቅራኔ እየከተቱት ይገኛሉ፡፡ ይኸም በወልቃይት ጠገዴ፣ በፀለምትና በሴቲት ሁመራ አካባቢ የሚገኘው መሬት በአማራ ክልል ወይስ በትግራይ ስር ነው? በሚል የተነሳው ጥያቄ ሁለቱን ወንድማማች ሕዝቦች ወደከፋ ግጭት ውስጥ ለማስገባት ከጫፍ ላይ ደርሶ ይገኛል፡፡ እንደነዚህ ያሉ ግጭቶች በአሁኗ ኢትዮጵያ አዲስ አይደሉም፡፡ ለምሳሌ፡- በቦረናና በጉጂ፣ በሀሪና በኮንሶ፣ በደቡብና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል እንዲሁም በኦሮሚያ በደቡብ ክልሎች መካከል በመሬት ይገባኛል ስበብ ተመሳሳይ ቅራኔዎች ተነስተው ህይወት ጠፍቷል፣ ንብረትም ወድሟል፡፡ ይሁን እንጂ ሁኔታው በሁለቱ ክልሎች ባለስልጣናት ሰፊ ውይይት እንዲፈታ ተደርጓል፡፡ በወልቃይትና በሁመራ ምክንያት የተነሳው ቅራኔ ግን በሰላማዊ መንገድ ከመፍታት ይልቅ በቅራኔ ብቻ በመጦዝ ላይ በመገኘቱ መኢአድን እጅግ አድርጐ አሳስቦታል፡፡ ይሀ ሁኔታ ማንንም የማይጠቅም ስለሆነ ጊዜ ሳይሰጠው በውይይትና በሰላማዊ መንገድ መፈታት አለበት የሚል እምነት አለን፡፡
ከዚህ ላይ የህውሓትና የትግራይ ክልል አመራሮች በጉዳዩ ላይ የተለያዩ ፍንጮችን ሲሰጡ የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) በኩል አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ መልስ ሲሰጥ ተሰምቶ አያውቁም፡፡ ይኸም እወክለዋለሁና እመራዋለሁ ለሚለው ሕዝብ ትክክለኛውን አቅጣጫ ሊያመላክተው አለመቻሉ ከትዝብት ላይ የሚጥለው ሆኖ አግኝተነዋል፡፡
ስለዚህ መኢአድ ለሁለቱም ክልል አመራሮችና የፖለቲካ ድርጅቶች የሚያሳስበው፤
1ኛ. በሁለቱ ወንድማማች መካከል የከፋ ቅራኔ ሳይፈጠር የሚመለከታችሁ አካላት ሕግንና ከዚህ ቀደም የነበረን የአመጣጥ እና የአሰፋፈር ታሪክን መሠረት በማድረግ በአስቸኳይ መፍትሄ እንዲያፈላልጉለት፡፡
2ኛ. የፌዴራሉ መንግሥትም ቅራኔውና ብጥብጡ እንስከሚነሳ ዝም ብሎ ከመመልከት ይልቅ በእነዚህ ሁለት ወንድማማች ህዝቦች አመጣጥና አሰፋፈር ታሪክ ላይ በመመርኮዝ የመፈትሄ ሀሳብ መሰጠት ይቻል ዘንድ እንዲያመቻች አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
3ኛ. ከዚህ በተጨማሪ በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሁኔታው በህግ በሞራልና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ጥረት እንዲያደርጉ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
III. የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ለኢትዮጵያ የተቀዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር ፈር ቀዳጅ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ መኢአድ ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ ከውስጥና ከውጭ በሚነሱ ችግሮች የተነሳ መጠነ ሰፊ የሆነ ፈተና ሲጋረጥበት መቆየቱ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ መሪውን ክቡር ኘሮፌሰር አሥራት ወልደየስን ጨምሮ ብዙ አመራሮቹና አባላቱ በውስጥ አርበኞች ጠቋሚነትና መስካሪነት ታስረዋል፣ አካላቸው ጐድሏል፣ ተገድለዋልም፡፡ መኢአድን ለማፍረስ ብዙ ቡድኖች በተለያዩ አካላትና በተለያዩ ጊዜያት ተቋቁመዋል፡፡ ነገር ግን መኢአድን ለማዳከም የቻሉ ቢመስልም ሊያጠፉት ግን አልቻሉም፡፡ አሁንም በቅርብ ጊዜ በቀድሞው የመኢአድ ኘሬዝዳንት የግል ሹፌርና በሌሎች ምንደኛ ግለሰቦች የሚመራው ቡድን በተለያዩ ጥቅማጥቅሞች በመደለል ፓርቲውን ለማዳከም ብዙ ጥረት አድርጓል፡፡ እነዚህ ግለሰቦች የአራዳ ምድብ ችሎትን በሀሰት ቃለ-መሐላ በማሳሳት የፓርቲውን ማህተም አሳግደው ኘሬዝዳንቱን አግደናል በሚል ለአንድ ሳምንት ብዙ አካላትን አሳስተው ሲያወናብዱ ቆይተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ፍ/ቤቱ በአደረገው ማጣራት ሕገወጦች ናቸሁ በማለት ፋይሉን ዘግቶ አባሯቸዋል፡፡ ከዚህ በላይ በጣም ያሳዘነንና ያስቆጨን ኘሮፌሰር አሥራት በተቀመጡበት ወነበር ላይ የቀድሞ የመኢአድ ኘሬዝዳንት የግል ሹፌር የሆኑት በኘሬዝዳንትነት ተሰየምኩ በማለት ኃላፊነቱን ለመውረስ መምጣታቸው ነው፡፡
ከዚህ ላይ በጣም ያሳዘነንና ተስፋችንን ያሟጠጠው አንዳንድ በሕዝብ ዘንድ ተነባቢነት ያላቸው ጋዜጦችና የሬዲዮ ባቢያዎች እነዚህ ህገወጥ ግለሰቦች የሰጧቸውን ወረቀት በመያዝ ሁኔታውን ሳያጣሩ ሚዛናዊነቱን ያጣ ዘገባ ማድረጋቸው ነው፡፡ እንደዚህ ያለው ድርጊትም በአገራችን ዲሞክራሲን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ስለሚኖረው ጥንቃቄ ሊደረግበት ይገባል እንላለን፡፡
በአጠቃላይ እነዚህ ግለሰቦች በአሰራጩት የሀሰት ኘሮፓጋንዳ የተነሳ፤
1. በአገር ውሰጥ የምትገኙ የመኢአድ አባላት እና ደጋፊዎች እንዚህ ህጋዊ ያልሆኑ ግለሰቦች ባሰራጩት ውዥንብር ሳትደናገጡ በፅናትና በአንድነት ከፓርቲያችሁ ጋር እንድትቆሙ፤
2. በውጭ የምትገኙ የመኢአድ አባላትና ደጋፊዎች እንደነዚህ ያሉ ግለሰቦች እየሰሩት ያለው የውሸት ውዥንብር በመፍጠር ፓርቲውን ለማዳከም ስለሆነ በውዥንብሩ ሳታዝኑና ሳትጨነቁ የተለመደ አብሮነታችሁ ከፓርቲያችን እንዳይለይ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
3. እንደነዚህ ያሉ ጥቅመኞች ከተለያዩ አካላት ገንዘብ በመቀበል ፓርቲዎችን ለማፍረስ ጥረት ማድረጋቸው የተለመደ ሆኗል፡፡ ስለዚህ የየፓርቲዎቹ አባላትና ደጋፊ እንደነዚህ ያሉ ግለሰቦችን በአንድነት ሊያወግዟቸውና ሀይ ሊላቸው ይገባል፡፡
አንዲት ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
አዲስ አበባ
የካቲት 28 ቀን 2008 ዓ.ም
ከዚህ ላይ የህውሓትና የትግራይ ክልል አመራሮች በጉዳዩ ላይ የተለያዩ ፍንጮችን ሲሰጡ የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ብአዴን) በኩል አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ መልስ ሲሰጥ ተሰምቶ አያውቁም፡፡ ይኸም እወክለዋለሁና እመራዋለሁ ለሚለው ሕዝብ ትክክለኛውን አቅጣጫ ሊያመላክተው አለመቻሉ ከትዝብት ላይ የሚጥለው ሆኖ አግኝተነዋል፡፡
ስለዚህ መኢአድ ለሁለቱም ክልል አመራሮችና የፖለቲካ ድርጅቶች የሚያሳስበው፤
1ኛ. በሁለቱ ወንድማማች መካከል የከፋ ቅራኔ ሳይፈጠር የሚመለከታችሁ አካላት ሕግንና ከዚህ ቀደም የነበረን የአመጣጥ እና የአሰፋፈር ታሪክን መሠረት በማድረግ በአስቸኳይ መፍትሄ እንዲያፈላልጉለት፡፡
2ኛ. የፌዴራሉ መንግሥትም ቅራኔውና ብጥብጡ እንስከሚነሳ ዝም ብሎ ከመመልከት ይልቅ በእነዚህ ሁለት ወንድማማች ህዝቦች አመጣጥና አሰፋፈር ታሪክ ላይ በመመርኮዝ የመፈትሄ ሀሳብ መሰጠት ይቻል ዘንድ እንዲያመቻች አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
3ኛ. ከዚህ በተጨማሪ በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሁኔታው በህግ በሞራልና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ጥረት እንዲያደርጉ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
III. የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ለኢትዮጵያ የተቀዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር ፈር ቀዳጅ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ መኢአድ ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ ከውስጥና ከውጭ በሚነሱ ችግሮች የተነሳ መጠነ ሰፊ የሆነ ፈተና ሲጋረጥበት መቆየቱ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ መሪውን ክቡር ኘሮፌሰር አሥራት ወልደየስን ጨምሮ ብዙ አመራሮቹና አባላቱ በውስጥ አርበኞች ጠቋሚነትና መስካሪነት ታስረዋል፣ አካላቸው ጐድሏል፣ ተገድለዋልም፡፡ መኢአድን ለማፍረስ ብዙ ቡድኖች በተለያዩ አካላትና በተለያዩ ጊዜያት ተቋቁመዋል፡፡ ነገር ግን መኢአድን ለማዳከም የቻሉ ቢመስልም ሊያጠፉት ግን አልቻሉም፡፡ አሁንም በቅርብ ጊዜ በቀድሞው የመኢአድ ኘሬዝዳንት የግል ሹፌርና በሌሎች ምንደኛ ግለሰቦች የሚመራው ቡድን በተለያዩ ጥቅማጥቅሞች በመደለል ፓርቲውን ለማዳከም ብዙ ጥረት አድርጓል፡፡ እነዚህ ግለሰቦች የአራዳ ምድብ ችሎትን በሀሰት ቃለ-መሐላ በማሳሳት የፓርቲውን ማህተም አሳግደው ኘሬዝዳንቱን አግደናል በሚል ለአንድ ሳምንት ብዙ አካላትን አሳስተው ሲያወናብዱ ቆይተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ፍ/ቤቱ በአደረገው ማጣራት ሕገወጦች ናቸሁ በማለት ፋይሉን ዘግቶ አባሯቸዋል፡፡ ከዚህ በላይ በጣም ያሳዘነንና ያስቆጨን ኘሮፌሰር አሥራት በተቀመጡበት ወነበር ላይ የቀድሞ የመኢአድ ኘሬዝዳንት የግል ሹፌር የሆኑት በኘሬዝዳንትነት ተሰየምኩ በማለት ኃላፊነቱን ለመውረስ መምጣታቸው ነው፡፡
ከዚህ ላይ በጣም ያሳዘነንና ተስፋችንን ያሟጠጠው አንዳንድ በሕዝብ ዘንድ ተነባቢነት ያላቸው ጋዜጦችና የሬዲዮ ባቢያዎች እነዚህ ህገወጥ ግለሰቦች የሰጧቸውን ወረቀት በመያዝ ሁኔታውን ሳያጣሩ ሚዛናዊነቱን ያጣ ዘገባ ማድረጋቸው ነው፡፡ እንደዚህ ያለው ድርጊትም በአገራችን ዲሞክራሲን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ስለሚኖረው ጥንቃቄ ሊደረግበት ይገባል እንላለን፡፡
በአጠቃላይ እነዚህ ግለሰቦች በአሰራጩት የሀሰት ኘሮፓጋንዳ የተነሳ፤
1. በአገር ውሰጥ የምትገኙ የመኢአድ አባላት እና ደጋፊዎች እንዚህ ህጋዊ ያልሆኑ ግለሰቦች ባሰራጩት ውዥንብር ሳትደናገጡ በፅናትና በአንድነት ከፓርቲያችሁ ጋር እንድትቆሙ፤
2. በውጭ የምትገኙ የመኢአድ አባላትና ደጋፊዎች እንደነዚህ ያሉ ግለሰቦች እየሰሩት ያለው የውሸት ውዥንብር በመፍጠር ፓርቲውን ለማዳከም ስለሆነ በውዥንብሩ ሳታዝኑና ሳትጨነቁ የተለመደ አብሮነታችሁ ከፓርቲያችን እንዳይለይ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
3. እንደነዚህ ያሉ ጥቅመኞች ከተለያዩ አካላት ገንዘብ በመቀበል ፓርቲዎችን ለማፍረስ ጥረት ማድረጋቸው የተለመደ ሆኗል፡፡ ስለዚህ የየፓርቲዎቹ አባላትና ደጋፊ እንደነዚህ ያሉ ግለሰቦችን በአንድነት ሊያወግዟቸውና ሀይ ሊላቸው ይገባል፡፡
አንዲት ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
አዲስ አበባ
የካቲት 28 ቀን 2008 ዓ.ም
ረቡዕ 9 ማርች 2016
ፍርድ ቤት የመኢአድ ፕሬዚዳንት የፓርቲውን ማኅተም እንዳይጠቀሙ አሳልፎት የነበረው ዕግድ ተነሳ
ፍርድ ቤት የመኢአድ ፕሬዚዳንት የፓርቲውን ማኅተም እንዳይጠቀሙ አሳልፎት የነበረው ዕግድ ተነሳ
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ሦስተኛ ፍትሐ ብሔር ችሎት፣ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ የፓርቲውን ማኅተም እንዳይጠቀሙ አሳልፎት የነበረውን የዕግድ ውሳኔ የካቲት 22 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰጠው ውሳኔ አነሳ፡፡
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንቱ ማኅተሙን እንዳይጠቀሙ ጥር 25 ቀን 2008 ዓ.ም. የዕግድ ውሳኔ አሳልፎ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ እዚህ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ ያደረገው የፓርቲው ላዕላይ ምክር ቤት አባላት በፕሬዚዳንቱ ላይ ያቀረቡት ክስ ነበር፡፡
ፓርቲው ዕገዳው እንደተነሳለት ያሳወቀው ሰኞ የካቲት 28 ቀን 2008 ዓ.ም. ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ዋና ጽሕፈት ቤት በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ነው፡፡ ፓርቲውን የማዳከም ሥራ ከውስጥም ከውጭም ተጠናክሮ እንደቀጠለበት የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባው በመግለጫው ወቅት ገልጸዋል፡፡
‹‹መኢአድ ለኢትዮጵያ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር ፈር ቀዳጅ ነው፡፡ ፓርቲው ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ ከውስጥና ከውጭ በሚነሱ ችግሮች የተነሳ መጠነ ሰፊ የሆነ ፈተና ሲጋረጥበት ቆይቷል፡፡ አሁንም በቅርቡ የግል ጥቅማቸውን ባስቀደሙ ግለሰቦች የሚመራ ቡድን በተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች በመደለል ፓርቲውን ለማዳከም ብዙ ጥረት አድርጓል፤›› በማለትም የቀረበባቸው ክስ ፓርቲውን ለማዳከም በተነሱ ኃይሎች እንደተቀነባበረ አመልክተዋል፡፡
የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት ጥር 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ፕሬዚዳንቱ አቶ አበባው መሐሪ ቀጣዩ ጠቅላላ ጉባዔ እስከሚካሄድ ድረስ ማገዱንና ቀዳሚው ምክትል ፕሬዚዳንቱ አቶ አንድርያስ ኤሮ ፓርቲውን እንዲመሩ መወሰኑን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡
ሆኖም የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባውና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ሙሉጌታ አበበ ይህን ውሳኔ ክፉኛ የተቹትና የተቃወሙት ሲሆን፣ ይህን ውሳኔ ያስተላለፉት ግለሰቦች በተለያዩ ምክንያቶች ከፓርቲው የተባረሩና ራሳቸውን ከፓርቲው ያገለሉ ግለሰቦች እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡
‹‹ፕሬዚዳንቱን አግደናል የሚል ውሳኔ ያሳለፉት ግለሰቦች 16 ብቻ ናቸው፡፡ ከእነዚህ 16 ግለሰቦች መካከል ደግሞ ከፓርቲው ጋር ያልተቋረጠ ግንኙነት የነበራቸው አራቱ ብቻ ናቸው፡፡ ስለዚህ ውሳኔው የፓርቲውን መተዳደርያ ደንብም ሆነ የአብዛኛውን አባላት ይሁንታ ያገኘ አይደለም፤›› በማለት አቶ ሙሉጌታ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
‹‹የመኢአድ የምክር ቤት መቀመጫ ብዛት 105 ነው፡፡ እንዴት ነው 16 ግለሰቦች ፕሬዚዳንቱን ማውረድ የሚችሉት?›› በማለት ውሳኔው የአካሄድ ችግር እንደነበረበት ጠቁመዋል፡፡ ‹‹እንኳን 16 ግለሰቦች 105ቱም የምክር ቤቱ አባላት ቢገኙና ቢስማሙም ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንቱን የማውረድ ሥልጣን የለውም፡፡ በፓርቲው ደንብ መሠረት ፕሬዚዳንቱን የሚያስቀምጠውም ሆነ የሚያነሳው ጠቅላላ ጉባዔው ነው፤›› ሲሉም አብራርተዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱን ያገደው ቡድን በምክንያትነት ከሚያስቀምጣቸው ነጥቦች መካከል አንዱ ፕሬዚዳንቱ ጠቅላላ ጉባዔ ለማድረግ ፈቃደኛ አይደሉም የሚል ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር ፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔውን መቼ ያካሂዳል በማለት ሪፖርተር ላቀረበው ጥያቄ አቶ አበባው ሲመልሱ፤ ‹‹ምንም እንኳን ቀኑን ባንወስንም በመጋቢት ወር ውስጥ ለማድረግ ዝግጅት አጠናቅቀናል፤›› ብለዋል፡፡
ፓርቲው ከዚህ በተጨማሪም በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ አለመረጋጋቶች በሰላማዊና በድርድር እንዲፈቱ ጥሪ አስተላልፏል፡፡ አቶ አበባው ‹‹የከፋ ቅራኔ ሳይፈጠር የሚመለከታቸው አካላት ሕግንና ከዚህ ቀደም የነበረን የአመጣጥና የአሰፋፈር ታሪክን መሠረት በማድረግ በአስቸኳይ መፍትሔ ይፈለጉለት፤›› ብለዋል፡፡
በሽግግሩ መንግሥት የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) በሚል በታዋቂው የሕክምና ባለሙያ በፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የተመሠረተው ፓርቲ በ1994 ዓ.ም. ለሁለት ሲሰነጠቅ፣ አንዱ ቡድን መኢአድ በሚባል ኅብረ ብሔራዊ ቅርፅ ወዳለው ፓርቲነት ከተለወጠ በኋላ በኢንጂነር ኃይሉ ሻውል እየተመራ በ1997 ዓ.ም. ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲ የነበረው ቅንጅት ቁልፍ አባል እንደነበር ይታወሳል፡፡
መኢአድ በሌሎች የቅንጅት የቀድሞ አባላት ከተመሠረተው አንድነት ፓርቲ ጋር ባለፈው ዓመት በተካሄደው ምርጫ ተፅዕኖ ሊኖራቸው ይችላል ተብለው የተገመቱና በአንድ ወቅትም ወደ ውህደት ሊያመሩ ነው ተብሎ የተነገረ ቢሆንም፣ የምርጫ ቦርድ በውስጥ ክፍፍል ጉዳይ ላይ የሰጠው ውሳኔ እጅግ በተዳከመ ሁኔታ ለምርጫው እንዲቀርቡ አድርጓል ተብሎ ይተቻል፡፡
ከምርጫ ቦርድ ውሳኔ በኋላ ይህን መሰል ውዝግቦች ከሁለቱም ፓርቲዎች መስማት የተለመደ ሲሆን፣ ፓርቲዎቹ ይህ ነው የሚባል እንቅስቃሴ ሲያደርጉም አይስተዋልም፡፡
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንቱ ማኅተሙን እንዳይጠቀሙ ጥር 25 ቀን 2008 ዓ.ም. የዕግድ ውሳኔ አሳልፎ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ እዚህ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ ያደረገው የፓርቲው ላዕላይ ምክር ቤት አባላት በፕሬዚዳንቱ ላይ ያቀረቡት ክስ ነበር፡፡
ፓርቲው ዕገዳው እንደተነሳለት ያሳወቀው ሰኞ የካቲት 28 ቀን 2008 ዓ.ም. ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ዋና ጽሕፈት ቤት በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ነው፡፡ ፓርቲውን የማዳከም ሥራ ከውስጥም ከውጭም ተጠናክሮ እንደቀጠለበት የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባው በመግለጫው ወቅት ገልጸዋል፡፡
‹‹መኢአድ ለኢትዮጵያ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር ፈር ቀዳጅ ነው፡፡ ፓርቲው ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ ከውስጥና ከውጭ በሚነሱ ችግሮች የተነሳ መጠነ ሰፊ የሆነ ፈተና ሲጋረጥበት ቆይቷል፡፡ አሁንም በቅርቡ የግል ጥቅማቸውን ባስቀደሙ ግለሰቦች የሚመራ ቡድን በተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች በመደለል ፓርቲውን ለማዳከም ብዙ ጥረት አድርጓል፤›› በማለትም የቀረበባቸው ክስ ፓርቲውን ለማዳከም በተነሱ ኃይሎች እንደተቀነባበረ አመልክተዋል፡፡
የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት ጥር 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ፕሬዚዳንቱ አቶ አበባው መሐሪ ቀጣዩ ጠቅላላ ጉባዔ እስከሚካሄድ ድረስ ማገዱንና ቀዳሚው ምክትል ፕሬዚዳንቱ አቶ አንድርያስ ኤሮ ፓርቲውን እንዲመሩ መወሰኑን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡
ሆኖም የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባውና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ሙሉጌታ አበበ ይህን ውሳኔ ክፉኛ የተቹትና የተቃወሙት ሲሆን፣ ይህን ውሳኔ ያስተላለፉት ግለሰቦች በተለያዩ ምክንያቶች ከፓርቲው የተባረሩና ራሳቸውን ከፓርቲው ያገለሉ ግለሰቦች እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡
‹‹ፕሬዚዳንቱን አግደናል የሚል ውሳኔ ያሳለፉት ግለሰቦች 16 ብቻ ናቸው፡፡ ከእነዚህ 16 ግለሰቦች መካከል ደግሞ ከፓርቲው ጋር ያልተቋረጠ ግንኙነት የነበራቸው አራቱ ብቻ ናቸው፡፡ ስለዚህ ውሳኔው የፓርቲውን መተዳደርያ ደንብም ሆነ የአብዛኛውን አባላት ይሁንታ ያገኘ አይደለም፤›› በማለት አቶ ሙሉጌታ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
‹‹የመኢአድ የምክር ቤት መቀመጫ ብዛት 105 ነው፡፡ እንዴት ነው 16 ግለሰቦች ፕሬዚዳንቱን ማውረድ የሚችሉት?›› በማለት ውሳኔው የአካሄድ ችግር እንደነበረበት ጠቁመዋል፡፡ ‹‹እንኳን 16 ግለሰቦች 105ቱም የምክር ቤቱ አባላት ቢገኙና ቢስማሙም ምክር ቤቱ ፕሬዚዳንቱን የማውረድ ሥልጣን የለውም፡፡ በፓርቲው ደንብ መሠረት ፕሬዚዳንቱን የሚያስቀምጠውም ሆነ የሚያነሳው ጠቅላላ ጉባዔው ነው፤›› ሲሉም አብራርተዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱን ያገደው ቡድን በምክንያትነት ከሚያስቀምጣቸው ነጥቦች መካከል አንዱ ፕሬዚዳንቱ ጠቅላላ ጉባዔ ለማድረግ ፈቃደኛ አይደሉም የሚል ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር ፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔውን መቼ ያካሂዳል በማለት ሪፖርተር ላቀረበው ጥያቄ አቶ አበባው ሲመልሱ፤ ‹‹ምንም እንኳን ቀኑን ባንወስንም በመጋቢት ወር ውስጥ ለማድረግ ዝግጅት አጠናቅቀናል፤›› ብለዋል፡፡
ፓርቲው ከዚህ በተጨማሪም በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰቱ አለመረጋጋቶች በሰላማዊና በድርድር እንዲፈቱ ጥሪ አስተላልፏል፡፡ አቶ አበባው ‹‹የከፋ ቅራኔ ሳይፈጠር የሚመለከታቸው አካላት ሕግንና ከዚህ ቀደም የነበረን የአመጣጥና የአሰፋፈር ታሪክን መሠረት በማድረግ በአስቸኳይ መፍትሔ ይፈለጉለት፤›› ብለዋል፡፡
በሽግግሩ መንግሥት የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) በሚል በታዋቂው የሕክምና ባለሙያ በፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የተመሠረተው ፓርቲ በ1994 ዓ.ም. ለሁለት ሲሰነጠቅ፣ አንዱ ቡድን መኢአድ በሚባል ኅብረ ብሔራዊ ቅርፅ ወዳለው ፓርቲነት ከተለወጠ በኋላ በኢንጂነር ኃይሉ ሻውል እየተመራ በ1997 ዓ.ም. ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲ የነበረው ቅንጅት ቁልፍ አባል እንደነበር ይታወሳል፡፡
መኢአድ በሌሎች የቅንጅት የቀድሞ አባላት ከተመሠረተው አንድነት ፓርቲ ጋር ባለፈው ዓመት በተካሄደው ምርጫ ተፅዕኖ ሊኖራቸው ይችላል ተብለው የተገመቱና በአንድ ወቅትም ወደ ውህደት ሊያመሩ ነው ተብሎ የተነገረ ቢሆንም፣ የምርጫ ቦርድ በውስጥ ክፍፍል ጉዳይ ላይ የሰጠው ውሳኔ እጅግ በተዳከመ ሁኔታ ለምርጫው እንዲቀርቡ አድርጓል ተብሎ ይተቻል፡፡
ከምርጫ ቦርድ ውሳኔ በኋላ ይህን መሰል ውዝግቦች ከሁለቱም ፓርቲዎች መስማት የተለመደ ሲሆን፣ ፓርቲዎቹ ይህ ነው የሚባል እንቅስቃሴ ሲያደርጉም አይስተዋልም፡፡
ማክሰኞ 8 ማርች 2016
በዋሽግተን ዲሲና በተለያዩ የአለም ክፍሎች ኢትዮጵያዊያን የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ
#ETHIOPIA | በዋሽግተን ዲሲና በተለያዩ የአለም ክፍሎች ኢትዮጵያዊያን የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ በዲሲ የፊታችን ማክሰኞ የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ ተደርጓል ቦታውንና ሰአቱን እናሳውቃለን። #SurmaProtests
ሰሙኑን ኢትዮጵያዊያንን በአንድ ስሜት ቆንጥጦ የያዛቸው ጉዳይ የሰው ልጅ የጭካኔ ጣሪያ እስከየት ሊደርስ እንደሚችል የተረጋገጠበት አጋጣሚ ደቡብ ኦሞ ሱርማ በገመድ አንገትና እጃቸው ተቆላልፎ ከአፍና አፍንጫቸው በድብደባ ብዛት የሚፍሰው ደማቸው እያሳዩ የሚያስጥል ወገን አተው በሃዘን የተገላታው ገፅታቸው የሚታይ ፊቶግራፎች ከሰተራጩ በኋላ ኢትዮዽያውያን በያሉበት ቁጣቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው። ይህን በህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ ጉጀሌ መንግስት የተፍፀመን ግፍ ሁላችንም ሰልፉ ጥሪ በተደረገበት ሃገሮች ላይ በነቂስ በመውጣት ልናወግዝ ይገባል።
ሰሙኑን ኢትዮጵያዊያንን በአንድ ስሜት ቆንጥጦ የያዛቸው ጉዳይ የሰው ልጅ የጭካኔ ጣሪያ እስከየት ሊደርስ እንደሚችል የተረጋገጠበት አጋጣሚ ደቡብ ኦሞ ሱርማ በገመድ አንገትና እጃቸው ተቆላልፎ ከአፍና አፍንጫቸው በድብደባ ብዛት የሚፍሰው ደማቸው እያሳዩ የሚያስጥል ወገን አተው በሃዘን የተገላታው ገፅታቸው የሚታይ ፊቶግራፎች ከሰተራጩ በኋላ ኢትዮዽያውያን በያሉበት ቁጣቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው። ይህን በህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ ጉጀሌ መንግስት የተፍፀመን ግፍ ሁላችንም ሰልፉ ጥሪ በተደረገበት ሃገሮች ላይ በነቂስ በመውጣት ልናወግዝ ይገባል።
Indignation and condemnation against inhumane treatment of indigenous people by Ethiopian police
A photo that surfaced on the social media on Sunday showing the Surma
people of South Ethiopia in a chain gang has triggered an uproar and
condemnation against the brutality of the forces of the tyrannical
regime in the country.
The undated
pictures show a group of men, loaded on a police pickup truck, one’s
neck tied to the upper arm of another while also tied at their knees.
The story that circulates with the picture in the social media say the
people were arrested while protesting
the encroachment of their natural habitat by the regime for sugar
plantation. The exact location of the pictures is not clear but the
insignia on the pickup truck is of the police in South Ethiopia.
Previous reports by media and rights groups show thousands of indigenous people in Ethiopia’s lower Omo valley were uprooted due to land grab by officials of the government and their cronies, commercial plantation as well as the building of hydroelectric dams.
Statistics show there are about eight tribes with a total of 200,000 indigenous people in South Omo whose way of life has not been tampered by modernization.
Survival International say it has been a documented fact that those indigenous people were being uprooted from their land without their consent and were exposed to health problems in their new settlement. SI also recalled the recent brutal action by the police against the people of Omo.
The people of the lower Omo valley in Ethiopia have been one of the top tourist attractions in country due to their unique way of life, culture and their interaction with the natural environment.
Previous reports by media and rights groups show thousands of indigenous people in Ethiopia’s lower Omo valley were uprooted due to land grab by officials of the government and their cronies, commercial plantation as well as the building of hydroelectric dams.
Statistics show there are about eight tribes with a total of 200,000 indigenous people in South Omo whose way of life has not been tampered by modernization.
Survival International say it has been a documented fact that those indigenous people were being uprooted from their land without their consent and were exposed to health problems in their new settlement. SI also recalled the recent brutal action by the police against the people of Omo.
The people of the lower Omo valley in Ethiopia have been one of the top tourist attractions in country due to their unique way of life, culture and their interaction with the natural environment.
ዓርብ 4 ማርች 2016
የጃዋር መሃመድ ቅኝቶች
ecadforum
March 4, 2016
ክንፉ አሰፋመገናኛ ብዙሃንን መቼ እና እንዴት መጠቀም እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል። የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ከፈጸመ በኋላ ግን እንደ በረሃ ተኩላ እያደፈጠ ይናከሳል። ሲናከስ ደግሞ ማንንም አይምርም። ውለታ የሚባል ነገር አያውቅም። ይሉኝታ አይነካካውም። እፍረትም በእርሱ ዘንድ የለችም። ከቶውን መቀበል እንጂ መስጠትን አያውቅም። አስር ተቀብሎ በዜሮ የሚሸኝ ጀግና ነው። በዚህ ተግባሩ አድናቂው ነኝ። “እኔ-ነኝ” ያለ የዲሲ ፖለቲከኛን ሳይቀር ከአንዴም ሁለቴ እንደማስቲካ እያኘከ መትፋቱን እንመሰክራለን። የጡት አባቱ የሆነው ኦነግንም ቢሆን ‘A Critical Assessment of the Oromo Liberation Front” በሚለው መጣጥፉ እንዳይሆን እንዳይሆን አድርጎ የጠረበ ፍጡር ነው። ይህ ሰው እንደገና ተመልሶ የ”ነፍጠኛውን ሜድያ” ለመጠቀም የማይሞክርበት ምክንያትም የለም።
ጃዋር በኢትዮጵያ የፖለቲካ ብቅ ያለው በቅርቡ ነው። በመጀመርያም ሆነ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በተማረባቸው ዱሙጋም እና ጭላሎ፣ አዳማም ሆን ሲንጋፖር ሆኖ ድምጹ አልተሰማም። የፖለቲካ ሂሳቡን ሰርቶ ሲያበቃ የበግ ለምድ ለብሶ ብቅ አለ። በሚኖሶታ ያለመውን ቅዠት ይዞ ዋሽንግተን ዲሲ ላይ ሲደርስ ባነነ። እዚያው ላይ ፈነዳ። ከዚያ በፊት ስሙም ተሰምቶ አያውቅም። እስከ ዲሲ ጉዞ ድረስ የኦሮሞ ህመም አይሰማውም ነበር። “ትንሽ ቆሉ ይዞ ወደ አሻሮው… “ እንዲሉ የኦሮሞነት ጆከሩን ይዞ ፖለቲከኞችን እና መገናኘ ብዙሃኑን መቅረብ ነበረበት። እነሱም ከሚገባው በላይ አስተዋወቁት። በደንብ አድርጎ ቦነሳቸው። ምሁር በሃገር የጠፋ እስኪመስል ድረስ መድረኩን እሱ በቻ ተቆጣጠረው። ቪ.ኦ.ኤ.፣ አልጃዚራ፣ ሲ.ኤን. ኤን፣ እና ዶች ቬለ ላይ ሳይቀር እየወጣ የኛን እጣ ፈንታ እስኪበቃን ነገረን። “ወጣቱ ምሁር” አንቱ የተባለ የኢትዮጵያ ጉዳይ ተንታኝ ሆኖ ከረመ። ድምሩን ካወራረድ በኋላ ፊቱን አዞረ። አዟዟሩ አደገኛ ነው። የፍሬቻ ምልክት ሳያሳይ እንደሚታጠፍ መኪና አይነት። “ይህ ሰው በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ የጫነው ዲግሪ ነው ወይንስ ድንጋይ?” እስኪያስብል ድረስ በዘርና በሃይማኖት በፖለቲካ ፈነዳ።
ባጣ ቆዩን ትግል ሲቀላቀል ለአፍ ሟሟሻው አጼ ምኒሊክን አነሳ። የእምዬ ምኒሊክ አጽም እና ሃውልት ላይ ክተት አወጀ። ግዜ የሰጠው ቅል… እንዲሉ እንጂ የመላው ጥቁር ሕዝብ ማንነት መነሻ የሆኑት ምኒሊክ በሱ አፍ የሚጠሩ እንኳን አልነበሩም። ዳሩ መነሻውን የማያቅ መድረሻ የለውም። ሁለት አይን ያለው፤ ከሁለት አቅጣጫ ይመለከታል። ሁለት ጆሮ ያለውም ሁሉንም አመዛዝኖ ይሰማል። አንገት ያለው ደግሞ አዙሮ ያለፈውን ይመለከታል። ያለፈው ከሌለ የወደፊቱ ከምን ሊነሳ? ጃዋር በአምሳሉ የፈጠራቸውን ምስለኔዎችን በሱ የፖለቲካ ዜማ ቃኝቶ ሲያበቃ በፓልቶክ ክፍሎች አሰማራቸው።
ከሁሉም የሚያሳዝነው ደግሞ ገና ነብስ ያላወቁ ሕጻናትን ፎቶ በማህበራዊ ድረ-ገጾች እየበተኑ ለራሳቸው የፖለቲካ ግብ መጠቀም መሞከራቸው ነው። በሞራልም፣ በስነ-ምግባርም ሆነ በባህል ፍጹም ነውር የሆኑ ነገሮችን እያሰሙን አብረን ከረምን። በቃ! የጃዋር ፖለቲካ ይኸው ነው። ይህ ነው የሱ ጀግነነት። ምኞቱ ጀግና መሆን ከሆነ ደግሞ ቦታው ሚነሶታ አልነበረም። ስለ አመጽ የሚሰብክ ወንድ ልጅ መኖርያው ልክ እንደ አንበሳ ከወደ በረሃው ነው።
ይህ ሰው በፌስቡክ ገጹ ላይ ያሰፈረውን አንድ ጽሁፍ ካነበብኩ በኋላ፤ ለዚያ አሳፋሪ ጽሁፍ ምላሽ በመስጠት እና ባለመስጠት ላይ ከራሴ ጋር ሙግት ገጥሜ ነበር። በጃዋር ገጽ ላይ የሰፈረው በዚያ አስጸያፊ ጽሁፍ ያልቆሰለ ቢኖር ጉዳዩ ያልገባው ብቻ መሆን አለበት። በእርግጥ ሌሎች እንዳደረጉት ነገሩን ንቆ መተው ይቻላል። ታድይ የሰው ዝምታ እንደስምምነት የተወሰደ ይመስል የሰውዬው ሙቀት እየጨመረ ሄደ። በተቀረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ላይ የጥላቻ ዘመቻውን ገፋበት። በዓድዋ እና የአጼ ምኒሊክን ቅኝት በአዲስ ዜማ ይዞ ዳግም ብቅ አለ። እንደራሴውን በስውር እየሰበሰበ በባንድራችንና በኢትዮጵያዊነት ላይ ዘመቻ አቀደ። ይህንን በሰፊው እመለስበታለሁ።
በፌስቡክ ገጹ ላይ የሰፈረው የጃዋር መልእክት እንዲህ ይነበባል፤
…Enjoy the show, the bill is on us… ወደ አማርኛ በግርድፉ ሲመለስ “(የኦሮሞ አመጽ) ትዕይንቱን እያያችሁ ተዝናኑ። ሂሳቡን በኛ ተውት።” እንደማለት ነው።
አሳዛኙን የኦሮሞ ወገኖቻችን እልቂት ነው ተዝናኑበት እያለን ያለው። ይህንን አሰቃቂ ድራማ ከሚነሶታ ሆኖ ሲመለከተው አስቂኝ ነው የሆነበት። እሱ ምን አለበት? እሳቱ ውስጥ አልገባ። ወላፈኑም ፈጽሞ አይነካው። ምሰቆቃውን እንደ ሆሊውድ ፊልም ቁጭ ብሎ መመልከቱ ሳይንሰው ሌሎችንም በራሱ ወጪ ለመጋበዝ የሚዳዳው ደፋር። ይህ ስላቅ ነው ወይስ ፌዝ? ከሞቀ ቤቱ መሽጎ በሰው ልጅ ሰቆቃ መቀለዱ አንድ ነገር ነው። ከሁሉም የሚያስገርመው ደግሞ በዚህ ጽሁፍ ስር ድጋፋቸውን የሚገልጹ እንደራሴዎቹ ብዛት ነው። ሰው በዘር ፖለቲካ ሰክሮ ማሰብና ማገናዘብ ተስኖታልም ያሰኛል። ጽሁፉ በግልጽ እንደሚያስረዳው እየተካሀደ ያለው እልቂት ላይ ጃዋር ማፌዙ አልገባቸው ይሆን? በዚያው የፌስ ቡክ ገጽ ላይ የሚወጡ ዘግናኝ ፎቶዎችን እየተመለከተ የሚዝናና ሰው ካለ ይህ ጤነኛ አይደለም። የአእምሮ ችግር ያለበስ ሰው እንኳን በዚህ አይነቱ የሰዎች ሰቆቃ የሚዝናና አይመስለኝም። ግን የዚህ ሰው ፍላጎት ምን ይሆን?
በዚያ ሰሞን ወዳጄ ሄኖክ የሺጥላ የለቀቀው ጽሁፍ ጃዋርን በደንብ አድርጎ ይገልጸዋል።
“እንጀራውን” በተገፉ እና በተከፉ ሰዎች ታሪክ ላይ ያደረገ ሰው ፣ ህይወቱን በሰዎች መከራ ላይ የገነባ ፣ ኑሮውን ባጋጣሚ ለድምጽ አልባ እና አቅም አልባ ወገኖቹ ለታይታ የሚቆጭ…. ራሱን ትልቅ ለማድረግ፣ ከፊት ሆኖ ለመታየት እና ለመግነን ማናቸውንም አይነት ክፋት ከመፈጸም ልቡ ተው የማይለው ሰው። ሲል ሄኖክ ይገልጸዋል። እኔም ጃዋርን ከዚህ በተሻለ አልገልጸውም።
ሲጀመር እየተካሄድ ባለው የኦሮሞ ወንድሞቻችን የመብት ትግል ውስጥ የእነ ጃዋር እጅ መግባቱ አብዛኞችን ጥርጣሬ ውስጥ ከትቷል። ምክንያቱም ግልጽ ነው። የኦሮሞ ወጣቶች እና ገበሬዎች ስለ መብት ሲሟገቱ የእነ ጃዋር አጀንዳ ደግሞ ሌላ በመሆኑ።
የኦሮሞ ተማሪዎችና ገበሬዎች ይዘውት የተነሱት ጥያቄ አግባብ ያለውና በመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊደገፍ የሚገባው ጉዳይ ሆኖ ሳለ ሌላው ወገን ዳር ቆሞ የመመልከቱ ምስጢር ግልጽ ይመስላል። እነዚህ ወገኖች መብታቸውን ለማስከበር የማያባራ ትግል እያደረጉ ባሉበት ወቅት እነጃዋር በረጅሙ ምላሳቸው ሌላውን ወገን የሚያስበረግጉ መፈክሮችን ይዘው ብቅ አሉ። “ኦሮሚያ ለኦሮሞ!” እና “የክርስትያኑን አንገት መቁረጥ!” መፈክር!
እርግጥ ነው። ጃዋር ረጅም ምላስ አለው። ወገን የሚሻው ደግሞ ረጅም ምላስ ሳይሆን ረጅም ጭንቅላት ነበር። የሁለቱ ልዩነት የትየለሌ ነው። ረጅም ጭንቅላት አርቆ ሲያስብ ረጅም ምላስ ደግሞ ከሩቅ ይስባል። እንደ አለመታደል ሆኖ ባለ ረጅም ምላሶች የህዝብን የመብት ጥያቄው እየነጠቁ በራሳቸው አጀንዳ ይተኩታል። እናም የዚህ ትግል ውስጥ ሌላው ወገን ተመልካች ብቻ እንዲሆን ያደረጉት ጃዋር እና በሱ የፖለቲካ ቅኝት ውስጥ ያሉት ደቀ መዛሙርቱ ናቸው። እነዚህ ሰዎች ይዘውት የተነሱት መፈክር ሌላውን ወገን ባያስበረግግ ነበር የሚገርመው። አንዳንድ ቦታዎች የጃዋርን መፈክር የያዙ ሰልፈኞችን የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች ማሰማራታቸውን ማስተዋሉ ለዚህ ማስረጃ ይሆናል።
በአንድ ወቅት በጃዋር የሚመራ ይህ ቡደን ዋሽንግተን ዲሲ ስቴት ዲፓርትመንት በር ላይ ቆሞ፣ “Ethiopia out of Oromia”! “ኢትዮጵያ ከኦሮሚያ ጥውጣ!” እያለ ፈረንጆችን ይማጸን የነበረበትን ማስረጃ ከዩቱብ ላይ መመልካት ይቻላል። (https://www.youtube.com/watch?v=uXah_qtW8sg)
በሌላ ግዜ ደግሞ “…እኔ በምኖርበት አካባቢ ቀና የሚል ክርሲያን ከተገኘ አንገቱን በሜንጫ ቆርጠን እንጥላለን::”(https://www.youtube.com/watch?v=RMLLmAMWdG8) ሲል የአይሲስን አንገት ቆረጣ በአደባባይ ያበሰረ ሰው ነው። እዚህ ላይ ልብ በሉ። ወንጀል የሰራን ክርስትያንን ሳይሆን “ቀና የሚል” ከተገኘ ነው እናርዳለን ያለው። ልቡ ያሰበውን እና አእምሮው የሚትያሰላስለውን ነው ያፈነዳው። የተናገረው በስህተት እንኳን ቢሆን ንግግሩን ባስተባበለው ነበር።
ከዶ/ር መረራ ጉዲና ጋር አንድ ምሽት በአምስተርዳም ስንጫወት፣ “በእርግጥ ጃዋር መሃመድ የክርስቲያን አንገት እቆርጣለሁ ብሎ ተናግሯል?” ሲል ጠየቀኝ። አብሮን የነበረው ገረሱ ቱፋም “ንግግሩን ከኮንቴክስት መረዳት አለብን…” እያለ ሲያስረዳ ሞከረ። ገረሱ ቱፋ በዩኒቨርሲቲ ለኦሮሞ መብት ሲታገል ቆይቶ በኋላም በአስመራ በኩል ሞክሮ ሲያበቃ በሆላንድ በስደት የሚኖር ወጣት ነው። ኮንቴክስቱ ባይገለጽልንም ከዩትዩብ ላይ ያወጣሁት ቪድዮ አንገት በሜንጫ ስለመቁረጥ በግልጽ አማርኛ አስቀምጦታል። በዚያ እለት ነበር የኦሮሞ ሕዝብ በብዛት የሚኖረው በሸዋ እንድሆነና ይህም የክርስትና እምነት ተከታይ መሆኑን ዶ/ር መረራ ያስረዳን።
በእነ ማልኮሜክስና በእነ ማርቲን ሉተር ምድር ቁጭ ብሎ አይሲስን አንገት መቅላት ወንጀል መናገሩ አይደለም የሚገርመው። ይህንን በአደባባይ በኩራት ሲናገር ህግ ባለበት ሃገር ዝም መባሉ እንጂ።
አል ጃዚራ ላይ ወጥቶ ኢትዮጵያዊነት በላዩ ላይ እንደተጫነበትም ደስኩሯል። ይህንን ዲስኩር ከሱ ውጭ ከሌሎች የኦሮሞ ልሂቃን አልሰማንም። በማንነት ቀውስ ውስጥ ካለ ሰው ይህንን መስማቱም ሊደንቀን አይገባም። ይልቁንም ይህንን ከነ በቀለ ገርባ ፣ ከዶ/ር መረራ፣ ከበአሉ ግርማ ፣ ከሎረት ጸጋዬ ገ/መድህን፣ ከዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ወይንም ከአቶ ቡልቻ ደመቅሳ አንደበት ብንሰማው እበር የሚከብደን። በእንደዚህ አይነት የጥላቻና የዘረኝነት እምሮው የታወረ ሰው እመራዋለው የሚለው አመጽ ላይ ለማበር የኢትዮጵያ ህዝብ ፈቃደኛ ባይሆን ሊደንቀን አይገባም። ከየትኞቹም የኦሮሞ ልሂቃን እንዲህ አይነት የኦሮሞ ሕዝብን ክብር የሚነካ ንግግር ሰምተን አናውቅም። “ኢትዮጵያ ከኦሮሚያ ትውጣ” “የክርስትያኑን አንገት በሜንጫ እንቆርጣለን” ሲል የትኛው የኦሮሞ ወገን ወይንም የትኛው የሙስሊም ህብረተሰብ ጃዋርን እንደወከለው አናውቅም። ልቡን ሞልቶ ሲናገር ግን የኦሮሞን ህዝብ ከሌላው ወገን ነጥሎ ለማስመታት የታቀደ አደጋ ላይ ሊጥለው እንደሚችል ግልጽ ነው።
የፖለቲካውን ምህዳር ጠቆጣጥረው ዘረኝነትን እና ጥላቻን ሲሰብኩ ምን እናደርጋለን? ንቆ መተው ወይንስ ቀይ መብራት ማሳየት? ቤንጃሚን ፍራንክሊን፣ ስለጥቃቅን ነገሮች ሲናገር፣ “በጥቃቅን ነገር ተጠንቀቅ፤ ትንሽ ፍሳሽ – ትልቅ መርከብን ታሰምጣለች።” ብሎ ነበር። በእርግጥ መርከቡ ሊሰምጥ የሚችለው ውሃ መርከብ ውስጥ እንዲገባ ስንፈቅድላት ብቻ ነው።
የጃዋርን አካሄድ ሳሰላስለው ቦካሳ ይታወሰኛል። የትም አይደርስም የተባው የማእከላዊ አፍሪካው አስር አለቃ ቦካሳ፣ ሁለቱም ተመሳሳይ አመጣጥ አላቸው። ሁለቱም በማንነታቸው የሚያፍሩበት የበታችነስ ስሜት ውስጥ የኖሩ ናቸው። ሁለቱም የማንነት ቀውስ ውስጥ የነበሩ ናቸው። ጃዋር በአንደበቱ እንደነገረን የአማራ እና የኦሮሞ፣ የክርስትያን እና የሙስሊም ቅልቅል ነው። እንደዚህ የተበሳተሩ ብዙ አሉ። አብዛኞቹ ታዲያ በማንነታቸው ይኮራሉ። እንደ ጃዋር ያሉ ጥቂቶች ግን የስነ-ልቦና ቀውስ ውስጥ ቢገቡ አይደንቅም። አባት እና እናቱን የማያውቀው ቦካሳ ከ 12 አመቱ ጀምሮ የማንነት ጥያቄ ሲያንገላታው የነበረ ሰው ነው። የም ሆኖ የትም አይደርስም እየተባለና የተናቀ ወታደር ነበር። የሃገሪቱ ርእሰ ብሄር ይሆናል ብሎ ያሰበ አልነበረም። አስር አለቃ ቦካሳ በለስ ቀንቶት እ.ኤ አ. 1966 በመፈንቅለ መንግሰ ስልጣን ይዞ ሲያበቃ የማእከላዊ አፍሪካን ህዝብ ጭካኔ በተሞላበት መንገድ ፈጀ ሀገሪቱን እንዳልነበረች አደረጋት።
ሰዎች ለአዶልፍ ሂትለርም የነበራቸው አመለካከት ከዚህ የተለየ ልነበረም። አንድ የጀርመን ታሪክ ተመራማሪ ሁኔታውን ሲገልጸው “They all had one thing in common – they underestimated Hitler” ነበር ያለው። ሁሉም የሚጋሩት አንድ ነገር ነበር። ሁሉም ሂትለርን ንቀውት ነበር። በመጨረሻ ሂትለር የጀርመን አዲሱ ቻንስለር ሆኖ ብቅ ሲል የናዚ ፓርቲ አባላት በደስታ እና በእንባ ተቀበሉት። በሀገሪቱ ህግ ሳይሆን በሂትለር አምላኪ ሆኑ። የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ሳይሆን የጃዋር አምላኪዎች እያደረጉ እንዳሉት ማለት ነው። ጃዋር “የእልቂቱን ትእይንት በኔ ሂሳብ እያያችሁ ተዝናኑበት” ያለውን አጢነው አይመስለኝም። በደፈናው ስለሚያመልኩት እንጂ።
ቦካሳም ሆነ ሂትለር በጥላቻ የመጡ ስለነበሩ ከምደር-ገጽ ጠፍተው ታሪክ ሆነው አልፈዋል። ጥለውት የሄዱት አሻራ ግን እስካሁን አለ።
እሑድ 21 ፌብሩዋሪ 2016
በኦሮሚያ ክልላዊ መስተዳደር አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማወጅ የቀረበው ሃሳብ በሕወሓት ውድቅ ተደረገ::
በኦሮሚያ ክልላዊ መስተዳደር አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማወጅ የቀረበው ሃሳብ በሕወሓት ውድቅ ተደረገ::
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – የወያኔን ትንፋሽ በጣረ ሞት የሸበበው የኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ ቀጥሏል::በተለያዩ ወረዳዎች የቀጠለው ተቃውሞ ሕዝቡ በወያኔ አገዛዝ የሚደረግበትን የፖለቲካ ጫና የኢኮኖሚ በደል እና ወታደራዊ እርምጃዎች በመቃውም ተቃውሞውን ለማሰማት አደባባይ የወጣ ሲሆን በየአከባቢው መንገዶችን በመዝጋት ለለውጥ ያለው ቁርጠኝነት በትግሉ እያሳየ ይገኛል::በተለየ ሁኔታ በሃረርጌ ጉራዋ በዳዋ አከባቢ እንዲሁም በበደኖ ተቃውሞ የተደረገ ሲሆን በዳዋ ያሉ ነዋሪዎች የአግኣዚ ሰራዊት ወደ በደኖ ዘልቆ ለመግባት ሙከራ ሲያደርግ ድልድዩን በመዝጋት የመግባት አላማውን አጨናግፈውበታል::
በሻሸመኔ በአምቦ በወለጋ ቀለም ወረዳ በተከታታይ የሚደረጉት ተቃውሞዎች በዛሬው እለት ቀጥለው የዋሉ ሲሆን በጉጁ በተደረገው የቦኮ የአገር ሽማግሌዎች በየ8 አመቱ የሚፈጸመው የመሪዎች ሽግግር እንደተለመደው የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳደር በሃገር ውስጥ ስላሌለ የተገኘው አሻንጉሊቱ ሙላቱ ተሾመ የተባለው የወያኔ ሹም ፕረዚዳንት ሲሆን በከፍተኛ የደህንነት እና ወታደራዊ ኮማንዶዎች አጀብ ተከቦ ውሏል::ርእሰ መስተዳደሩ ሙክታር ከድር ለሕክምና ባንኮክ ነው ይባል እንጂ ምናልባት በቁም እስር ላይ ሊሆን ይችላል የሚሉ የደህንነት ማስረጃዎች ተገኝተዋል::የአግኣዚ ወታደሮች አብዛናው የኦሮሚያ ክልል ከተሞችን ከበው እጥረት ለመፍጠር ቢሞክሩም ሕዝቡ ያለውን አቋም ዝንፍ ሳያደርግ በተቃውሞ ትግሉን ገፍቶበታል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ በኦሮሚያ ክልላዊ መስተዳደር አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ የኦሕዴድ ከፍተኛ አመራር ሁለት አባላት በወይዘሮ አስቴር በኩል ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረቡት ሃሳብ አሻንጉሊዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ሳይደርስ በደህንነት ሹሙ በአላቃ ጸጋይ ውድቅ መደረጉን ምንጮች ጠቁመዋል::ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ ኦሮሚያ የጦርነት ቀጠና ትሆናለች ያሉ አመራሮች ከሕወሓት የተሰጣቸው መልስ ግን ልክ እናስገባቹሃለን የሚል ነው::ከባለፈው ግምገማ በኋላ በሕወሓት እና በኦሕዴድ አመራሮች መካከል ከፍተኛ የከንፈር መነካከስ እንዳለ ሆኖ አለመተማመኑ እና በጥርጣሬ መተያየቱ ስብሰባዎችን እየወገኑ መጥራት እና የማይፈለጉ አባላትን ማግለል እና ማስደንገጥ በሕወሓት እየተፈጸመ መሆኑ ሲገለጽ ተቃውሞውም እየጋለ መምጣቱ ታውቋል::ሕወሓት በአሁን ወቅት ተቃውሞ በርዶ የክልሉን ባለስልጣናት በሰበብ በማሰር በማባረር እና በመበታተን በመፐወዝ ካድሬዎችን አዳዲስ ኦሮሚኛ በተማሩ የሕወሓት ሰዎች በመተካት አዲስ የጭቆና ስልት ለማስፈጸም ዝግጅት እያደረገ ይገኛል::ኦሮሚያ በከፍተኛ ደረጃ በተቃውሞ ባለችበት በዚህ ወቅት ላይ የአግኣዚ ጦር የዘር ማጥፋት ስራ ላይ ተሰማርቶ ባለበት በዚህ ቀውጢ ሰአት ላይ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አላውጅም ሲል ወያኔ ማገዱ ለሕዝብ ሕይወት ደንታ ቢስነቱን ከማሳየቱም በላይ ተቃውሞውን አቅልሎ ለማሳየት መሞከሩ የባሰ እያጋጋለው እንደመጣ ታውቋል::#ምንሊክሳልሳዊ

ዓርብ 19 ፌብሩዋሪ 2016
የበይነመረብ ዘመቻ ጋዜጣዊ መግለጫ : Online Campaign Press Release
የዘመቻው ርዕስ፦ የኅሊና እስረኞች ይፈቱ!
የዘመቻው ቀናት፦ የካቲት 16-17, 2008
የዘመቻው ዓላማ፦
1ኛ) በግፍ የታሰሩ ጓደኞቻችን እንዲሁም ሁሉም የኅሊና እስረኞች (በምርመራ ቀጠሮ ላይ ያሉ፣ ክስ ተመስርቶባቸው ፍርድ ቤት የሚመላለሱ እና የተፈረደባቸው) ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ መንግሥትን ለመጠየቅ እና ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር የሚሠሩ አካላትም ተፅዕኖ እንዲያደርጉ ለመጠየቅ፤
2ኛ) በየእስርቤቱ ያሉ የፖለቲካ እስረኞች ያሉበትን ሁኔታ ለሕዝብ ማሳወቅ፤
3ኛ) ስለመረጃና የመናገር ነፃነት፤ ስለፍትሕ፣ ስለመንቀሳቀስ መብት፤ እና መሰል ሰብኣዊ መብቶች ግንዛቤ ማስጨበጥ እና መንግሥት እነዚህን መሠረታዊ መብቶች እንዲያከብር ዜጎች እስከጥግ ስለመብታቸው በመጠየቅ የድርሻቸውን እነወዲወጡ ማበረታታት።
የዘመቻው ቦታ፦ ዘመቻው በዋነኛነት የሚካሄደው ‹‹ፌስቡክ›› እና ‹‹ትዊተርን›› በመጠቀም ይሆናል፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ ጦማሪዎችና የዜና አውታሮች በየጦማሮቻቸው ላይ በመጻፍ ዘመቻውን መቀላቀል ይችላሉ።
የዘመቻው ዋና፣ ዋና ሃሽታጎች፦ #FreeAllPoliticalPrisoners #ሁሉም_የኅሊና_እስረኞ_ችይፈቱ #FreeZelalem #ዘላለም_ይፈታ #FreeEthiopia #ኢትዮጵያ_ትፈታ #FreeAllBloggersAndJournalists #ጋዜጠኞችና_ጦማሪዎች_ይፈቱ #FreeJournalists #ጋዜጠኞች_ይፈቱ
የዘመቻው ተሳታፊዎች፦ ያገባናል የሚሉ ሁሉ!
ዘመቻው ላይ መሳተፍ የሚቻልባቸው መንገዶች፦
1ኛ) በዘመቻው ወቅት ዘማቾች ፕሮፋይል ፎቶዎቻቸውን እና የከቨር ምስሎቻቸውን ለዘመቻው በተዘጋጁ የፖለቲካ እስረኞች ፎቶዎች (ወይም ራሳቸው ባዘጋጁት ምስል) እነወዲሁም አባባሎች በማስዋብ መቀየር፣
2ኛ) በየዕለቱ የተለያዩ ግንዛቤ የሚያስጨብጡ፣ በፖለቲካ እስረኞች አያያዝ፣ በፍርድ ቤት ቤት ሒደት እና መሰል ጉዳዮች ላይ የሚያውቁትን መረጃ በመጻፍ እና የተጻፉትንም በማጋራት፣
3ኛ) ስለሚያውቁት የፖለቲካ እስረኛ ማንነት እና ስለእስሩ ዝርዝር መረጃዎችን በማጋራት፣
4ኛ) መጠየቅ የሚፈቀድላቸው የፖለቲካ እስረኞችን በመጠየቅ አሰተያየቶቻቸውን እና ያሉበትን ሁኔታ መልሶ ለሕዝብ በማድረስ፣
5ኛ) ከፖለቲካ እስረኛ ቤተሰቦች ጋር በመነጋገር ያሉበትን ጥቅል ሁኔታ ይፋ በማድረግ… እና ወዘተ።
——
ዘላለም ወርቃገኘሁ ደ ብርሃን ብሎግ ላይ አጋር ጦማሪ ሆኖ ሰርቷል። በታሰረበት ወቅት ሃምሌ ሁለትሺ ስድስት በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን የማስተርስ ዲግሪ ተማሪ ነበር። ከአራት ወራት በሁዋላ ሲከሰስ የግንቦት ፯ አባል በመሆን፤ በዓረቡ አገር የተከሰተው ሽብር በኢትዮጵያም ተከስቶ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በአመጽ ለመጣል ሰዎች መልምሏል ፣ ለዚህም የሚጠቀምበት አሥር ሺሕ ብር ተልኮለታል ተብሎ ተከሷል። በተጨማሪም ማኅበራዊ ድረ ገጽ በመክፈት፣ በአንድ አገር በአመጽና በግጭት ማኅበራዊ ለውጥ የሚመጣበትን ማብራሪያ የሚጠይቅ መልዕክት ተላልኳልም ተብሎ ተከሶ ነበር:: ይሄ ብቻ አደለም ስለጎንደር ዩንቨርሲቲ ረብሻ በፈረንጆች አቆጣጠር ፳፩፩ መፃፉና ይህም በውጭ አገር ባሉ ድህረ ገፆች ላይ መውጣቱ፣ ሃገር ቤት ውስጥ ካሉ ጓደኞቹ ጋራ ስለፖለቲካ መወያየቱ መምከሩ ሁሉ በክሱ ወስጥ ተጠቅሰዋል። ከዘላለም ጋራ ሌሎች ሁለት ጓደኞቹ ታስረዋል፥ ዮናታን ወልዴና ባህሩ ደጉ፣ ጥፋታቸው ደሞ አንድ አሜሪካን አገር ያለ ኢትዮጲያውዊ ጋዜጠኛ አለ ባለው የኢንተርኔት ስልጠና ላይ ለመካፈል በማመልከታቸው። ክሱ ግን የሽብር ስልጠና ነው ይለዋል።
ከስድስት ወር በፊት ፍርድ ቤቱ ብዙዎቹን ክሶች ውድቅ አድርጎ አባላት ለመመልመል መሞከርና የኢንተርኔት ስልጠናውን ማመቻቸት በሚሉት ላይ እንዲከላከሉ ወሥኖ ነበር። በዚህም መሠረት ሁሉም የመከላከያ ምስክሮች የተሰሙ ሲሆን (ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጨምሮ)፤ በየካቲት 16 የመጨረሻው የመከላከያ ምስክር አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንዲሰሙ ቀጠሮ ተይዟል። ዘላለም አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን መከላከያ ምስክር አድርጎ የጠራው በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ተገናኝተህ ነበር የሚል ክሱ ውስጥ ስለተካተተ ነው።
ደብርሃን ብሎግና ወዳጆቻችን የሁለት ቀን የበይነ መረብ ዘመቻ አዘጋጅተናል። በዚህ ዘመቻ ላይ በመሳተፍ እነዘላለምንና እነሱን የመሳሰሉ ሰዎች ከእስር እንዲፈቱ፤ ይህን አይነትም ኢፍትሃዊነት እንዲበቃ በጋራ እንድንጠይቅ ጋብዘናችሗል።
ስለ ተከሳሾቹ ወይም ስለክሶቹ ጠለቅ ያለ መረጃንማግኘት ይህን: ይህን: ይህን: ይህን ወይም ይህን ማስፈንጠሪያ ወይም ሊንኮች ይጠቀሙ።
ረቡዕ 17 ፌብሩዋሪ 2016
መኢአድ ፓርቲ እርስ በርሱ ሲባላ በደቡብ የወያኔ-ደህንነት ቢሮ ሶስት የተቃዋሚ አመራሮችን አፍኗል::
ወያኔ ሰላማዊ ፓርቲዎችን እና አመራሮችን ማሸበሩን ቀጥሏል::በኢንጂነር ሃይሉ ሻውል ፓርቲ መኢአድ ውስጥ በፕሬዚደንቱ አበባው መሃሪ እና በማእከላዊ ምክር ቤቱ መካከል በተነሳው አምባጓሮ ደክሞ የነበረው ፓርቲ ተሽመድምዶ እየሞተ ነው ሲሉ አባላቱ ማማረራቸው ሲታወቅ አቶ አበባ ያልታወቀ ሃይል መከታ በማድረግ የፍርድ ቤት ማገጃ በመጣስ ማህተሙን ለሕገወጥ ስራ እየተጠቀሙበት ነው ሲሉ አባላቱ ይናገራሉ::
አቶ አበባው መሃሪ በመኢአድ ማዕከላዊ ምክርቤት በጥር 15 ቀን, 2008 ዓ.ም ከፕሬዚዳንትነት ሃላፊነታቸው የማንሳቱን ውሳኔ እና በጥር 23 ቀን, 2008 ዓ.ም በፍርድቤት ተከሰው የድርጅቱን ማህተም እንዳይጠቀሙ መታገዳቸውን አምነው እና አክብረው ከተቀበሉ በኋላ ፤በህገወጥ መንገድ የፓርቲው ማዕከላዊ ምክር ቤትን ውሳኔ እና የፍርድቤት የዕግድ ትዕዛዝ በመጣስ የፓርቲውን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ እንድሪያስ ጨምሮ ሌሎች የላዕላይ ምክር ቤት አባላትን በግላቸው አግጃለው እያሉ ደብዳቤ እያሰራጩ መሆኑ ስለተደረሰባቸው ፓርቲው በማጭበርበር ወንጀል ሕግ ሊጠይቃቸው ነው ። ሲሉ አባላቱ ተናግረዋል::
አቶ አበባው መሃሪ በመኢአድ ማዕከላዊ ምክርቤት በጥር 15 ቀን, 2008 ዓ.ም ከፕሬዚዳንትነት ሃላፊነታቸው የማንሳቱን ውሳኔ እና በጥር 23 ቀን, 2008 ዓ.ም በፍርድቤት ተከሰው የድርጅቱን ማህተም እንዳይጠቀሙ መታገዳቸውን አምነው እና አክብረው ከተቀበሉ በኋላ ፤በህገወጥ መንገድ የፓርቲው ማዕከላዊ ምክር ቤትን ውሳኔ እና የፍርድቤት የዕግድ ትዕዛዝ በመጣስ የፓርቲውን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ እንድሪያስ ጨምሮ ሌሎች የላዕላይ ምክር ቤት አባላትን በግላቸው አግጃለው እያሉ ደብዳቤ እያሰራጩ መሆኑ ስለተደረሰባቸው ፓርቲው በማጭበርበር ወንጀል ሕግ ሊጠይቃቸው ነው ። ሲሉ አባላቱ ተናግረዋል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ በደቡብ ክልል ሲዳማ አርነት ንቅናቄ አመራሮች ባለታወቀ ምክንያት ከያሉበት በደህንነት ሃይሎች ታፍነው መታሰራቸው ታውቋል።በዚህም መሰረት የታፈኑ አመራሮች
1ኛ ደሳለኝ ሜሳ(ሲአን ፖሊቲካ ዘርፍ ኃላፊ )
2ኛ ተሾመ ደበበ (የሲአን ወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ)
3ኛ ደበሳ ዳካ ( የሲአን ቱላ ዞን ሊቀመንበር) ሲሆኑ የደቡብ ክልል ደህነቶችና ፖሊሶች ተባብረው አመራሮቹ በማፈን ወደ ተለያዩ እስር ቤቶች መወሰዳቸው ታውቋል::
1ኛ ደሳለኝ ሜሳ(ሲአን ፖሊቲካ ዘርፍ ኃላፊ )
2ኛ ተሾመ ደበበ (የሲአን ወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ)
3ኛ ደበሳ ዳካ ( የሲአን ቱላ ዞን ሊቀመንበር) ሲሆኑ የደቡብ ክልል ደህነቶችና ፖሊሶች ተባብረው አመራሮቹ በማፈን ወደ ተለያዩ እስር ቤቶች መወሰዳቸው ታውቋል::
ሰማያዊና መድረክ ከስዊድን የፓርላማ አባላት ጋር ተወያዩ
የሰማያዊ እና የመድረክ ፓርቲዎች አመራሮች ከስዊድን የፓርላማ አባላት ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ተናግረዋል፡፡
የፓርቲዎቹ አመራሮች የሆኑት ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ፣ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት እና ዶ/ር መረራ ጉዲና ከስዊድን ፓርላማ የውጭ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ልዑክ ጋር በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ዛሬ የካቲት 9/2008 ዓ.ም መወያየታቸው ታውቋል፡፡
የፓርቲ አመራሮቹ ከስዊድን ስድስት ፓርቲዎች ከተውጣጡ 11 የልዑካኑ አባላት ጋር በተወያዩበት ወቅት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ በተቀሰቀሰው የህዝብ ተቃውሞ እና በጋምቤላ ክልል ስለነበረው ግጭት ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡
አመራሮቹ ለተቃውሞ አደባባይ በወጣው ህዝብ ላይ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እየወሰዱት ያለውን እርምጃ በተመለከተም በውይይታቸው አንስተዋል፡፡
አሁን ላይ በኢትዮጵያ የተቃውሞ ድምጽ የሚያሰሙ የፓርቲ አባላትን እና በነጻነት ስራቸውን በሚያከናውኑ ጋዜጠኞች ላይ እንዲሁም በአጠቃላይ ተቃውሞ በሚያሰማው ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው አፈና እየጨመረ መሆኑንና በሀገሪቱ ፓርላማም አንድም ተቃዋሚ ድምጽ የማይሰማበት መሆኑን እንደገለጹላቸው ታውቋል፡፡
የስዊድን ፓርላማ አባላትም የተቃዋሚ ፓርቲዎች እያደረጉት ስላለው የፖለቲካ እንቅስቃሴና በጋራ ስለሚሰሩበት ጉዳይ ጥያቄ አንስተው በፓርቲዎች አመራሮች ገለጻ እንደተደረገላቸው ኢ/ር ይልቃል ተናግረዋል፡፡
የስዊድን የፓርላማ አባላት ጠ/ሚ ኃ/ማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር እንደተወያዩም ለማወቅ ተችሏል፡፡
የፓርቲዎቹ አመራሮች የሆኑት ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ፣ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት እና ዶ/ር መረራ ጉዲና ከስዊድን ፓርላማ የውጭ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ልዑክ ጋር በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ዛሬ የካቲት 9/2008 ዓ.ም መወያየታቸው ታውቋል፡፡
የፓርቲ አመራሮቹ ከስዊድን ስድስት ፓርቲዎች ከተውጣጡ 11 የልዑካኑ አባላት ጋር በተወያዩበት ወቅት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም በኦሮሚያ በተቀሰቀሰው የህዝብ ተቃውሞ እና በጋምቤላ ክልል ስለነበረው ግጭት ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡

አሁን ላይ በኢትዮጵያ የተቃውሞ ድምጽ የሚያሰሙ የፓርቲ አባላትን እና በነጻነት ስራቸውን በሚያከናውኑ ጋዜጠኞች ላይ እንዲሁም በአጠቃላይ ተቃውሞ በሚያሰማው ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው አፈና እየጨመረ መሆኑንና በሀገሪቱ ፓርላማም አንድም ተቃዋሚ ድምጽ የማይሰማበት መሆኑን እንደገለጹላቸው ታውቋል፡፡
የስዊድን ፓርላማ አባላትም የተቃዋሚ ፓርቲዎች እያደረጉት ስላለው የፖለቲካ እንቅስቃሴና በጋራ ስለሚሰሩበት ጉዳይ ጥያቄ አንስተው በፓርቲዎች አመራሮች ገለጻ እንደተደረገላቸው ኢ/ር ይልቃል ተናግረዋል፡፡
የስዊድን የፓርላማ አባላት ጠ/ሚ ኃ/ማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር እንደተወያዩም ለማወቅ ተችሏል፡፡
ረቡዕ 3 ፌብሩዋሪ 2016
በኦሮሚያ ክልል አዲስ የጸጥታና የደህንነት/ስለላ መዋቅር ሊዘረጋ ነው::በጋምቤላ የሕወሓት ባለስልጣናትና ቤተሰቦቻቸው ንብረት በታጠቁ የደቡብ ሱዳን ቅጥረኞች እና በአግአዚ ወታደሮች መጠበቅ ተጀምሯል::
ልዩነት ውበት ነው…ግን አልፈጠረብንም::መቻቻል ያልተጋባቸው ያልበሰሉ ጭፍኖች በ2 ጽንፍ ማሕበራዊ ድህረገጾችን ወረዋል:: #Ethiopia #Oromoprotests #Gambella #MinilikSalsawi
በኦሮሚያ ክልል አዲስ የጸጥታና የደህንነት/ስለላ መዋቅር ሊዘረጋ ነው::በጋምቤላ የሕወሓት ባለስልጣናትና ቤተሰቦቻቸው ንብረት በታጠቁ የደቡብ ሱዳን ቅጥረኞች እና በአግአዚ ወታደሮች መጠበቅ ተጀምሯል::
===========================================================
Minilik Salsawi – በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አከባቢዎች አሁንም ውጥረት የነገሰ መሆኑን የደህንነት ቢሮ የሚደርሱ ሪፖርቶች እንደሚጠቁሙ ለጉዳዩ ቅርበት ያላችው ወገኖች መረጃ ሰጥተዋል::በኦሮሚያ ክልል በጥሩ ክፍያ በፎቶግራፍ እና በቭድዮ ቀረጻ ላይ ተሰማርተው የነበሩ የኦሕደእድ ካድሬዎች እየተለቀሙ መሆኑ ታውቋል::የወያኔው ጁንታ አገዛዝ አስፈላጊውን ግድያና የጅምላ እስር ከፈጸመ በኋላ ለይስሙላ የመለሳለስ ባሕሪያ በማሳየት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን አቆምኩት እንዲሁም የሕዝቡ ጥያቄ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ነው በሚል የሰራውን እኩይ ተግባር ለመሸፋፈን ቢዳክርም የሕዝቡ ተቃውሞ እያገረሸ ብሎም እንዳተኮሰ ይገኛል::መሰሪ እና ውሸታም የሆነው የወያኔ አስተዳደር ላይ ላዩን በመለሳለስ ውስጥ ውስጡን አዲስ የጸጥታ እና የደህንነት/ ስለላ መዋቅር ሊዘረጋ ሲሆን ሕዝቡ ግን አሁንም ለአንድ ለአምስት የአፈና መዋቅር ያልተበገረ ለአዲሱም የስለላ መዋቅር እንደሚያስቸውግር ስጋት መኖሩት የወያነ የደህንነት መረጃዎች ጠቁመዋል:: የመዋቅሩ አዘረጋግ በተመለከተ አስፈላጊው ስራ እየተሰራ ሲሆን ይህ መረጃ የደረሳችሁ ማንኛውም የሕዝብ አካላት የወያኔን መዋቅር በማፈራረስ ዳግም ለህዝባዊ እምቢተኝነት እንድትዘጋጁ ምንጮቹ አሳስበዋል::
በኦሮሚያ ክልል አዲስ የጸጥታና የደህንነት/ስለላ መዋቅር ሊዘረጋ ነው::በጋምቤላ የሕወሓት ባለስልጣናትና ቤተሰቦቻቸው ንብረት በታጠቁ የደቡብ ሱዳን ቅጥረኞች እና በአግአዚ ወታደሮች መጠበቅ ተጀምሯል::
===========================================================
Minilik Salsawi – በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አከባቢዎች አሁንም ውጥረት የነገሰ መሆኑን የደህንነት ቢሮ የሚደርሱ ሪፖርቶች እንደሚጠቁሙ ለጉዳዩ ቅርበት ያላችው ወገኖች መረጃ ሰጥተዋል::በኦሮሚያ ክልል በጥሩ ክፍያ በፎቶግራፍ እና በቭድዮ ቀረጻ ላይ ተሰማርተው የነበሩ የኦሕደእድ ካድሬዎች እየተለቀሙ መሆኑ ታውቋል::የወያኔው ጁንታ አገዛዝ አስፈላጊውን ግድያና የጅምላ እስር ከፈጸመ በኋላ ለይስሙላ የመለሳለስ ባሕሪያ በማሳየት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን አቆምኩት እንዲሁም የሕዝቡ ጥያቄ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ነው በሚል የሰራውን እኩይ ተግባር ለመሸፋፈን ቢዳክርም የሕዝቡ ተቃውሞ እያገረሸ ብሎም እንዳተኮሰ ይገኛል::መሰሪ እና ውሸታም የሆነው የወያኔ አስተዳደር ላይ ላዩን በመለሳለስ ውስጥ ውስጡን አዲስ የጸጥታ እና የደህንነት/ ስለላ መዋቅር ሊዘረጋ ሲሆን ሕዝቡ ግን አሁንም ለአንድ ለአምስት የአፈና መዋቅር ያልተበገረ ለአዲሱም የስለላ መዋቅር እንደሚያስቸውግር ስጋት መኖሩት የወያነ የደህንነት መረጃዎች ጠቁመዋል:: የመዋቅሩ አዘረጋግ በተመለከተ አስፈላጊው ስራ እየተሰራ ሲሆን ይህ መረጃ የደረሳችሁ ማንኛውም የሕዝብ አካላት የወያኔን መዋቅር በማፈራረስ ዳግም ለህዝባዊ እምቢተኝነት እንድትዘጋጁ ምንጮቹ አሳስበዋል::
በጋምቤላ ክልል አኙዋክ ብሄሮች ላይ ከቀያቸው አፈናቅሎ በሕወሓቶች ለመተካት በደቡብ ሱዳን ቅጥረኛ ኑዌሮች የተጀመረው ግድያ እና ማሳደድ የቀጠለ ሲሆን የሕወሓት ባለስልጣናትና ቤተሰቦቻቸው ንብረት በታጠቁ የደቡብ ሱዳን ቅጥረኞች እና በአግአዚ ወታደሮች መጠበቅ ተጀምሯል::በአኙዋክ ሕዝብ ላይ እጅግ አደገኛ የሚባልለት ይህ የዘር ማጽዳት ከዚህ ቀደም የተካሄደ ሲሆን ለም መሬቶችን ለመቀራመት ባሰፈሰፉ የሕወሓት ስዎች እና ጋሻጃግሬዎቻቸው የደቡብ ሱዳን ኑዌር ስደተኞችን በማስታጠቅ አከባቢው በደም እንዲጨቀይ አድርገዋል::በአለም አቀፉ እና በሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጫና ግጭቱ ራሱ በከፈተው መንገድ ራሱ ያቀዘቀዘው ሕወሓት አሁንም በበቂ ሁኔታ ለመስፋፋት እና አዳዲስ ለም መሬቶችን ለመያዝ እንዳቀደ በስፋት እየተነገረ ይገኛል::በሃገሪቱ ከባድ እና አደገኛ ውጥረት በመጫር ዘእጎች በሞት እንዲያልኡ እያደረገ የሚገኘውን የሕወሓት አገዛዝ ከስሩ ነቅሎ ለመጣል ትግላችንን አጠናክረን መቀጠል እንዳለብን አሳስባለሁ::

ማክሰኞ 2 ፌብሩዋሪ 2016
የመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንቱን አገደ
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ላዕላይ ምክር ቤት ሰኞ ጥር 16 ቀን 2008 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ፣ የፓርቲውን ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪን አገደ፡፡ ቀጣዩ ጠቅላላ ጉባዔ እስከሚካሄድ ድረስም ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ እንድርያስ ኤሮ ፓርቲውን እንዲመሩ ወስኗል፡፡
‹‹ፕሬዚዳንቱ ስብሰባ እንዲጠሩንና ጠቅላላ ጉባዔ እንዲካሄድ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም ፈቃደኛ ካለመሆን አልፈው፣ ወደ አምባጓሮ በመግባታቸው ይህን ለመወሰን ተገደናል፤›› ሲሉ ተቀዳሚ ፕሬዚዳንቱ አቶ እንድርያስ ለሪፖርተር አስታውቀዋል፡፡
ፓርቲው ከገዥው ፓርቲ የሚደርሱበት ጫናና ፈተናዎች እንደተጠበቁ ሆነው፣ ጥቂት የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች የውስጥ ችግሮችን ተወያይተው እንዳይፈቱ መሰናክል እየሆኑ ነው በማለት ገልጸው፣ ‹‹የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ የላዕላይ ምክር ቤቱን በደንቡ መሠረት ስብሰባ ባለመጥራት፣ እንዲሁም የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባዔ በወቅቱ እንዳይካሄድ በማድረግ ላይ ናቸው፤›› በማለት ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ ስብሰባ እንዲጠሩ በተደጋጋሚ ጠይቀው እንደነበር የገለጹት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ‹‹አቶ አበባው ይህን ማድረግ ባለመፈለጋቸው ከአንድ ሦስተኛ በላይ የምንሆን የምክር ቤቱ አባላት ተሰባስበን በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መክረን ፕሬዚዳንቱን ለማገድ ወስነናል፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡
የፓርቲው ላዕላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንቱን በመተካት እስከ ቀጣይ ጠቅላላ ጉባዔ ድረስም በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንቱ እየተመራ እንዲቆይም እንዲሁ ወስኗል፡፡
ቀጣይ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ መቼ እንደሚካሄድ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹በመጪዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ ይካሄዳል፤›› ሲሉ አቶ እንድሪያስ መልሰዋል፡፡
ከዚህ ውሳኔ በተጨማሪም የፓርቲው ላዕላይ ምክር ቤት ምንም እንኳን የፓርቲው ፕሬዚዳንት የሥልጣን ዘመናቸው የተጠናቀቀ ቢሆንም፣ በመጪው ጠቅላላ ጉባዔ የፓርቲውን ሙሉ ሪፖርት፣ የውስጥና የውጭ ኦዲተሮችን ሪፖርትን ያካተተ ሪፖርት ይዘው እንዲቀርቡም መወሰኑ ተሰምቷል፡፡
የላዕላይ ምክር ቤቱ አባላትም ባወጡት መግለጫ፣ ‹‹እኛ የመኢአድ የላዕላይ ምክር ቤት አባላት መጪው ጠቅላላ ጉባዔ እስኪደረግ ድረስ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንቱና አመራሩ የሚያወርደውን ማንኛውም የድርጅቱ ሥራዎችን ለማከናወን ዝግጁ መሆናችንን እናረጋግጣለን፤›› በማለት ለተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ይሁንታውን መግለጹን አስታውቋል፡፡
ምርጫ 2007 ከመከናወኑ ወራት በፊት መኢአድ ተመሳሳይ ችግር አጋጥሞት እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፣ በወቅቱ ፓርቲውን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት በአቶ ማሙሸት አማረና በአቶ አበባው መሐሪ መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር፡፡
በወቅቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው ውሳኔ መሠረት አቶ አበባው የፓርቲው ፕሬዚዳንት ሆነው እንዲቀጥሉ መደረጉ የሚታወስ ነው፡፡
በመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት ከፕሬዚዳንትነት ሥልጣናቸው የታገዱትን አቶ አበባው በአካልም ሆነ በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡
‹‹ፕሬዚዳንቱ ስብሰባ እንዲጠሩንና ጠቅላላ ጉባዔ እንዲካሄድ በተደጋጋሚ ብንጠይቅም ፈቃደኛ ካለመሆን አልፈው፣ ወደ አምባጓሮ በመግባታቸው ይህን ለመወሰን ተገደናል፤›› ሲሉ ተቀዳሚ ፕሬዚዳንቱ አቶ እንድርያስ ለሪፖርተር አስታውቀዋል፡፡
ፓርቲው ከገዥው ፓርቲ የሚደርሱበት ጫናና ፈተናዎች እንደተጠበቁ ሆነው፣ ጥቂት የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች የውስጥ ችግሮችን ተወያይተው እንዳይፈቱ መሰናክል እየሆኑ ነው በማለት ገልጸው፣ ‹‹የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ የላዕላይ ምክር ቤቱን በደንቡ መሠረት ስብሰባ ባለመጥራት፣ እንዲሁም የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባዔ በወቅቱ እንዳይካሄድ በማድረግ ላይ ናቸው፤›› በማለት ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ ስብሰባ እንዲጠሩ በተደጋጋሚ ጠይቀው እንደነበር የገለጹት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ‹‹አቶ አበባው ይህን ማድረግ ባለመፈለጋቸው ከአንድ ሦስተኛ በላይ የምንሆን የምክር ቤቱ አባላት ተሰባስበን በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መክረን ፕሬዚዳንቱን ለማገድ ወስነናል፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡
የፓርቲው ላዕላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንቱን በመተካት እስከ ቀጣይ ጠቅላላ ጉባዔ ድረስም በተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንቱ እየተመራ እንዲቆይም እንዲሁ ወስኗል፡፡
ቀጣይ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ መቼ እንደሚካሄድ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹በመጪዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ ይካሄዳል፤›› ሲሉ አቶ እንድሪያስ መልሰዋል፡፡
ከዚህ ውሳኔ በተጨማሪም የፓርቲው ላዕላይ ምክር ቤት ምንም እንኳን የፓርቲው ፕሬዚዳንት የሥልጣን ዘመናቸው የተጠናቀቀ ቢሆንም፣ በመጪው ጠቅላላ ጉባዔ የፓርቲውን ሙሉ ሪፖርት፣ የውስጥና የውጭ ኦዲተሮችን ሪፖርትን ያካተተ ሪፖርት ይዘው እንዲቀርቡም መወሰኑ ተሰምቷል፡፡
የላዕላይ ምክር ቤቱ አባላትም ባወጡት መግለጫ፣ ‹‹እኛ የመኢአድ የላዕላይ ምክር ቤት አባላት መጪው ጠቅላላ ጉባዔ እስኪደረግ ድረስ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንቱና አመራሩ የሚያወርደውን ማንኛውም የድርጅቱ ሥራዎችን ለማከናወን ዝግጁ መሆናችንን እናረጋግጣለን፤›› በማለት ለተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ይሁንታውን መግለጹን አስታውቋል፡፡
ምርጫ 2007 ከመከናወኑ ወራት በፊት መኢአድ ተመሳሳይ ችግር አጋጥሞት እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፣ በወቅቱ ፓርቲውን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት በአቶ ማሙሸት አማረና በአቶ አበባው መሐሪ መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር፡፡
በወቅቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው ውሳኔ መሠረት አቶ አበባው የፓርቲው ፕሬዚዳንት ሆነው እንዲቀጥሉ መደረጉ የሚታወስ ነው፡፡
በመኢአድ ላዕላይ ምክር ቤት ከፕሬዚዳንትነት ሥልጣናቸው የታገዱትን አቶ አበባው በአካልም ሆነ በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡
እሑድ 31 ጃንዋሪ 2016
ኢንሳ የአየር ላይ ፎቶ በማንሳት ላይ የሚገኘው ለሱዳን ተሰጥቷል የሚባለውን አልፋሽጋ ተብሎ የሚጠራውን አካባቢ መሆኑ ታወቀ
ጥር ፲፯ (አሥራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ካለፈው ጥር ወር መግቢያ ጀምሮ የአየር ላይ ፎቶ እየተነሳ ያለው አካባቢ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ” ኢትዮጵያ መሬቱ የእኛ መሆኑን እውቅና ሰጥታለች” በማለት ለአልጀዚራ የተናገሩት አልፋሽጋ እየተባለ የሚጠራው ቦታ መሆኑ ታውቋል።
ትናንት ኢሳት የመረጃና ደህንነት ኢንፎረሜሽን ባለሙያ በማናገር በሰራው ዘገባ ላይ በአሁኑ ሰአት የአየር ላይ ፎቶ ለማንሳት ምልክቶችን መሬት ላይ የማስቀመጡ ስራ የሚከናወነው 365 ኪሜ ርዝመት ባለው ቦታ ላይ መሆኑን ቢዘግብም፣ ይህ ርቀት ግን የአየር ላይ ርቀትን የሚያመለክት እንጅ የመሬትን እርቀት የሚያመለክት ባለመሆኑ ማስተከከያ እንዲደረግበት ጠይቀዋል። በመጀመሪያው ሂደት ድንበር የማካለሉ ሂዳት የሚከናወነው 725 ኪሜ ርዝመት ላይ ባለው መሬት ላይ ሲሆን፣ ይህም አካባቢ ሱዳን የኢትዮጵያ መንግስት የእኔ መሬት መሆኑን አምኖልኛል በማለት የገለጸችው አልፋሽጋ እየተባለ የሚጠራውን ለም መሬት የሚያካትት ነው።
አልፋሽጋ የሚባለው ቦታ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ከመለየቷ በፊት ከራስካሳር እስከ አትባራ የሚደርሰውን ቦታ ያካልል እንደነበር የሚገልጹት ባለሙያዎች፣ የኢህአዴግ መንግስት ለማስረከብ እየተዘጋጀ ያለው ከሰቲት ወንዝ እስከ አትባራ ድረስ ያለውን 725 ኪሜ የሚደርስ ሰፊ መሬት ነው። አልፋሽጋ በደቡብ አጥባራ፣ በሰሜን ሰቲት ማሃል ላይ ባህረነጋሽ በተባለ ወንዝ የተከበበ በመሆኑ፣ መሬቱ ለእርሻ ስራ እጅግ ተስማሚ ነው።
በሁለተኛው ዙር መሬት የማካለል ስራ ከሁመራ ጫፍ እስከ ኤልሚ ወይም የሱዳን፣ ኬንያና ኢትዮጵያ መገናኛ ድንበር ድረስ እንደሚካሄድ ባለሙያዎች ገልጸዋል።
የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አልፋሽጋ ሱዳን መሆኑን ኢትዮጵያ ማረጋገጫ ሰጥታለች ቢሉም፣ በኢህአዴግ መንግስት በኩል እስካሁን ምንም አይነት ማስተባበያ አልተሰጠም። ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያምና ቃለአቀባዩ ጌታቸው ረዳ ከሱዳን ጋር ምንም አይነት የድንበር ማካለል ድርድር እየተካሄደ እንዳልሆነ ገልጸው ነበር።
ሱዳኖች በበኩላቸው የሁለቱ አገራት የድንበር ኮሚቴ ስራውን በማጠቃለል ላይ መሆኑንና የመጀመሪያው ድንበር የመለየት ስራ በቅርቡ እንደሚጀመር ገልጸዋል።
የኢህአዴግ መንግስት የድንበር ጉዳዩን ለህዝብ ለምን ግልጽ ማድረግ እንደተሳነው የታወቀ ነገር የለም። መሬቱን በድብቅ ለማስረከብ የሚደረገው ሂደት በሁለቱ አገራት መካከል ሰላም ያመጣል ተብሎ አይታመንም።
የአካባቢው ነዋሪዎች በእርሻ ማሳዎች ላይ የሚተከሉትን ምልክቶች በመንቀል ተቃውአቸውን እንዲገልጹ ባለሙያዎች ጥሪያቸውን በድጋሜ አቅርበዋል።
ዓርብ 8 ጃንዋሪ 2016
ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በዋሽንግተን ዲሲ የፊታችን ሰኞ ጃንዋሪ 25 / 2015 በኣሜሪካ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት
US Department of State
2201 C St NW
Washington, DC. 20520
Date and Time:
Monday 25th January 2016 at 9:00 AM
Dress code Black
2201 C St NW
Washington, DC. 20520
Date and Time:
Monday 25th January 2016 at 9:00 AM
Dress code Black

Organizers: Ethiopian Orthodox Religious Leaders, Ethiopian Muslim Leaders (First Higrah), Ethiopian Evangelical Religious Leaders, United OLF, Moresh Wegene, All Amhara Peoples Party, United Ethiopian Muslims Peaceful Movement Support Group, Patriotic Ginbot 7, EPRP, Shengo, AEDP Support Group, SMNE, DC Joint Task Force, Border Committee, SOCEPP, Netsanet Radio
ማክሰኞ 5 ጃንዋሪ 2016
በወቅታዊ የአገራችን አሳሳቢ ጉዳዮች ላይ ለመምከር የተዘጋጀ የዉይይት መድረክ — በዋሽንግተን ዲሲ
የኢትዮጵያ እና የህዝቦቿ የወደፊት እጣ ፈንታ አሳስበዎታል? ያገርዎ፣ የባህልዎ፣ የእምነትዎ ወዘተ ጉዳይ ያገባኛል ይላሉ? እዉነተኛ ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር፣ የህግ የበላይነት፣ ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ስርዓት እንዲመጣ ይሻሉ? ለነዚህ እና ለመሳሰሉት አንገብጋቢ ጉዳዮች ገንቢ ሃሳብ ለመስማት እና የርስዎንም ለማካፈል እንዲሁም ባገር ዉስጥ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እቅድ እና እንቅስቃሴን ለመረዳት በዚህ ዝግጅት ላይ ተካፋይ ይሁኑ!
ተጋባዥ እንግዶች:
(ከአዲስ አበባ)
ዶ/ር መረራ ጉዲና
ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት
አቶ ነጋሲ በየነ
ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት
አቶ ነጋሲ በየነ
(ከዋሺንግቶን ዲሲ)
አቶ ሀይለገብርኤል አያሌው
አቶ ሄኖክ ጋቢሳ
አቶ ሄኖክ ጋቢሳ
አወያይ:
አቶ ጥበበ ሳሙኤል
አቶ ጥበበ ሳሙኤል
ቀን: እሁድ Jan 10, 2016 ሰአት: 2pm
ቦታ: 7701 16th St NW, Washington DC, 20012
ቦታ: 7701 16th St NW, Washington DC, 20012
አዘጋጅ: የሰማያዊ አንድነት ድጋፍ በሰሜን አሜሪካ
ይህ ዉይይት የሚካሄደው በአዲስ አበባ እና በዋሺንግቶን ዲሲ በቪዲዮ ግንኙነት ስለሆነ በሁለቱ ከተሞች መካከል ያለዉን የሰአታት ልዩነት ታሳቢ በማድረግ ፕሮግራሙ በሰአቱ የሚጀመር መሆኑን አዘጋጆች ማሳሳብ እንሻለን። እርስዎም ከጥሪው ሰአት ቀደም ብለዉ በመገኝት እንዲተባበሩን በማክበር እንጠይቃለን።
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)